ዘፍጥረት 25 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዘፍጥረት 25:1-34

የአብርሃም መሞት

25፥1-4 ተጓ ምብ – 1ዜና 1፥32-33

1አብርሃም ኬጡራ የተባለች ሌላ ሚስት አገባ።25፥1 ወይም አግብቶ ነበር 2እርሷም፦ ዘምራንን፣ ዮቅሳንን፣ ሜዳንን፣ ምድያምን፣ የስቦቅንና ስዌሕን ወለደችለት። 3ዮቅሳንም ሳባንና ድዳንን ወለደ፤ የድዳንም ልጆች፦ አሦራውያን፣ ለጡሳውያንና ለኡማውያን ናቸው። 4የምድያም ልጆች፦ ጌፌር፣ ዔፌር፣ ሄኖኅ፣ አቢዳዕና ኤልዳድ ናቸው። እነዚህ ሁሉ የኬጡራ ልጆች ናቸው።

5አብርሃም ያለውን ሀብት ሁሉ ለይስሐቅ አወረሰው፤ 6ለቁባቶቹ ልጆች ግን በሕይወት እያለ ስጦታ አደረገላቸው፤ ከልጁ ከይስሐቅም ርቀው እንዲኖሩ ወደ ምሥራቅ ምድር ሰደዳቸው።

7አብርሃም በጠቅላላው መቶ ሰባ አምስት ዓመት ኖረ። 8ከዚያም ዐረፈ፤ ዕድሜ ጠግቦ በመልካም ሽምግልና ሞተ፤ ወደ ወገኖቹም ተሰበሰበ። 9ልጆቹ ይስሐቅና እስማኤል በመምሬ አጠገብ በምትገኝ በኬጢያዊው በሰዓር ልጅ በኤፍሮን ዕርሻ በመክፈላ ዋሻ ቀበሩት፤ 10ይህም የዕርሻ ቦታ አብርሃም ከኬጢያውያን25፥10 ወይም የኬጢ ልጆች የገዛው ነበር፤ ከሚስቱ ከሣራ አጠገብ በዚያ ተቀበረ። 11አብርሃም ከሞተ በኋላ እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ይስሐቅን ባረከው፤ በዚህ ጊዜ ይስሐቅ በብኤርላሃይሮኢ አቅራቢያ ይኖር ነበር።

የእስማኤል ልጆች

25፥12-16 ተጓ ምብ – 1ዜና 1፥29-31

12ግብፃዊቷ የሣራ አገልጋይ አጋር፣ ለአብርሃም የወለደችለት የእስማኤል ትውልድ ይህ ነው።

13የእስማኤል ልጆች ስም እንደ ዕድሜያቸው ቅደም ተከተል እንዲህ ነው፦

የእስማኤል በኵር ልጅ ነባዮት፣

ቄዳር፣ ነብዳኤል፣ መብሳም፣

14ማስማዕ፣ ዱማ፣ ማሣ፣

15ኩዳን፣ ቴማን፣ ኢጡር፣

ናፌስና ቄድማ።

16እነዚህ የእስማኤል ልጆች ነበሩ፤ እነርሱም በኖሩባቸውና በሰፈሩባቸው ቦታዎች የዐሥራ ሁለት ነገድ አለቆች ስሞች ናቸው።

17እስማኤል በጠቅላላው መቶ ሠላሳ ሰባት ዓመት ኖረ፤ ከዚያም ሞተ፤ ወደ ወገኖቹም ተሰበሰበ። 18ዘሮቹም መኖሪያቸውን ከግብፅ ድንበር አጠገብ፣ ወደ አሦር በሚወስደው መንገድ፣ በኤውላጥና በሱር መካከል አደረጉ፤ ከወንድሞቻቸውም ሁሉ ጋር በጠላትነት ኖሩ።25፥18 ወይም በስተ ምሥራቅ ኖሩ

