ዘፍጥረት 24 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዘፍጥረት 24:1-67

የይስሐቅና የርብቃ ጋብቻ

1በዚህ ጊዜ አብርሃም ሸመገለ፤ ዕድሜውም ገፋ፤ እግዚአብሔርም (ያህዌ) አብርሃምን በሁሉ ነገር ባረከው። 2አብርሃም የንብረቱ ሁሉ ኀላፊ፣ የቤቱ ሁሉ አዛዥ24፥2 ወይም ታላቅ የሆነውን አረጋዊ አገልጋዩን እንዲህ አለው፤ “እጅህን ከጭኔ በታች አድርግ፤ 3ልጄን፣ በመካከላቸው ከምኖር ከከነዓናውያን ሴቶች ልጆች ጋር እንዳታጋባው በሰማይና በምድር አምላክ በእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ማልልኝ። 4ነገር ግን ወደ አገሬ፣ ወደ ገዛ ዘመዶቼ ሄደህ ለልጄ ለይስሐቅ ሚስት ትፈልግለታለህ።”

5አገልጋዩም፣ “ሴቲቱ ከእኔ ጋር ወደዚህ ምድር ለመምጣት ፈቃደኛ ባትሆን ምን አደርጋለሁ? ልጅህን አንተ ወደ መጣህበት አገር ልውሰደውን?” ሲል ጠየቀው።

6አብርሃምም እንዲህ አለው፤ “ምንም ቢሆን ልጄን ወደዚያ እንዳትመልሰው ተጠንቀቅ፤ 7ከአባቴ ቤት፣ ከትውልድ አገሬ ያወጣኝና፣ ‘ለዘርህ ይህችን ምድር እሰጣለሁ’ ብሎ በመሐላ ተስፋ የገባልኝ የሰማይ አምላክ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) መልአኩን ከፊትህ ይልካል፤ ለልጄም ሚስት ከዚያ ታመጣለታለህ። 8ሴቲቱ አብራህ ወደዚህ ለመምጣት ፈቃደኛ ካልሆነች ግን ካስማልሁህ መሐላ ነጻ ትሆናለህ፤ ነገር ግን ወደዚያ አትውሰደው” አለው። 9ስለዚህም አገልጋዩ እጁን ከጌታው ከአብርሃም ጭን በታች አድርጎ ስለዚህ ጕዳይ ማለለት።

10አገልጋዩም ከጌታው ግመሎች መካከል ዐሥሩን ወሰደ፤ ምርጥ ምርጡንም ዕቃ ሁሉ ጭኖ፣ የናኮር ከተማ ወደምትገኝበት ወደ ሰሜን ምዕራብ መስጴጦምያ ተጓዘ። 11እዚያም እንደ ደረሰ፣ ግመሎቹን ከከተማው ውጭ የውሃ ጕድጓድ አጠገብ አንበረከከ፤ ጊዜውም ጥላ የበረደበት፣ ሴቶች ውሃ ለመቅዳት የሚወጡበት ነበር።

12ከዚያም እንዲህ ሲል ጸለየ፣ “የጌታዬ የአብርሃም አምላክ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ሆይ፤ በዛሬው ቀን ጕዳዬን አሳካልኝ፤ ለጌታዬ ለአብርሃም ቸርነትህን አሳየው። 13እነሆ፤ እኔ በዚህ ምንጭ አጠገብ ቆሜአለሁ፤ የከተማዪቱ ሴቶች ልጆች ውሃ ለመቅዳት ወደዚህ ይመጣሉ። 14እንግዲህ፣ ‘እንስራሽን አውርጂና ውሃ አጠጪኝ’ ስላት፣ ‘ዕንካ ጠጣ፤ ግመሎችህንም ላጠጣልህ’ የምትለኝ ቈንጆ እርሷ ለባሪያህ ለይስሐቅ የመረጥካት ትሁን፤ በዚህም ለጌታዬ ቸርነትህን እንዳሳየኸው ዐውቃለሁ።”

