ዘፍጥረት 49 – NASV & BPH

New Amharic Standard Version

ዘፍጥረት 49:1-33

ያዕቆብ ልጆቹን ባረከ

49፥1-28 ተጓ ምብ – ዘዳ 33፥1-29

1ከዚህ በኋላ ያዕቆብ ልጆቹን ሁሉ አስጠርቶ እንዲህ አላቸው፤ “በኋለኛው ዘመን ምን እንደሚደርስባችሁ እነግራችሁ ዘንድ ተሰብሰቡ፤

2“እናንተ የያዕቆብ ልጆች ሆይ፤

ተሰብሰቡና ስሙ፤

አባታችሁ እስራኤልንም አድምጡ፤

3“ሮቤል፣ አንተ የበኵር ልጄ ነህ፤

ኀይሌና የጕብዝናዬም መጀመሪያ፤

በክብር ትልቃለህ፤ በኀይልም

ትበልጣለህ።

4እንደ ውሃ የዋለልህ ነህና እልቅና

አይኖርህም፤

የአባትህን መኝታ ደፍረሃል፤

ምንጣፌንም አርክሰሃል።

5“ስምዖንና ሌዊ ወንድማማቾች፣

ሰይፎቻቸው49፥5 በዕብራይስጥ የዚህ ቃል ትርጕም አይታወቅም። የዐመፅ መሣሪያዎች ናቸው።

6ወደ ሸንጓቸው አልግባ፤

ጉባኤያቸው ውስጥ አልገኝ፤

በቍጣ ተነሣሥተው ሰዎችን ገድለዋል፤

የበሬዎችንም ቋንጃ እንዳሻቸው ቈራርጠዋል።

7እጅግ አስፈሪ የሆነ ቍጣቸው፣

ጭከና የተሞላ ንዴታቸው የተረገመ ይሁን፤

በያዕቆብ እበትናቸዋለሁ፤

በመላው እስራኤልም አሠራጫቸዋለሁ።

8“ይሁዳ፣49፥8 ይሁዳ የሚለው ቃል ውዳሴ የሚል ትርጕም ካለው የዕብራይስጥ ቃል የመጣ ሲሆን፣ ከዚሁ ቃል ጋር አንድ ዐይነት ድምፅ አለው። ወንድሞችህ ይወድሱሃል፤

እጅህም የጠላቶችህን ዐንገት ዐንቆ ይይዛል፤

የአባትህ ልጆች በፊትህ ተደፍተው ይሰግዱልሃል።

9አንተ የአንበሳ ደቦል ይሁዳ፤

ከዐደንህ የምትመለስ ልጄ፣

እንደ አንበሳ ያደፍጣል፤ በምድርም ላይ ይተኛል፤

እንደ እንስት አንበሳም ያደባል፤

ታዲያ ማን ሊቀሰቅሰው ይደፍራል?