ያዕቆብና ዔሳው

19የአብርሃም ልጅ የይስሐቅ ትውልድ ይህ ነው፤

አብርሃም ይስሐቅን ወለደ፤ 20ይስሐቅ ርብቃን ሲያገባ ዕድሜው አርባ ዓመት ነበር፤ ርብቃ በሰሜን ምዕራብ መስጴጦምያ የሚኖረው የሶርያዊው የባቱኤል ልጅ፣ የሶርያዊውም የላባ እኅት ነበረች።

21ይስሐቅ፣ ርብቃ መካን ስለ ነበረች ስለ እርሷ ወደ እግዚአብሔር (ያህዌ) ጸለየ፤ እግዚአብሔርም (ያህዌ) ጸሎቱን ሰማ፤ ርብቃም ፀነሰች። 22ልጆቹም በማሕፀኗ ውስጥ እርስ በርሳቸው ይጋፉ ጀመር፤ እርሷም “ለምን እንዲህ ይሆንብኛል?” ብላ እግዚአብሔርን (ያህዌ) ለመጠየቅ ሄደች።

23እግዚአብሔርም (ያህዌ) እንዲህ አላት፤

“ወገኖች በማሕፀንሽ አሉ፤

ሁለትም ሕዝቦች ከውስጥሽ ተለያይተው ይወጣሉ፤

አንደኛው ከሌላው ይበረታል፤

ታላቁም ለታናሹ አገልጋይ ይሆናል” አላት።

24የመውለጃዋ ጊዜ ሲደርስም፣ እነሆ፤ በማሕፀኗ መንታ ወንዶች ልጆች ነበሩ። 25በመጀመሪያ የተወለደው መልኩ ቀይ፣ ሰውነቱም በሙሉ ጠጕር የለበሰ ነበር፤ ስለዚህ ስሙ ዔሳው25፥25 ዔሳው ማለት ጠጕራማ ማለት ነው፤ በተጨማሪ ኤዶም ተብሎ ተጠርቷል፤ ትርጕሙም ቀይ ማለት ነው። ተባለ። 26ከዚያም ወንድሙ ተወለደ፤ በእጁም የዔሳውን ተረከዝ ይዞ ወጣ፤ ከዚህም የተነሣ ስሙ ያዕቆብ25፥26 ያዕቆብ ማለት ተረከዝ ይይዛል ማለት ነው፤ በምሳሌያዊ አገላለጽ ያታልላል ማለት ነው። ተባለ። ርብቃ ልጆቿን ስትወልድ፣ ይስሐቅ የስድሳ ዓመት ሰው ነበር።

27ልጆቹም ዐደጉ፤ ዔሳው ጐበዝ ዐዳኝ፣ የበረሓም ሰው ሆነ፤ ያዕቆብ ግን ጭምት፣ ከድንኳኑ የማይወጣ ሰው ነበር። 28ይስሐቅ ከዐደን የመጣ ሥጋ ደስ ይለው ስለ ነበር፣ ዔሳውን ይወድደው ነበር፤ ርብቃ ግን ያዕቆብን ትወድደው ነበር።

29አንድ ቀን ያዕቆብ ወጥ እየሠራ ሳለ ዔሳው እጅግ ተርቦ ከዱር መጣ። 30ዔሳውም ያዕቆብን፣ “ቶሎ በል፤ በጣም ርቦኛልና ከዚህ ቀይ ወጥ አብላኝ” አለው። ስለዚህም ስሙ ኤዶም ተባለ።

31ያዕቆብም፣ “በመጀመሪያ ብኵርናህን ሽጥልኝ” አለው።

32ዔሳውም፣ “እነሆ፤ ልሞት ደርሻለሁ፤ ታዲያ ብኵርናው ምን ያደርግልኛል!” አለ።

33ያዕቆብም ዔሳውን፣ “እንግዲያማ፣ አስቀድመህ ማልልኝ” አለው፤ ስለዚህም ማለለት፤ ብኵርናውንም ለያዕቆብ ሸጠለት።

34ያዕቆብም ለዔሳው እንጀራና የምስር ወጥ ሰጠው፤ እርሱም ከበላና ከጠጣ በኋላ ተነሥቶ ሄደ።

ዔሳው ብኵርናውን እንዲህ አድርጎ አቃለላት።

Thai New Contemporary Bible

ปฐมกาล 25:1-34

อับราฮัมสิ้นชีวิต

(1พศด.1:32-33)