15እርሱም ገና ጸሎቱን ሳይጨርስ፣ እነሆ፤ ርብቃ እንስራዋን በትከሻዋ ላይ አድርጋ ብቅ አለች። እርሷም ከአብርሃም ወንድም ከናኮርና ከሚስቱ ከሚልካ የተወለደው የባቱኤል ልጅ ነበረች። 16ልጃገረዲቱ እጅግ ውብና ወንድ ያልደረሰባት ድንግል ነበረች። ወደ ምንጩም ወርዳ ውሃ በእንስራዋ ሞልታ ተመለሰች።

17አገልጋዩም ወደ እርሷ ፈጥኖ ቀረበና፣ “እባክሽ ከእንስራሽ ጥቂት ውሃ አጠጪኝ” አላት።

18እርሷም፣ “ጌታዬ፤ ጠጣ” አለችው፤ ፈጥናም እንስራዋን ወደ እጇ አውርዳ አጠጣችው።

19እርሱን ካጠጣችው በኋላ፣ “ግመሎችህም ጠጥተው እስኪጠግቡ ድረስ ውሃ እቀዳላቸዋለሁ” አለች። 20ፈጥናም በእንስራው ውስጥ የነበረውን ውሃ በገንዳ ውስጥ ገለበጠች፤ እየሮጠች ከጕድጓዱ ውሃ እያመላለሰች ግመሎቹ እስኪበቃቸው ድረስ አጠጣቻቸው። 21አገልጋዩም አንዲት ቃል ሳይናገራት፣ እግዚአብሔር (ያህዌ) መንገዱን አሳክቶለት እንደ ሆነ ወይም እንዳልሆነ ለማወቅ ልጂቱን በአንክሮ ይከታተል ነበር። 22ግመሎቹ ጠጥተው ካበቁ በኋላ ሰውየው ግማሽ ሰቅል24፥22 5.5 ግራም ያህል ነው። የሚመዝን የወርቅ ቀለበትና ዐሥር ሰቅል24፥22 110 ግራም ያህል ነው። የሚመዝኑ ሁለት የወርቅ አምባሮች አውጥቶ፣ 23“ለመሆኑ አንቺ የማን ልጅ ነሽ? በአባትሽ ቤት የምናድርበት ስፍራ ይገኝ እንደ ሆነ፣ እባክሽ ንገሪኝ” ብሎ ጠየቃት።

24እርሷም፣ “እኔ፣ ሚልካ ለናኮር የወለደችለት፣ የባቱኤል ልጅ ነኝ” አለችው፤ 25ደግሞም፣ “በቤታችን በቂ ገለባና ድርቈሽ እንዲሁም ለእናንተ የሚሆን ማደሪያ አለን” አለችው።

26ሰውየውም ተደፍቶ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) ሰገደ፤ 27እንዲህም አለ፤ “ቸርነቱንና ታማኝነቱን ከጌታዬ ያላጓደለ፣ እኔንም ወደ ጌታዬ ዘመዶች ቤት የመራኝ፣ የጌታዬ የአብርሃም አምላክ እግዚአብሔር (ያህዌ) የተመሰገነ ይሁን።”

28ልጂቷ ሮጣ ሄዳ፣ የሆነውን ሁሉ ለእናቷ ቤተ ሰቦች ነገረች። 29ርብቃም ላባ የተባለ ወንድም ነበራት፤ እርሱም ሰውየው ወዳለበት የውሃ ጕድጓድ ፈጥኖ ሄደ። 30እኅቱ ያደረገችውን የወርቅ ቀለበትና አምባሮች እንዳየ፣ እንዲሁም ርብቃ ሰውየው ያላትን ስትናገር እንደ ሰማ፣ ወዲያውኑ ወደ ሰውየው ሄደ፤ በምንጩም ዳር ከግመሎቹ አጠገብ ቆሞ አገኘው፤ 31እርሱንም “አንተ የእግዚአብሔር (ያህዌ) ቡሩክ ሆይ፤ ና፤ እዚህ ውጭ የቆምኸው ለምንድን ነው? እነሆ፤ ለአንተ ማረፊያ ለግመሎችህም ማደሪያ አዘጋጅቻለሁ” አለው።

