ዘፍጥረት 36 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

ዘፍጥረት 36:1-43

የዔሳው ዝርያዎች

36፥10-14 ተጓ ምብ – 1ዜና 1፥35-37

36፥20-28 ተጓ ምብ – 1ዜና 1፥38-42

1ኤዶም የተባለው የዔሳው ትውልድ ይህ ነው፦

2ዔሳው ከከነዓን ሴቶች አገባ፤ እነርሱም፦ የኬጢያዊው የዔሎን ልጅ ዓዳን፣ የኤዊያዊው የፅብዖን ልጅ ዓና የወለዳት አህሊባማ፣ 3እንዲሁም የነባዮት እኅት የሆነችው የእስማኤል ልጅ ቤሴሞት ነበሩ።

4ዓዳ ለዔሳው ኤልፋዝን ወለደችለት፤ ቤሴሞት ደግሞ ራጉኤልን ወለደችለት። 5እንደዚሁም አህሊባማ የዑስን፣ የዕላምንና ቆሬን ወለደችለት፤ እነዚህ ዔሳው በከነዓን አገር የወለዳቸው ልጆች ናቸው።

6ዔሳው ሚስቶቹን፣ ወንዶችና ሴቶች ልጆቹን፣ ቤተ ሰቦቹን በሙሉ እንደዚሁም የቀንድ ከብቶቹንና ሌሎቹንም እንስሳት ሁሉ በከነዓን ምድር ያፈራውን ሀብት እንዳለ ይዞ ከወንድሙ ከያዕቆብ ራቅ ወዳለ ቦታ ሄደ። 7ብዙ ሀብት ስለ ነበራቸው አብረው መኖር አልቻሉም፤ የነበሩበትም ስፍራ ከከብቶቻቸው ብዛት የተነሣ ሊበቃቸው አልቻለም። 8ስለዚህ ኤዶም የተባለው ዔሳው መኖሪያውን በተራራማው አገር በሴይር አደረገ።

9በሴይር ተራራማ አገር የሚኖሩ የኤዶማውያን አባት፣ የዔሳው ዝርያዎች እነዚህ ናቸው፤

10የዔሳው ልጆች ስም፦

የዔሳው ሚስት የዓዳ ልጅ ኤልፋዝና የዔሳው ሚስት የቤሴሞት ልጅ ራጉኤል፤

11የኤልፋዝ ልጆች፦

ቴማን፣ ኦማር፣ ስፎ፣ ጎቶምና ቄኔዝ፤ 12የዔሳው ልጅ ኤልፋዝ ትምናዕ የምትባል ቁባት ነበረችው፤ እርሷም አማሌቅን ወለደችለት፤ የዔሳው ሚስት የዓዳ የልጅ ልጆች እነዚህ ናቸው።

13የራጉኤል ልጆች፦

ናሖት፣ ዛራ፣ ሣማና ሚዛህ፤ እነዚህ ደግሞ የዔሳው ሚስት የቤሴሞት የልጅ ልጆች ናቸው።

14የፅብዖን የልጅ ልጅ፣ የዓና ልጅ የዔሳው ሚስት አህሊባማ ለዔሳው የወለደቻቸው ልጆች፦

የዑስ፣ የዕላማና ቆሬ።

15ከዔሳው ዝርያዎች እነዚህ የነገድ አለቆች ነበሩ፤

የዔሳው የበኵር ልጅ የኤልፋዝ ልጆች፦

አለቃ ቴማን፣ አለቃ ኦማር፣ አለቃ ስፎ፣ አለቃ ቄኔዝ፣ 16አለቃ ቆሬ፣36፥16 ከማሶሬቲኩ ጽሑፍ ጋር ተመሳሳይ ሲሆን በኦሪተ ሳምራውያን ግን (በተጨማሪ ዘፍ 36፥11 እና 1ዜና 1፥36 ይመ) ውስጥ “ቆሬ” የሚለው ቃል የለም። አለቃ ጎቶምና አለቃ አማሌቅ፤ እነዚህ በኤዶም ምድር ከኤልፋዝ የተገኙ የነገድ አለቆች፣ የዓዳ የልጅ ልጆች ነበሩ።

17የዔሳው ልጅ ራጉኤል ልጆች፦

አለቃ ናሖት፣ አለቃ ዛራ፣ አለቃ ሣማና አለቃ ሚዛህ፤ እነዚህ በኤዶም ምድር ከራጉኤል የተገኙ የነገድ አለቆች፣ የዔሳው ሚስት የቤሴሞት የልጅ ልጅ ነበሩ።

