ዘፍጥረት 42 – NASV & NUB

New Amharic Standard Version

ዘፍጥረት 42:1-38

የዮሴፍ ወንድሞች ወደ ግብፅ ሄዱ

1ያዕቆብ በግብፅ እህል መኖሩን ሲሰማ፣ ልጆቹን እንዲህ አላቸው፤ “ለምን እርስ በርስ ትተያያላችሁ? 2በግብፅ እህል መኖሩን ሰምቻለሁ፤ ስለዚህ ከመሞት መሰንበት ይሻላልና ወደዚያው ወርዳችሁ እህል ሸምቱልን” አላቸው። 3ከዚያም ዐሥሩ የዮሴፍ ወንድሞች እህል ለመሸመት ወደ ግብፅ ወረዱ። 4ነገር ግን ያዕቆብ የዮሴፍን ወንድም ብንያምን፣ ክፉ ነገር ይደርስበታል በሚል ፍርሀት ከወንድሞቹ ጋር አልላከውም። 5ራቡ በከነዓንም በመበርታቱ፣ እህል ለመሸመት ወደ ግብፅ ከሄዱት ሰዎች መካከል የእስራኤል ልጆችም ነበሩ።

6በዚህ ጊዜ ዮሴፍ የምድሪቱ ገዥ ነበር፤ ለአገሩ ሰዎች ሁሉ እህል የሚሸጥላቸው እርሱ ነበር። የዮሴፍ ወንድሞችም እንደ ደረሱ፣ ከፊቱ ቀርበው ወደ ምድር ለጥ ብለው እጅ ነሡት። 7ዮሴፍም ወንድሞቹን ገና ሲያያቸው ወዲያውኑ ዐወቃቸው፤ ነገር ግን እንደማያውቃቸው ሆኖ፣ “ከየት የመጣችሁ ናችሁ?” ብሎ በቍጣ ቃል ተናገራቸው። እነርሱም፣ “እህል ለመሸመት ከከነዓን ምድር የመጣን ነን” ብለው መለሱለት።

8ዮሴፍ ወንድሞቹን ቢያውቃቸውም እንኳ እነርሱ ግን አላወቁትም። 9በዚህ ጊዜ ስለ ወንድሞቹ ያየው ሕልም ትዝ አለውና፣ “ሰላዮች ናችሁ፤ የመጣችሁት አገራችን በየትኛው በኩል ለጥቃት የተጋለጠች መሆኗን ለመሰለል ነው” አላቸው።

10እነርሱም እንዲህ አሉት፤ “ጌታችን ሆይ፤ እንዲህስ አይደለም፤ አገልጋዮችህ የመጣነው እህል ለመሸመት ነው፤ 11ሁላችንም የአንድ አባት ልጆች ነን፤ አገልጋዮችህ የታመንን ሰዎች እንጂ ሰላዮች አይደለንም።”

12እርሱም መልሶ፣ “አይደለም፤ አገራችን በየት በኩል ለጥቃት የተጋለጠች መሆኗን ለመሰለል ነው” አላቸው።

13እነርሱ ግን መልሰው፣ “እኛ አገልጋዮችህ በከነዓን አገር ከሚኖር ከአንድ ሰው የተወለድን ዐሥራ ሁለት ወንድማማቾች ነን። ትንሹ ወንድማችን አባታችን ዘንድ ሲሆን፣ አንዱ ግን የለም” አሉት።

14ዮሴፍም እንዲህ አላቸው፤ “ነገርኋችሁ እኮ፤ ሰላዮች ናችሁ! 15ታናሽ ወንድማችሁ እዚህ እስካልመጣ ድረስ ከዚህ ንቅንቅ እንደማትሉ በፈርዖን ስም እምላለሁ፤ ማንነታችሁ የሚረጋገጠውም በዚህ ነው። 16በሉ፣ ከእናንተ አንዱን ላኩና ወንድማችሁን ይዞ ይመለስ፤ የቀራችሁት ግን የተናገራችሁት ቃል እስኪረጋገጥ ድረስ እስር ቤት ትቈያላችሁ። እንደ ተናገራችሁት ካልሆነ ግን፣ በፈርዖን ስም እምላለሁ፤ ሁላችሁም ሰላዮች ናችሁ” አላቸው። 17ሁሉንም ሦስት ቀን በእስር አቈያቸው።