32ሰውየው ከላባ ጋር ወደ ቤት ሄደ፤ የግመሎቹ ጭነት ተራግፎ ገለባና ድርቈሽ ተሰጣቸው፤ ለእርሱና አብረውት ለነበሩት ሰዎች የእግር ውሃ ቀረበላቸው። 33ለሰውየውም ማዕድ ቀረበለት፤ እርሱ ግን፣ “የመጣሁበትን ጕዳይ ሳልናገር እህል አልቀምስም” አለ።

ላባም፣ “እሺ፤ ተናገር” አለው።

34እርሱም እንዲህ አለ፤ “እኔ የአብርሃም አገልጋይ ነኝ፤ 35እግዚአብሔር (ያህዌ) ጌታዬን እጅግ ባርኮታል፤ እርሱም በልጽጓል፤ በጎችና ከብቶች፣ ብርና ወርቅ፣ ወንድና ሴት አገልጋዮች፣ ግመሎችና አህዮች ሰጥቶታል። 36የጌታዬ ሚስት ሣራ በስተርጅናዋ24፥36 ወይም በስተርጅናው ወንድ ልጅ ወልዳለታለች፤ ጌታዬም ያለውን ሀብት ሁሉ ለልጁ ሰጥቶታል። 37ጌታዬ እንዲህ ሲል አማለኝ፤ ‘ከዚህ ከምኖርበት አገር፣ ከከነዓናውያን ሴቶች ልጆች ጋር ልጄን አታጋባው፤ 38ነገር ግን ወደ አባቴ ቤት፣ ወደ ገዛ ወገኖቼ ሄደህ ለልጄ ሚስት አምጣለት’።

39“እኔም ጌታዬን፣ ‘ሴቲቱ ከእኔ ጋር ወደዚህ ለመምጣት ባትፈቅድስ?’ ብዬ ጠየቅሁት።

40“እርሱም እንዲህ አለኝ፤ ‘አካሄዴን በፊቱ ያደረግሁ እግዚአብሔር (ያህዌ) መልአኩን ከአንተ ጋር ይልካል፤ ከገዛ ወገኖቼና ከአባቴ ቤት፣ ለልጄ ሚስት እንድታመጣለት መንገድህን ያቃናል። 41ወደ ወገኖቼ ከሄድህ፣ ከመሐላው የተፈታህ ትሆናለህ፤ እነርሱ እንኳ ልጂቱን አንሰጥም ቢሉህ፣ ከመሐላው ንጹሕ ትሆናለህ’ አለኝ።

42“እኔም ዛሬ ወደ ውሃው ጕድጓድ ስደርስ እንዲህ ብዬ ጸለይሁ፤ ‘የጌታዬ የአብርሃም አምላክ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ሆይ፤ ፈቃድህ ቢሆን የመጣሁበትን ጕዳይ አቃናልኝ፤ 43እነሆ፤ በምንጩ አጠገብ ቆሜአለሁ፤ ውሃ ልትቀዳ የምትመጣውን ኮረዳ፣ “ከእንስራሽ ውሃ አጠጪኝ” ስላት፣ 44“እሺ ጠጣ፤ ለግመሎችህም እቀዳላቸዋለሁ” የምትለኝ እርሷ እግዚአብሔር (ያህዌ) ለጌታዬ ልጅ የመረጣት ትሁን።’

45“በልቤ የምጸልየውን ጸሎት ገና ሳልጨርስ፣ ርብቃ እንስራዋን በትከሻዋ ላይ አድርጋ ብቅ አለች፤ ወደ ምንጩም ወርዳ ውሃ ቀዳች። እኔም፣ ‘እባክሽ፤ ውሃ አጠጪኝ’ አልኋት።

