ዘፍጥረት 32 – NASV & PCB

New Amharic Standard Version

ዘፍጥረት 32:1-32

ያዕቆብ፣ ወንድሙን ዔሳውን ሊገናኝ ተዘጋጀ

1ያዕቆብም ጕዞውን ቀጠለ፤ የእግዚአብሔርም (ኤሎሂም) መላእክት ተገናኙት፤ 2ባያቸውም ጊዜ፣ “ይህ የእግዚአብሔር (ኤሎሂም) ሰፈር ነው” አለ፤ የዚያንም ቦታ ስም መሃናይም32፥2 መሃናይም ማለት ሁለት ጐራ ማለት ነው። አለው።

3ያዕቆብም በኤዶም አገር ሴይር በተባለው ምድር ወደሚኖረው ወንድሙ ወደ ዔሳው መልእክተኞችን አስቀድሞ ላከ፤ 4እንዲህም ብሎ አዘዛቸው፤ “ጌታዬን ዔሳውን እንዲህ ትሉታላችሁ፤ ‘አገልጋይህ ያዕቆብ እንዲህ ብሏል በሉት፤ “ከላባ ዘንድ ተቀምጬ እስከ አሁን ድረስ እዚያው ኖርሁ፤ 5ከብቶች፣ አህዮች፣ የበግና የፍየል መንጎች እንደዚሁም የወንድና የሴት አገልጋዮች አሉኝ፤ አሁንም ይህን መልእክት ለጌታዬ መላኬ በጎ ፈቃድህን እንዳገኝ በማሰብ ነው።” ’ ”

6የተላኩትም ሰዎች ወደ ያዕቆብ ተመልሰው፣ “ወደ ወንድምህ ወደ ዔሳው ሄደን ነበር፤ እርሱም ሊቀበልህ በመምጣት ላይ ነው፤ አራት መቶ ሰዎችም አብረውት አሉ” አሉት። 7ያዕቆብም በታላቅ ፍርሀትና ጭንቀት ተውጦ፣ አብረውት የነበሩትን ሰዎች ሁለት ቦታ32፥7 ወይም ጐራ፤ በ10 ላይ ያለውም እንዲሁ፤ ከፈላቸው፤ በጎቹን፣ ፍየሎቹን፣ ከብቶቹንና ግመሎቹን ሁለት ቦታ ከፈላቸው። 8“ዔሳው መጥቶ በአንደኛው ላይ አደጋ ቢጥል፣ ሌላው ክፍል32፥8 ወይም ጐራ ሊያመልጥ ይችላል” ብሎ አስቦ ነበር።

9ያዕቆብ እንዲህ ሲል ጸለየ፤ “የአባቴ የአብርሃም አምላክ፣ የአባቴ የይስሐቅ አምላክ (ኤሎሂም) ሆይ፤ ‘ወደ አገርህና ወደ ዘመዶችህ ተመለስ፤ እኔም በጎ ነገር አደርግልሃለሁ’ ያልኸኝ እግዚአብሔር (ያህዌ) ሆይ፤ 10እኔ ባሪያህ እስካሁን ላደረግህልኝ ቸርነትና ታማኝነት ብቁ አይደለሁም፤ ዮርዳኖስን ስሻገር በእጄ ላይ ከነበረው በትር በስተቀር ምንም አልነበረኝም፤ አሁን ግን ይኸው ሁለት ሰራዊት ሆኛለሁ። 11ከወንድሜ ከዔሳው እጅ እንድታድነኝ እለምንሃለሁ፤ መጥቶ እኔንም ሆነ እነዚህን እናቶች ከነልጆቻቸው ያጠፋናል ብዬ ፈርቻለሁና፤ 12ነገር ግን፣ አንተ ራስህ፣ ‘አበለጽግሃለሁ፤ ዘርህንም ሊቈጠር እንደማይቻል እንደ ባሕር አሸዋ አበዛዋለሁ’ ብለኸኛል።”