18በሦስተኛውም ቀን ዮሴፍ እንዲህ አላቸው፤ “እኔ እግዚአብሔርን (ኤሎሂም) ስለምፈራ እንዲህ በማድረግ ሕይወታችሁን አትርፉ። 19ታማኝ ሰዎች ከሆናችሁ፣ ከመካከላችሁ አንዱ እዚህ እስር ቤት ሲቈይ፣ የቀራችሁት ግን ለተራቡት ቤተ ሰቦቻችሁ እህል ትወስዱላቸዋላችሁ፤ 20ታናሽ ወንድማችሁን ግን ይዛችሁ መምጣት አለባችሁ፤ በዚህም የተናገራችሁት ቃል እውነተኛነት ይረጋገጣል፤ እናንተም ከመሞት ትተርፋላችሁ።” እነርሱም ይህንኑ ለመፈጸም ተስማሙ።

21እርስ በርሳቸውም፣ “ይኸው በወንድማችን ላይ ባደረስነው በደል ምክንያት ቅጣታችንን እየተቀበልን ነው። እርሱ እንደዚያ ተጨንቆ ስለ ሕይወቱ ሲማጠነን፣ እኛ አልሰማነውም ነበር፤ ይህ መከራ የደረሰብንም በዚሁ ምክንያት ነው” ተባባሉ።

22ሮቤልም መልሶ፣ “በዚህ ልጅ ላይ፣ ‘ክፉ ነገር አታድርጉ’ ብዬ አልነበረምን? እናንተ ግን አልሰማችሁኝም፤ ስለዚህም ደሙ ከእጃችን ይፈለጋል” አላቸው። 23ዮሴፍ የሚያነጋግራቸው በአስተርጓሚ ስለሆነ የሚነጋገሩትን እንደሚሰማቸው አላወቁም ነበር።

24ከፊታቸውም ዘወር ብሎ አለቀሰ፤ ከዚያም ወደ እነርሱ ተመልሶ እንደ ገና አነጋገራቸው፤ ስምዖንንም ከእነርሱ ለይቶ ዐይናቸው እያየ አሰረው።

25በስልቻዎቻቸው እህል እንዲሞሉላቸው፣ ብሩንም በእያንዳንዱ ሰው ስልቻ ውስጥ መልሰው እንዲያስቀምጡና ለጕዟቸው ስንቅ እንዲያሲዟቸው ዮሴፍ ትእዛዝ ሰጠ። ይህም ከተደረገላቸው በኋላ፣ 26እህላቸውን በአህዮቻቸው ጭነው ጕዟቸውን ቀጠሉ።

27በመንገድም ለዐዳር ሰፍረው ሳሉ፣ ከእነርሱ አንዱ ከያዘው እህል ላይ ለአህያው ለመስጠት ስልቻውን ሲፈታ፣ በስልቻው አፍ ላይ ብሩን አገኘ። 28እርሱም ወንድሞቹን፣ “ኧረ ብሬ ተመልሶልኛል፤ ይኸው ስልቻዬ ውስጥ አገኘሁት” አላቸው።

ሁሉም ልባቸው በድንጋጤ ተሞልቶ እየተንቀጠቀጡ በመተያየት፣ “እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ምን ሊያመጣብን ይሆን?” አሉ።

29በከነዓን ምድር ወዳለው ወደ አባታቸው ወደ ያዕቆብ ከደረሱ በኋላ፣ ያጋጠማቸውን ሁሉ እንዲህ ብለው ነገሩት፤ 30“የአገሩ ጌታ የሆነው ሰው ምድሪቱን እንደምንሰልል ቈጥሮን በቍጣ ተናገረን። 31እኛ ግን እንዲህ አልነው፤ ‘እኛ የታመንን ሰዎች እንጂ ሰላዮች አይደለንም። 32እኛ የአንድ አባት ልጆች የሆንን፣ ዐሥራ ሁለት ወንድማማቾች ነን፤ አንዱ የለም፤ ታናሽ ወንድማችን ግን ከአባታችን ጋር በከነዓን ይገኛል።’