18የዔሳው ሚስት የአህሊባም ልጆች፦

አለቃ የዑስ፣ አለቃ የዕላማና፣ አለቃ ቆሬ፤ እነዚህ ከዓና ልጅ፣ ከዔሳው ሚስት ከአህሊባማ የተገኙ የነገድ አለቆች ነበሩ።

19እነዚህም ኤዶም የተባለው የዔሳው ልጆችና የነገድ አለቆቻቸው ነበሩ።

20በዚያች ምድር ይኖሩ የነበሩ የሖሪው የሴይር ልጆች እነዚህ ነበሩ፦

ሎጣን፣ ሦባል፣ ፅብዖን፣ ዓና፣ 21ዲሶን፣ ኤጽርና ዲሳን፤ እነዚህ በኤዶም የነበረው የሴይር ልጆች፣ የሖሪውያን የነገድ አለቆች ነበሩ።

22የሎጣን ልጆች፦

ሖሪና ሔማም36፥22 ሔማም የሚለው የዕብራይስጥ ቃል ሖማም ለሚለው ቃል አማራጭ ትርጕም ነው (1ዜና 1፥39 ይመ)።፤ የሎጣንም እኅት ቲምናዕ ትባል ነበር።

23የሦባል ልጆች፦

ዓልዋን፣ ማኔሐት፣ ዔባል፣ ስፎና አውናም፤

24የፅብዖን ልጆች፦

አያና ዓና፤ ይህ ዓና የአባቱን የፅብዖንን አህዮች ሲጠብቅ፣ የፍል ውሃ ምንጮችን36፥24 ከቩልጌት ጋር ተመሳሳይ ሲሆን ሱርስቱ ግን የተገኘ ውሃ ይለዋል፤ በዕብራይስጥ የዚህ ቃል ትርጕም አይታወቅም። በምድረ በዳ ያገኘ ሰው ነው።

25የዓና ልጆች፦

ዲሶንና የዓና ሴት ልጅ አህሊባማ፤

26የዲሶን36፥26 በዕብራይስጥ ዲሳን፣ የዲሶን አማራጭ ትርጕም ነው። ልጆች፦

ሔምዳን፣ ኤስባን፣ ይትራንና ክራን፤

27የኤጽር ልጆች፦

ቢልሐን፣ ዛዕዋንና ዓቃን፤

28የዲሳን ልጆች፦

ዑፅና አራን።

29የሖሪውያን የነገድ አለቆች እነዚህ ነበሩ፦

ሎጣን፣ ሦባል፣ ፅብዖን፣ ዓና፣ 30ዲሶን፣ ኤጽርና ዲሳን፤ እነዚህ በሴይር ምድር እንደየነገዳቸው የሖሪውያን የነገድ አለቆች ነበሩ።

የኤዶም ነገሥታት

36፥31-43 ተጓ ምብ – 1ዜና 1፥43-54

31ንጉሥ በእስራኤል ከመንገሡ በፊት፣36፥31 ወይም እስራኤላዊ መንግሥት በእነርሱ ላይ ከመንገሡ በፊት በኤዶም የነገሡ ነገሥታት እነዚህ ነበሩ፦

32የቢዖር ልጅ ባላቅ በኤዶም ነበር፤ የከተማውም ስም ዲንሃባ ይባል ነበር።

33ባላቅ ሲሞት፣ የባሶራው የዛራ ልጅ ኢዮባብ በምትኩ ነገሠ።

34ኢዮባብ ሲሞት፣ የቴማኒው ሑሳም በምትኩ ነገሠ።

35ሑሳም ሲሞት፣ የምድያምን ሰዎች በሞዓብ ምድር ድል ያደረጋቸው የባዳድ ልጅ ሃዳድ በምትኩ ነገሠ፤ የከተማውም ስም ዓዊት ይባል ነበር።

36ሃዳድ ሲሞት፣ የመሥሬቃው ሠምላ በምትኩ ነገሠ።

37ሠምላ ሲሞት፣ በወንዙ36፥37 የኤፍራጥስ ወንዝ ሊሆን ይችላል። አጠገብ ያለው የርሆቦቱ ሳኦል በምትኩ ነገሠ።

38ሳኦል ሲሞት፣ የዓክቦር ልጅ በኣልሐናን በምትኩ ነገሠ።

39የዓክቦር ልጅ በኣልሐናን ሲሞት፣ ሃዳር በምትኩ ነገሠ፤ የከተማውም ስም ፋዑ ይባል ነበር፤ የሚስቱም ስም መሄጣብኤል ሲሆን፣ እርሷም የሜዛሃብ ልጅ መጥሬድ የወለደቻት ነበረች።