13በዚያችም ሌሊት ያዕቆብ እዚያው ዐደረ፤ ካለው ሀብት ለወንድሙ ለዔሳው እጅ መንሻ እነዚህን መረጠ፦ 14ሁለት መቶ እንስት ፍየሎችና ሃያ አውራ ፍየሎች፣ ሁለት መቶ እንስት በጎችና ሃያ አውራ በጎች፣ 15ሠላሳ የሚያጠቡ ግመሎች ከነግልገሎቻቸው፣ አርባ ላሞችና ዐሥር ኮርማዎች፣ ሃያ እንስት አህዮችና ዐሥር ተባት አህዮች። 16እነዚህንም በየመንጋው ለይቶ፣ የሚነዷቸውን ጠባቂዎች መደበላቸው፤ ጠባቂዎቹንም፣ “እናንተ ቀድማችሁኝ ሂዱ፣ መንጋዎቹንም አራርቃችሁ ንዷቸው” አላቸው።

17ቀድሞ የሚሄደውንም እንዲህ ሲል አዘዘው፤ “ዔሳው አግኝቶህ፣ ‘የማን ነህ? ወዴትስ ትሄዳለህ? የምትነዳውስ ይህ ሁሉ ከብት የማን ነው?’ ብሎ ቢጠይቅህ፣ 18‘የአገልጋይህ የያዕቆብ ናቸው፤ ለጌታዬ ለዔሳው እጅ መንሻ የሰደዳቸው ናቸው፤ እርሱም ከበስተ ኋላችን እየመጣ ነው’ ብለህ ንገረው።”

19እንዲሁም ሁለተኛውን፣ ሦስተኛውንና መንጎችን የሚነዱትን ሌሎቹንም ሁሉ እንዲህ ሲል አዘዛቸው፤ “ዔሳውን ስታገኙት ይህንኑ ትነግሩታላችሁ፤ 20በተለይም ‘አገልጋይህ ያዕቆብ ከኋላችን እየመጣ ነው’ ማለትን አትዘንጉ።” ይህንም ያዘዘው፣ “ዔሳው ከእኔ ጋር ከመገናኘቱ በፊት እጅ መንሻዬ አስቀድሞ ቢደርሰው ምናልባት ልቡ ይራራና በሰላም ይቀበለኛል” ብሎ ስላሰበ ነበር። 21ስለዚህ የያዕቆብ እጅ መንሻ ከእርሱ አስቀድሞ ተላከ፤ እርሱ ራሱ ግን እዚያው በሰፈሩበት ቦታ ዐደረ።

ያዕቆብ ከእግዚአብሔር ጋር የገጠመው ትግል

22በዚያች ሌሊት ያዕቆብ ተነሣ፤ ሁለቱን ሚስቶቹን እንዲሁም ሁለቱን ሴት አገልጋዮቹንና ዐሥራ አንድ ልጆቹን ይዞ በያቦቅ መልካ ተሻገረ። 23ወንዙን አሻግሮ ከሸኛቸው በኋላ፣ ጓዙን ሁሉ ሰደደ። 24ያዕቆብ ግን ብቻውን እዚያው ቀረ፤ አንድ ሰውም እስኪነጋ ድረስ ሲታገለው ዐደረ። 25ያም ሰው ያዕቆብን ታግሎ ማሸነፍ እንዳቃተው በተረዳ ጊዜ፣ የጭኑን ሹልዳ ነካው፤ በግብግቡም የያዕቆብ ጭን ከመጋጠሚያው ላይ ተናጋ። 26በዚያን ጊዜ ሰውየው፣ “እንግዲህ መንጋቱ ስለሆነ ልቀቀኝና ልሂድ” አለው።