33“ከዚህ በኋላ የአገሩ ጌታ የሆነው ሰው እንዲህ አለን፤ ‘ታማኝ ሰዎች መሆናችሁን የማውቀው በዚህ ነው፤ ከእናንተ መካከል አንዱን ወንድማችሁን እዚህ እኔ ዘንድ ትታችሁ የተቀራችሁት ለተራቡት ቤተ ሰቦቻችሁ እህል ይዛችሁላቸው ሂዱ። 34ነገር ግን ታናሽ ወንድማችሁን ወደ እኔ አምጡት። በዚያንም ጊዜ ታማኝ ሰዎች እንጂ ሰላዮች አለመሆናችሁን ዐውቃለሁ፤ ወንድማችሁንም መልሼ እሰጣችኋለሁ፤ እናንተም በምድሪቱ እንደ ልብ ለመዘዋወር ትችላላችሁ።’ ”

35እህሉንም ሲዘረግፉ በየስልቾቻቸው ውስጥ ብራቸው እንደ ተቋጠረ ተገኘ፤ የእያንዳንዳቸውን የተቋጠረ ብር ሲያዩም፣ እነርሱም ሆኑ አባታቸው ደነገጡ። 36አባታቸው ያዕቆብም፣ “ያለ ልጅ እኮ አስቀራችሁኝ፤ ዮሴፍ የለም፤ ስምዖንም የለም፤ አሁን ደግሞ ብንያምን ልትወስዱ ትፈልጋላችሁ፤ ኧረ ምን ጕድ ነው የመጣብኝ!” አላቸው።

37በዚህን ጊዜ ሮቤል አባቱን፣ “መልሼ ባላመጣው፣ ሁለቱን ወንዶች ልጆቼን ግደላቸው፤ ኀላፊነቱን ለእኔ ተውልኝ፤ እኔው መልሼ አመጣዋለሁ” አለው።

38ያዕቆብም፣ “ልጄ አብሯችሁ ወደዚያ አይወርድም፤ ወንድሙ እንደሆን ሞቷል፤ የቀረው እርሱ ብቻ ነው። ይዛችሁት ስትሄዱ በመንገድ ላይ አደጋ ቢደርስበት፣ ሽበቴን በመሪር ሐዘን ወደ መቃብር42፥38 ዕብራይስጡ ሲኦል ይለዋል። ታወርዱታላችሁ” አላቸው።

Swedish Contemporary Bible

1 Moseboken 42:1-38

Josef och hans bröder träffas i Egypten

1När Jakob hörde att det fanns säd i Egypten, sa han till sina söner: ”Varför står ni här och tittar på varandra? 2Jag har hört att det finns säd i Egypten. Res dit och köp åt oss så att vi överlever och inte svälter ihjäl!”

3Då reste tio av Josefs bröder ner till Egypten för att köpa säd. 4Jakob ville nämligen inte att Josefs bror Benjamin skulle få resa med, eftersom han var rädd att någon olycka skulle drabba honom. 5Israels söner kom alltså till Egypten tillsammans med många andra för att köpa mat, för svälten var mycket svår också i Kanaan.

6Eftersom Josef var härskare över hela Egypten och den som sålde säd till alla, var det till honom hans bröder kom, och de bugade sig djupt för honom med sina ansikten mot jorden.

7Josef kände omedelbart igen sina bröder när han såg dem, men låtsades inte om det. ”Var kommer ni ifrån?” frågade han barskt. ”Från Kanaans land”, svarade de. ”Vi har kommit för att köpa säd.”

8Josef kände igen sina bröder, men de kände inte igen honom. 9Josef kom ihåg drömmarna som han hade haft om dem. Han sa till dem: ”Ni är spioner! Ni har kommit hit för att se var landet saknar skydd.”