1อับราฮัมได้มีภรรยาอีกคนหนึ่งชื่อเคทูราห์ 2นางให้กำเนิดบุตรแก่เขาคือ ศิมราน โยกชาน เมดาน มีเดียน อิชบาก และชูอาห์ 3โยกชานมีบุตรชายชื่อเชบาและเดดาน ลูกหลานของเดดานคือพวกอัสชูริม เลทูชิม และเลอุมมิม 4บุตรของมีเดียนคือ เอฟาห์ เอเฟอร์ ฮาโนค อาบีดา และเอลดาอาห์ ทั้งหมดนี้คือลูกหลานของนางเคทูราห์

5อับราฮัมยกทุกสิ่งที่เขามีให้อิสอัค 6แต่ขณะที่ยังมีชีวิตอยู่ เขาก็ได้ให้ของบางอย่างแก่บุตรทั้งหลายที่เกิดจากบรรดาภรรยาน้อย และส่งคนเหล่านั้นออกไปยังดินแดนทางทิศตะวันออก แยกไปจากอิสอัคบุตรของเขา

7อับราฮัมมีอายุรวมทั้งหมด 175 ปี 8แล้วอับราฮัมก็สิ้นลมหายใจเมื่อชรามากแล้ว เขาเป็นชายชราอายุยืนยาว และเขาก็ถูกรวมไว้กับบรรพบุรุษของเขา 9อิสอัคกับอิชมาเอลบุตรของอับราฮัมจึงฝังเขาไว้ในถ้ำมัคเปลาห์ใกล้มัมเร ในทุ่งของเอโฟรนบุตรของโศหาร์ชาวฮิตไทต์ 10คือทุ่งที่อับราฮัมได้ซื้อจากชาวฮิตไทต์25:10 หรือลูกหลานของเฮท อับราฮัมถูกฝังไว้กับซาราห์ภรรยาของเขาที่นั่น 11หลังจากที่อับราฮัมสิ้นชีวิตแล้ว พระเจ้าทรงอวยพรอิสอัคบุตรชายของเขา ขณะนั้นอิสอัคอาศัยอยู่ที่เบเออร์ลาไฮรอย

เชื้อสายของอิชมาเอล

(1พศด.1:29-31)

12นี่คือเรื่องราวของอิชมาเอล บุตรชายของอับราฮัมที่เกิดจากนางฮาการ์สาวใช้ชาวอียิปต์ของนางซาราห์

13ต่อไปนี้เป็นรายชื่อบุตรทั้งหลายของอิชมาเอล เรียงตามลำดับอายุได้แก่ เนบาโยทบุตรหัวปีของอิชมาเอล เคดาร์ อัดบีเอล มิบสัม 14มิชมา ดูมาห์ มัสสา 15ฮาดัด เทมา เยทูร์ นาฟิช และเคเดมาห์ 16คนเหล่านี้คือบุตรของอิชมาเอล เป็นชื่อของหัวหน้าเผ่าทั้งสิบสองเผ่า ตามถิ่นฐานและค่ายของเขา 17อิชมาเอลมีอายุรวมทั้งหมด 137 ปี แล้วก็สิ้นลมหายใจ และเขาก็ถูกรวมไว้กับบรรพบุรุษของเขา 18ลูกหลานของเขาตั้งถิ่นฐานอยู่ทั่วดินแดนจากเมืองฮาวิลาห์ไปถึงเมืองชูร์ ใกล้ชายแดนอียิปต์ บนเส้นทางไปยังเมืองอัสชูร์ และพวกเขาอยู่ประจันหน้ากับ25:18 หรืออยู่ทางตะวันออกของพี่น้องทั้งปวงของเขา