ያዕቆብም፣ “ካልባረክኸኝ አልለቅህም” አለው።

27ሰውየውም፣ “ስምህ ማን ነው?” አለው።

እርሱም፣ “ያዕቆብ ነው” አለ።

28ሰውየውም፣ “ከእግዚአብሔርም (ኤሎሂም)፣ ከሰዎችም ጋር ታግለህ አሸንፈሃልና ከእንግዲህ ስምህ እስራኤል32፥28 እስራኤል ማለት ከእግዚአብሔር ታገለ ማለት ነው። እንጂ፣ ያዕቆብ አይባልም” አለው።

29ያዕቆብም፣ “እባክህ ስምህን ንገረኝ” ብሎ ጠየቀው።

ሰውየውም፣ “ስሜን ለማወቅ ለምን ፈለግህ?” አለው፤ በዚያም ስፍራ ባረከው።

30ስለዚህ ያዕቆብ፣ “እግዚአብሔርን (ኤሎሂም) ፊት ለፊት አይቼ እንኳ ሕይወቴ ተርፋለች” ሲል፣ የዚያን ቦታ ስም ጵኒኤል32፥30 ጵኒኤል ማለት የእግዚአብሔር ፊት ማለት ነው። አለው።

31ጵኒኤልንም32፥31 በዕብራይስጥ ጵኑኤል ማለት ሲሆን፣ የጵኒኤል አማራጭ ትርጕም ነው። እንዳለፈ ፀሓይ ወጣችበት፤ እርሱም በጭኑ ምክንያት ያነክስ ነበር። 32ከዚህም የተነሣ የእስራኤል ልጆች እስከ ዛሬ ድረስ ሹልዳን ከጭኑ ጋር የሚያገናኘውን ሥጋ አይበሉም፤ ምክንያቱም በጭኑ መጋጠሚያ ላይ ያለው የያዕቆብ ሹልዳ ተነክቶ ነበር።

Persian Contemporary Bible

پيدايش 32:1‏-32

آمادگی يعقوب برای روبرو شدن با عيسو

1‏-2يعقوب با خانواده‌اش به سفر خود ادامه داد. در بين راه فرشتگان خدا بر او ظاهر شدند. يعقوب وقتی آنها را ديد، گفت: «اين است لشكر خدا.» پس آنجا را مَحَنايِم32‏:1‏و2 «محنايم» به معنی «دولشکر» است که منظور لشکر خدا و لشکر يعقوب می‌باشد.‏ ناميد.

3‏-4آنگاه يعقوب، قاصدانی با اين پيغام نزد برادر خود عيسو به ادوم، واقع در سرزمين سعير فرستاد: «بنده‌ات يعقوب تا چندی قبل نزد دايی خود لابان سكونت داشتم. 5اكنون گاوها، الاغها، گوسفندها، غلامان و كنيزان فراوانی به دست آورده‌ام. اين قاصدان را فرستاده‌ام تا تو را از آمدنم آگاه سازند. ای سَروَرم، اميدوارم مورد لطف تو قرار بگيرم.»

6قاصدان نزد يعقوب برگشته، به وی خبر دادند كه برادرت عيسو با چهارصد نفر به استقبال تو می‌آيد! 7يعقوب بی‌نهايت ترسان و مضطرب شد. او اعضا خانوادهٔ خود را با گله‌ها و رمه‌ها و شترها به دو دسته تقسيم كرد 8تا اگر عيسو به يک دسته حمله كند، دستهٔ ديگر بگريزد.

9سپس يعقوب چنين دعا كرد: «ای خدای جدم ابراهيم و خدای پدرم اسحاق، ای خداوندی كه به من گفتی به وطن خود نزد خويشاوندانم برگردم و قول دادی كه مرا بركت دهی، 10من لياقت اين همه لطف و محبتی كه به من نموده‌ای ندارم. آن زمان كه زادگاه خود را ترک كردم و از رود اردن گذشتم، چيزی جز يک چوبدستی همراه خود نداشتم، ولی اكنون مالک دو گروه هستم! 11اكنون التماس می‌كنم مرا از دست برادرم عيسو رهايی دهی، چون از او می‌ترسم. از اين می‌ترسم كه مبادا اين زنان و كودكان را هلاک كند. 12به یاد آور كه تو قول داده‌ای كه مرا بركت دهی و نسل مرا چون شنهای ساحل دريا بی‌شمار گردانی.»