46“እርሷም ፈጥና እንስራዋን ከትከሻዋ አውርዳ፣ ‘ጠጣ፤ ግመሎችህንም አጠጣለሁ’ አለች። እኔም ጠጣሁ፤ ግመሎቹንም አጠጣች።

47“ለመሆኑ የማን ልጅ ነሽ” ብዬ ጠየቅኋት።

“እርሷም፣ ‘ሚልካ ለናኮር የወለደችለት፣ የባቱኤል ልጅ ነኝ’ አለችኝ።

“ከዚያም ቀለበቱን አደረግሁላት፤ አምባሩንም በእጇ አስገባሁላት። 48ተደፍቼም ለእግዚአብሔር (ያህዌ) ሰገድሁ፤ ለጌታዬ ወንድም የልጅ ልጅ የሆነችውን ቈንጆ፣ ለጌታዬ ልጅ እንዳገኝለት በቀና መንገድ የመራኝን የጌታዬ የአብርሃምን አምላክ እግዚአብሔርን (ኤሎሂም ያህዌ) አመሰገንሁ። 49እንግዲህ አሁን ለጌታዬ በጎነትና ታማኝነት የምታሳዩ ከሆነ ሐሳባችሁን አስታውቁኝ፤ ካልሆነ ግን ቍርጡን ንገሩኝና የምሄድበትን ልወስን።”

50ላባና ባቱኤል እንዲህ ሲሉ መለሱ፤ “ነገሩ ከእግዚአብሔር (ያህዌ) ስለሆነ በዚህም ሆነ በዚያ ምንም ማለት አንችልም። 51ርብቃ ይቻትልህ፤ ይዘሃት ሂድ፤ እግዚአብሔር (ያህዌ) እንደ ተናገረው ለጌታህ ልጅ ሚስት ትሁነው።”

52የአብርሃም አገልጋይ ያሉትን በሰማ ጊዜ በምድር ላይ ተደፍቶ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) ሰገደ። 53ከዚያም የወርቅና የብር ጌጣጌጥ፣ እንዲሁም ልብሶች አውጥቶ ለርብቃ ሰጣት፤ ደግሞም ለወንድሟና ለእናቷ ከፍ ያለ ዋጋ ያላቸው ስጦታዎች ሰጣቸው። 54እርሱና አብረውት የነበሩ ሰዎችም በልተው፣ ጠጥተው እዚያው ዐደሩ።

በማግስቱም ጧት ሲነሡ፣ የአብርሃም አገልጋይ፣ “እንግዲህ ወደ ጌታዬ እንድመለስ አሰናብቱኝ” አለ።

55ወንድሟና እናቷም፣ “ልጂቷ ከእኛ ጋር ቢያንስ ዐሥር ቀን ያህል ትቈይና ከዚያ በኋላ ልትሄድ24፥55 ወይም ልትሄጂ ትችላለች።” ብለው መለሱ።

56እርሱ ግን፣ “እግዚአብሔር (ያህዌ) መንገዴን አቅንቶልኛልና አታዘግዩኝ፤ ወደ ጌታዬ እንድመለስ አሰናብቱኝ” አላቸው።

57እነርሱም፣ “ለማናቸውም ልጂቱን እንጥራትና ትጠየቅ” አሉ። 58ስለዚህ ርብቃን ጠርተው፣ “ከዚህ ሰው ጋር መሄድ ትፈቅጃለሽ?” ሲሉ ጠየቋት።

እርሷም፣ “አዎን፤ እሄዳለሁ” አለች።

59ከዚያም እኅታቸውን ርብቃን ከሞግዚቷ ጋር፣ እንዲሁም የአብርሃምን አገልጋይና አብረውት የነበሩትን ሰዎች አሰናበቷቸው። 60ርብቃንም እንዲህ ብለው መረቋት፤