ยาโคบและเอซาว

19นี่คือเรื่องราวของอิสอัคบุตรชายของอับราฮัม

อับราฮัมได้เป็นบิดาของอิสอัค 20อิสอัคอายุได้สี่สิบปีเมื่อเขาแต่งงานกับเรเบคาห์ บุตรสาวของเบธูเอลชาวอารัมจากถิ่นปัดดานอารัม และเป็นน้องสาวของลาบันชาวอารัม

21อิสอัคอธิษฐานต่อองค์พระผู้เป็นเจ้าเพื่อภรรยาเพราะนางเป็นหมัน และองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงตอบคำอธิษฐานของเขา นางเรเบคาห์ผู้เป็นภรรยาก็ได้ตั้งครรภ์ 22ทารกในท้องเบียดดันกันจนนางร้องว่า “ทำไมฉันจึงต้องเจอเรื่องนี้?” ดังนั้นนางจึงไปทูลถามองค์พระผู้เป็นเจ้า

23องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับนางว่า

“สองชนชาติอยู่ในครรภ์ของเจ้า

สองชนชาติที่เกิดจากตัวเจ้าจะแยกออกจากกัน

ชนชาติหนึ่งจะแข็งแกร่งกว่าอีกชนชาติหนึ่ง

และพี่จะรับใช้น้อง”

24เมื่อถึงกำหนดคลอด ปรากฏว่ามีลูกแฝดชายอยู่ในครรภ์ของนาง 25คนแรกที่เกิดมาตัวแดง มีขนทั่วตัวเหมือนเสื้อขนสัตว์ ดังนั้นพวกเขาจึงตั้งชื่อให้ว่าเอซาว25:25 คำว่าเอซาวอาจจะมีความหมายว่าขนดกเขามีอีกชื่อหนึ่งว่าเอโดมซึ่งแปลว่าแดง 26หลังจากนั้นน้องชายของเขาก็คลอดออกมา มือของเขาจับส้นเท้าของเอซาวไว้ ดังนั้นเขาจึงได้ชื่อว่ายาโคบ25:26 คำว่ายาโคบมีความหมายว่าเขาจับส้นเท้า(เป็นสำนวนแปลว่าเขาหลอกลวง) อิสอัคอายุหกสิบปี เมื่อเรเบคาห์ให้กำเนิดบุตรชายทั้งสอง

27เด็กชายทั้งสองคนเติบโตขึ้น เอซาวเป็นนายพรานผู้ช่ำชอง เป็นคนที่ชอบใช้ชีวิตในทุ่งกว้าง ส่วนยาโคบเป็นคนชอบอยู่กับบ้าน อยู่ตามเต็นท์ต่างๆ 28อิสอัคชอบกินเนื้อสัตว์ที่ล่ามาได้ เขาจึงรักเอซาว แต่เรเบคาห์รักยาโคบ

29ครั้งหนึ่งขณะที่ยาโคบกำลังทำอาหาร เอซาวกลับมาจากทุ่งกว้างและกำลังหิวจัด 30เขากล่าวกับยาโคบว่า “เร็วเข้า ให้ฉันกินอะไรแดงๆ ที่ต้มอยู่นั่นสักหน่อย! ฉันหิวจะตายอยู่แล้ว!” (เขาจึงมีอีกชื่อหนึ่งว่าเอโดม25:30 แปลว่าแดง)

31ยาโคบตอบว่า “ขายสิทธิ์บุตรหัวปีของพี่ให้ฉันก่อน”

32เอซาวตอบว่า “ดูสิ ฉันกำลังจะตายอยู่แล้ว สิทธิ์บุตรหัวปีจะมีประโยชน์อะไรต่อฉัน?”

33แต่ยาโคบกล่าวว่า “สาบานกับฉันก่อน” ดังนั้นเอซาวจึงสาบานกับเขา ขายสิทธิ์บุตรหัวปีให้แก่ยาโคบ

34แล้วยาโคบจึงแบ่งขนมปังและถั่วแดงต้มให้เอซาว เขาก็กินดื่มแล้วก็ลุกจากไป

เห็นได้ว่าเอซาวได้ดูถูกสิทธิ์บุตรหัวปีของตน