10በትረ መንግሥት ከይሁዳ እጅ አይወጣም፤

የገዥነት ምርኵዝም ከእግሮቹ መካከል።

ገዥነት የሚገባው እስኪመጣ ድረስ፣49፥10 ወይም ሴሎ እስኪመጣ ድረስ ወይም ክብር የሚገባው እስኪመጣ ድረስ

ሕዝቦች ሁሉ ይታዘዙታል።

11አህያውን በወይን ግንድ፣

ውርንጫውንም በምርጡ የወይን ሐረግ

ቅርንጫፍ ላይ ያስራል፤

ልብሱን በወይን ጠጅ፣

መጐናጸፊያውንም በወይን ጭማቂ ያጥባል።

12ዐይኖቹ ከወይን ጠጅ የቀሉ፣

ጥርሶቹም ከወተት ይልቅ የነጡ ይሆናሉ።

13“ዛብሎን፣ በባሕር ዳር ይኖራል፤

የመርከቦች መጠጊያም ይሆናል፤

ወሰኑም እስከ ሲዶና ይደርሳል።

14“ይሳኮር፣ በጭነት49፥14 የመስክ ላይ እሳት መካከል የሚተኛ

ዐጥንተ ብርቱ አህያ ነው።

15ማረፊያ ቦታው መልካም፣

ምድሪቱም አስደሳች መሆኗን ሲያይ፣

ትከሻውን ለሸክም ያመቻቻል፤

ተገድዶም ያገለግላል።

16“ዳን፣49፥16 ዳን ማለት ፍትሕ ይሰጣል ማለት ነው። ከእስራኤል ነገዶች እንደ አንዱ ሆኖ፣

በራሱ ሕዝብ ላይ ይፈርዳል።

17ዳን የመንገድ ዳር እባብ፣

የመተላለፊያም መንገድ እፉኝት ነው፤

ጋላቢው የኋሊት እንዲወድቅ፣

የፈረሱን ሰኰና ይነክሳል።

18እግዚአብሔር ሆይ (ያህዌ)፤ ማዳንህን እጠባበቃለሁ።

19“ጋድን49፥19 ጋድ ማለት ማጥቃት እንዲሁም ወራሪ ሰራዊት ማለት ነው። ወራሪዎች አደጋ ይጥሉበታል፤

እርሱ ግን ዱካቸውን ተከታትሎ ብድሩን ይመልሳል።

20“አሴር ማእደ ሰፊ ይሆናል፤

ለነገሥታትም የሚስማማ ምግብ ያቀርባል።

21“ንፍታሌም ነጻ እንደ ተለቀቀች፣

የሚያማምሩም ግልገሎች49፥21 ወይም ነጻ፤ ውብ ቃሎችን የሚናገር

እንደምትወልድ ሚዳቋ ነው።

22“ዮሴፍ፤ ፍሬያማ የወይን ተክል፣

በምንጭ ዳር የተተከለ ወይን ነው።

ሐረጎቹ ቅጥርን ያለብሳሉ።49፥22 ወይም ዮሴፍ የዱር የፈረስ ግልገል፣ በምንጭ ዳር ያለ የፈረስ ግልገል፣ በባለ ዕርከን ኰረብታ ላይ የዱር አህያ ነው

23ቀስተኞች በጭካኔ አጠቁት፤

በጥላቻም ነደፉት።

24ነገር ግን በያዕቆብ ኀያል አምላክ ክንድ፣49፥23-24 ወይም ቀስተኞች ያጠቃሉ… ያስፈነጥራሉ… ይኖራሉ… ይቈያሉ

እረኛው በሆነው በእስራኤል ዐለት፣ ቀስቱ ጸና፤

ጠንካራ ክንዱም ቀለጠፈ።

25አንተን በሚረዳህ በአባትህ አምላክ፣

በሚባርክህ፣ ሁሉን ማድረግ በሚችል አምላክ፣49፥25 ዕብራይስጡ ሻዳይ ይለዋል

ከላይ ከሰማይ በሚገኝ ረድኤት፣

ከምድር ጥልቅ በሚገኝ በረከት፣

ከማሕፀንና ከጡት በሚገኝ ምርቃት ይባርክሃል።

26ከጥንት ተራሮች በረከት፣

ከዘላለም ኰረብቶች ምርቃት ይልቅ፣

የአባትህ በረከት ይበልጣል።49፥26 …ከአያት ቅድማያቶቼ… ታላቅ ነው

ይህ ሁሉ በዮሴፍ ራስ ላይ ይውረድ፤

በወንድሞቹ መካከል አለቃ በሆነውም ግንባር ላይ ይረፍ።49፥26 ወይም ከ… የተለየ

27“ብንያም፣ ነጣቂ ተኵላ ነው፤

ያደነውን ማለዳ ይበላል፤

የማረከውን ማታ ይከፋፈላል።”

28እነዚህ ሁሉ ዐሥራ ሁለቱ የእስራኤል ነገዶች ናቸው። ይህም እያንዳንዳቸውን ተገቢ በሆነው በረከት አባታቸው ሲባርካቸው የተናገረው ቃል ነው።

የያዕቆብ መሞት

29ከዚህ በኋላ ያዕቆብ እንዲህ ሲል አዘዛቸው፤ “እነሆ፤ ወደ ወገኖቼ የምሰበሰብበት ጊዜ ደርሷል፤ በኬጢያዊው በኤፍሮን ዕርሻ ውስጥ ባለችው ዋሻ ከአባቶቼ ዘንድ ቅበሩኝ፤ 30ይህ በከነዓን ምድር፣ በመምሬ አጠገብ፣ በማክፌላ ዕርሻ ውስጥ ያለው ዋሻ፣ የመቃብር ቦታ እንዲሆን አብርሃም ከኬጢያዊው ኤፍሮን ላይ ከነዕርሻ ቦታው የገዛው ነው። 31በዚያ አብርሃምና ሚስቱ ሣራ ተቀብረዋል፤ በዚያ ይስሐቅና ሚስቱ ርብቃ ተቀብረዋል፤ 32እኔም ልያን የቀበርኋት እዚያው ነው። ዕርሻውና ዋሻው የተገዙት ከኬጢያውያን49፥32 ወይም ከኬጢ ልጆች ላይ ነው።”

33ያዕቆብ እነዚህን ቃላት ለልጆቹ ተናግሮ እንዳበቃ፣ እግሮቹን በዐልጋው ላይ ሰብስቦ፣ የመጨረሻ ትንፋሹን ተነፈሰ፤ ወደ ወገኖቹም ተሰበሰበ።

Bibelen på hverdagsdansk

1. Mosebog 49:1-33

Jakobs sidste ord til sine 12 sønner

1Derefter tilkaldte Jakob alle sine sønner, og de samlede sig omkring ham: „Nu skal jeg fortælle jer, hvordan det vil gå jer fremover.