10”Nej, herre”, svarade de. ”Vi, dina tjänare, har bara kommit för att köpa mat. 11Vi är alla bröder, söner till en och samme man, hederliga män och inga spioner.” 12”Jo, det är ni”, fortsatte han. ”Ni har kommit för att ta reda på var vårt land saknar skydd.” 13”Herre”, sa de. ”Vi var tolv bröder, söner till en och samme man i Kanaans land. Vår yngste bror är kvar hos vår far, och en av våra bröder finns inte mer.”

14”Det är som jag har sagt”, sa Josef. ”Ni är spioner. 15Men ni ska få prövas. Så sant farao lever ska ni inte lämna Egypten förrän er yngste bror kommit hit. 16En av er får resa och hämta honom. Resten av er stannar kvar här i fängelse, tills vi ser om ni talar sanning eller inte. Om inte, så är ni spioner, så sant farao lever!”

17Under tre dagar lät han dem sitta i fängelse.

18Den tredje dagen sa Josef till dem: ”Gör så här, så får ni leva. Jag är en man som fruktar Gud. 19Om ni är ärliga män, låt då en av er bröder stanna kvar i fängelset, medan resten av er kan resa hem med säd åt era svältande familjer. 20Kom sedan tillbaka med er yngste bror hit till mig. Det får visa om ni talar sanning. Om ni gör det, behöver ni inte dö.”

Så fick de göra, men 21sinsemellan sa de: ”Det här är straffet för det vi gjorde mot vår bror. Vi såg hans vånda och hörde hans vädjan om nåd, men vi ville inte lyssna. Därför har nu denna hemsökelse drabbat oss.” 22”Var det inte det jag sa, att ni inte skulle skada pojken?” svarade Ruben. ”Ni ville inte lyssna, och nu kommer vi att få vårt straff för hans liv.”

23De visste inte att Josef förstod dem, för han hade talat med dem genom tolk. 24Josef vände sig om och gick ut och grät. När han kom tillbaka, talade han till dem igen. Sedan tog han Simon och lät fängsla honom inför deras ögon.

25Josef befallde sedan att männens säckar skulle fyllas med säd och att vars och ens pengar skulle läggas tillbaka i hans säck. Han gav dem också mat för resan. När detta var gjort, 26lastade de sina åsnor med säden och gav sig iväg hem.

27Men när de stannade för natten och en av dem öppnade sin säck för att ge foder åt sin åsna, såg han att hans pengar låg överst i säcken. 28Han sa till sina bröder: ”Mina pengar har lagts tillbaka! De finns här i säcken.” Då blev de alldeles skräckslagna och frågade varandra: ”Vad är det Gud har gjort mot oss?”

29När de sedan kom hem till sin far Jakob i Kanaans land, berättade de för honom allt som hänt dem:

30”Mannen som är herre i landet talade mycket strängt till oss och trodde att vi var spioner. 31’Nej’, sa vi, ’vi är hederliga män och inga spioner. 32Vi var tolv bröder, söner till en och samme far. En finns inte mer, och den yngste är kvar hemma hos vår far i Kanaans land.’ 33Sedan sa mannen, landets herre, till oss: ’Så här ska jag få reda på om ni är hederliga. Lämna en av era bröder här hos mig och ta säd åt era svältande familjer och res hem, 34men för hit er yngste bror till mig. Då vet jag om ni inte är spioner utan hederliga män. Då ska jag ge er bror tillbaka till er, och sedan kan ni röra er fritt i landet.’ ”

35När de tömde sina säckar fanns pungen med pengarna de betalt för säden överst i varje säck. Då blev både de och fadern skräckslagna.

36Deras far Jakob sa till dem: ”Ni har berövat mig mina barn. Josef är borta, Simon är borta, och nu vill ni ta Benjamin också! Allting går mig emot.”

37Då sa Ruben till sin far: ”Du får döda mina två söner om jag inte har med mig Benjamin tillbaka. Lämna honom åt mitt ansvar. Jag ska se till att han kommer tillbaka.”

38Men Jakob svarade: ”Min son ska inte resa dit med er, för hans bror är död, och bara han är kvar. Om något händer honom på er resa, driver ni er gråhårige far med sorg ner i dödsriket.”