40ከዔሳው የተገኙት የነገድ አለቆች ስም፣ እንደየነገዳቸውና እንደየአገራቸው ይህ ነው፦

ቲምናዕ፣ ዓልዋ፣ የቴት፣

41አህሊባማ፣ ኤላ፣ ፊኖን፣

42ቄኔዝ፣ ቴማን፣ ሚብሳር፣

43መግዲኤልና ዒራም።

እነዚህ፣ በያዙት ምድር እንደየይዞታቸው ከኤዶም የተገኙ የነገድ አለቆች ነበሩ።

ይህም ዔሳው፣ የኤዶማውያን አባት ነው።

Japanese Contemporary Bible

創世記 36:1-43

36

エサウの子孫

1エサウ、別名エドムの子孫は次のとおりです。

2-3エサウには妻が三人いました。三人ともカナン人で、アダ〔ヘテ人エロンの娘〕、オホリバマ〔アナの娘、ヒビ人ツィブオンの孫娘〕、バセマテ〔イシュマエルの娘でネバヨテの妹、エサウにはいとこに当たる〕。

4アダとの間にはエリファズという息子がいました。バセマテにはレウエルという息子が生まれました。

5オホリバマにはエウシュ、ヤラム、コラという三人の息子が生まれました。以上はみな、カナンの地でエサウに生まれた息子です。

6-8それからエサウは、妻子、召使、家畜の群れなど、カナンの地で手に入れた全財産を携え、セイルの山地に移りました。ヤコブといっしょでは、家畜の数に比べて土地が狭すぎたからです。

9セイルの山地へ移ってからは、エドム人として次の人々が生まれました。

10-12アダの息子エリファズの子は、テマン、オマル、ツェフォ、ガタム、ケナズ、そして、エリファズのそばめティムナが産んだアマレク。

13-14もう一人の妻バセマテにも孫ができました。息子レウエルの子で、ナハテ、ゼラフ、シャマ、ミザ。

オホリバマには孫はいません。

15-16エサウの孫はそれぞれの氏族の長となりました。次のとおりです。テマン族、オマル族、ツェフォ族、ケナズ族、コラ族、ガタム族、アマレク族。以上は、エサウの長男エリファズの子孫です。

17エサウとバセマテがカナンに住んでいた時、生まれたレウエルからは、次の氏族が出ました。ナハテ族、ゼラフ族、シャマ族、ミザ族。

18-19アナの娘オホリバマにできた息子たちからは、次の氏族が出ました。エウシュ族、ヤラム族、コラ族。

20-21もともとセイルの山地に住んでいたホリ人セイルから出た氏族は、次のとおりです。ロタン族、ショバル族、ツィブオン族、アナ族、ディション族、エツェル族、ディシャン族。

22セイルの息子ロタンの子はホリとヘマムです。ロタンにはティムナという妹がいました。

23ショバルの子は、アルワン、マナハテ、エバル、シェフォ、オナム。

24ツィブオンの子は、アヤ、アナ〔父親のろばに草を食べさせていた時、荒れ地で温泉を発見した少年〕。

25アナの子は、ディション、オホリバマ。

26ディションの子は、ヘムダン、エシュバン、イテラン、ケラン。

27エツェルの子は、ビルハン、ザアワン、アカン。

28-30ディシャンの子は、ウツ、アラン。

31-39イスラエルを統治する王がまだいなかった当時、エドム地方を治めていた歴代の王は次のとおりです。エドムのディヌハバ出身のベラ王〔ベオルの息子〕、続いてボツラ出身のヨバブ王〔ゼラフの息子〕、続いてテマン人の出のフシャム王、続いてハダデ王〔ベダデの息子。ミデヤン人がモアブを侵略した際、これを撃退した指導者。出身地はアビテ〕、続いてマスレカ出身のサムラ王、続いて川のそばのレホボテ出身のサウル王、続いてバアル・ハナン王〔アクボルの息子〕、続いてパウ出身のハダル王。ハダル王の妻はマテレデの娘でメヘタブエルと言い、メ・ザハブの孫娘に当たります。

40-43エサウの氏族は次のとおりです。ティムナ族、アルワ族、エテテ族、オホリバマ族、エラ族、ピノン族、ケナズ族、テマン族、ミブツァル族、マグディエル族、イラム族。

これらの氏族の名はまた、それぞれが住んでいた土地の名ともなりました。以上がエサウの子孫であるエドム人です。