2Kom og hør, I Jakobs sønner,

lyt til Israel, jeres far!

3Ruben, du min ældste søn,

det første skud på stammen,

ypperlig i rang og styrke,

4men uregerlig som havets bølger.

Du mistede din forret som førstefødt,

for du gik i seng med din fars kone.

Hvilken skændig handling

at vanære sin far sådan.

5Simeon og Levi, to alen af ét stykke,

mænd af vold og vrede ord.

6Jeres planer og motiver kan jeg ikke acceptere,

i galskab myrdede I mennesker og lemlæstede okser for sjov.

7Forbandet være jeres hidsighed,

forbandet jeres vrede og vold.

I bliver adskilt i Israel,

spredt ud over landet.

8Juda, dine brødre vil juble,

når du tilintetgør dine fjender.

Ja, dine brødre skal bøje sig for dig.

9Juda er en løve, der vogter over sit bytte.

Når han hviler sig, hvem tør da vække ham?

10Scepteret skal tilhøre Juda,

og han skal herske,

indtil den rette hersker kommer,49,10 Betydningen af det hebraiske shilo er omstridt, men det henviser nok til den Messiaskonge, der skulle komme fra Judas slægt.

han, som alle folkeslag skal lyde.

11Han binder sit æsel til en vinstok

og vasker sit tøj i druesaft.

12Hans øjne er mørkere end rødvin,

hans tænder hvidere end mælk.

13Zebulon vil havne ved havet,

hans land bliver hjemsted for skibe,

det strækker sig helt til Sidon.

14Issakar er stærk som et æsel,

han hviler sig mellem kvægfoldene.

15Når han opdager, hvor godt et sted, han har fundet

og hvor frugtbart landet er,

tager han villigt åget på skuldrene

og arbejder hårdt for føden.

16Dan skaffer sit folk deres ret

så godt som nogen af Israels stammer.

17Han er som en slange på stien,

hugger i hestens hæl, så rytteren styrter.

18Åh Gud, du er vores redning!

19Gad bliver angrebet af omstrejfende bander,

men han forfølger og udplyndrer dem.

20Asher får en overflod af afgrøder

og kan levere til kongens hof.

21Naftali løber frit omkring,

kommer gerne med smukke ord.49,21 Eller: „smukt afkom”. Oversættelsen er usikker i flere af disse korte, poetiske vers.

22Josef er som en vinstok, plantet ved kilden,

hvis ranker spreder sig over muren.

23Han blev beskudt med bitterheds pile,

hans modstandere behandlede ham hårdt,

24men han holdt sin bue med fasthed,

hans stærke arme rystede ikke.

Han blev hjulpet af Jakobs mægtige Gud,

og igennem det blev han en hyrde,

en frelser for Israels folk.

25Din fars Gud er din hjælper,

og den Almægtige velsigner dig

med himlens velsignelser ovenfra

og jordens velsignelser nedenfra,

med ægteskabelige glæder

og med mange børn.

26Den velsignelse, du får fra din far,

overgår de ældgamle bjerges velsignelser

og det, de evige høje kan tilbyde.

Må disse velsignelser hvile på Josefs hoved,

på issen af fyrsten blandt brødre.

27Benjamin er som en ulv på rov.

Han æder af sit bytte om morgenen

og deler ud af sit overskud om aftenen.”

28Det var, hvad Jakob sagde til Israels 12 stammeoverhoveder. Hver især fik de deres særlige ord med på vejen.

Jakobs død og begravelse

29Til sidst sagde Jakob til sine sønner: „Nu skal jeg dø. Begrav mig hos mine forfædre i Kana’ans land i hulen på Makpela-marken øst for Mamre, den mark, som Abraham købte af hittitten Efron. 30-32I den gravhule ligger Abraham og Sara begravet. Der ligger også Isak og Rebekka, og der har jeg selv begravet Lea.” 33Med disse ord til sine sønner udtrykte Jakob sin sidste vilje. Så lagde han sig til rette i sengen og drog sit sidste åndedrag.