13‏-15يعقوب شب را آنجا به سر برد و دويست بز ماده، بيست بز نر، دويست ميش، بيست قوچ، سی شتر شيرده با بچه‌هايشان، چهل گاو ماده، ده گاو نر، بيست الاغ ماده و ده الاغ نر به عنوان پيشكش برای عيسو تدارک ديد.

16او آنها را دسته‌دسته جدا كرده، به نوكرانش سپرد و گفت: «از هم فاصله بگيريد و جلوتر از من حركت كنيد.» 17به مردانی كه دستهٔ اول را می‌راندند گفت كه موقع برخورد با عيسو اگر عيسو از ايشان بپرسد: «كجا می‌رويد؟ برای چه كسی كار می‌كنيد؟ و اين حيوانات مال كيست؟» 18بايد بگويند: «اينها متعلق به بنده‌ات يعقوب می‌باشند و هدايايی است كه برای سَروَر خود عيسو فرستاده است. خودش هم پشت سر ما می‌آيد.»

19‏-20يعقوب همين دستورات را با همان پيغام به ساير دسته‌ها نيز داد. نقشهٔ يعقوب اين بود كه خشم عيسو را قبل از اين كه با هم روبرو شوند، با هدايا فرو نشاند تا وقتی يكديگر را می‌بينند او را بپذيرد. 21پس او هدايا را جلوتر فرستاد اما خود، شب را در اردوگاه به سر برد.

كشتی گرفتن يعقوب در فنی‌ئيل

22‏-24شبانگاه يعقوب برخاست و دو همسر و كنيزان و يازده فرزند و تمام اموال خود را برداشته، به كنار رود اردن آمد و آنها را از گذرگاه يبوق به آن طرف رود فرستاد و خود در همانجا تنها ماند. سپس مردی به سراغ او آمده، تا سپيدهٔ صبح با او كشتی گرفت. 25وقتی آن مرد ديد كه نمی‌تواند بر يعقوب غالب شود، بر بالای ران او ضربه‌ای زد و پای يعقوب صدمه ديد.

26سپس آن مرد گفت: «بگذار بروم، چون سپيده دميده است.» اما يعقوب گفت: «تا مرا بركت ندهی نمی‌گذارم از اينجا بروی.»

27آن مرد پرسيد: «نام تو چيست؟»

جواب داد: «يعقوب.»

28به او گفت: «پس از اين نام تو ديگر يعقوب نخواهد بود، بلكه اسرائيل32‏:28 «اسرائيل» يعنی «کسی که نزد خدا مقاوم است».‏، زيرا نزد خدا و مردم مقاوم بوده و پيروز شده‌ای.»

29يعقوب از او پرسيد: «نام تو چيست؟»

آن مرد گفت: «چرا نام مرا می‌پرسی؟» آنگاه يعقوب را در آنجا بركت داد.

30يعقوب گفت: «در اينجا من خدا را روبرو ديده‌ام و با اين وجود هنوز زنده هستم.» پس آن مكان را فنی‌ئيل (يعنی «چهرهٔ خدا») ناميد.

31يعقوب هنگام طلوع آفتاب به راه افتاد. او به خاطر صدمه‌ای كه به رانش وارد شده بود، می‌لنگيد. 32(بنی‌اسرائيل تا به امروز ماهيچهٔ عِرق النِساء32‏:32 «عِرق النِساء» همان عصب سياتيک است.‏ را كه در ران است نمی‌خورند، زيرا اين قسمت از رانِ يعقوب بود كه در آن شب صدمه ديد.)