“እኅታችን ሆይ፤ እልፍ አእላፋት ሁኚ፤

ዘርሽ የጠላቶቹን ደጆች ይውረስ”።

61ከዚያም ርብቃና አገልጋዮቿ ተዘጋጁ፤ ግመሎቻቸውም ላይ ወጥተው ሰውየውን ተከተሉት፤ በዚህ ሁኔታ አገልጋዩ ርብቃን ይዟት ሄደ።

62በዚህን ጊዜ፣ ይስሐቅ በኔጌብ ይኖር ስለ ነበር፣ ከብኤርላሃይሮኢ መጥቶ ነበር። 63እርሱም አንድ ምሽት ላይ በጥሞና24፥63 በዕብራይስጥ የዚህ ቃል ትርጕም አይታወቅም። ለመቈየት ወደ መስክ ወጣ አለ፤ ቀና ብሎ ሲመለከትም፣ ግመሎች ከሩቅ ሲመጡ አየ። 64ርብቃም እንደዚሁ አሻግራ ስትመለከት፣ ይስሐቅን አየች፤ ከግመልም ወረደች፤ 65አገልጋዩንም፣ “ይህ ሊገናኘን በመስኩ ውስጥ ወደዚህ የሚመጣው ሰው ማን ነው?” ስትል ጠየቀችው።

አገልጋዩም፣ “ጌታዬ ነው” ብሎ መለሰላት፤ እርሷም መሸፈኛዋን ተከናነበች።

66አገልጋዩም ያደረገውን ሁሉ ለይስሐቅ ነገረው። 67ይስሐቅም ርብቃን ወደ እናቱ ወደ ሣራ ድንኳን ይዟት ገባ፤ አገባት፣ ሚስትም ሆነችው፤ እርሱም ወደዳት። ይስሐቅም ከእናቱ ሞት ተጽናና።

Thai New Contemporary Bible

ปฐมกาล 24:1-67

อิสอัคกับเรเบคาห์

1อับราฮัมชรามากแล้ว และองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงอวยพรเขาทุกด้าน 2วันหนึ่งอับราฮัมพูดกับหัวหน้าคนรับใช้24:2 หรือคนรับใช้ซึ่งอาวุโสที่สุดซึ่งเป็นผู้ดูแลทรัพย์สมบัติทั้งหมดของเขาว่า “จงเอามือของเจ้าไว้ที่หว่างขาของเรา 3ขอให้เจ้าสาบานต่อพระยาห์เวห์ พระเจ้าผู้สร้างสวรรค์และโลก ว่าเจ้าจะไม่หาลูกสาวของชาวคานาอันซึ่งเป็นหมู่ชนที่เราอาศัยอยู่นี้มาเป็นภรรยาลูกชายของเรา 4แต่จะไปยังบ้านเกิดและญาติพี่น้องของเรา เพื่อหาภรรยาให้อิสอัคลูกชายของเรา”

5คนรับใช้นั้นจึงถามเขาว่า “หากหญิงสาวนั้นไม่ยอมจากบ้านตามข้าพเจ้ามายังดินแดนนี้เล่า? ข้าพเจ้าควรจะพาลูกชายของท่านกลับไปยังบ้านเมืองที่ท่านจากมาหรือ?”

6อับราฮัมกล่าวว่า “อย่าพาลูกชายของเรากลับไปที่นั่นเด็ดขาด 7พระยาห์เวห์ พระเจ้าผู้สร้างสวรรค์ ผู้ทรงนำเราออกมาจากครัวเรือนของบิดาและจากบ้านเกิดเมืองนอนของเรา ผู้ซึ่งได้ตรัสและสัญญากับเราโดยคำปฏิญาณได้ตรัสว่า ‘เราจะมอบดินแดนนี้แก่เชื้อสาย24:7 หรือเมล็ดพันธุ์ของเจ้า’ พระองค์จะทรงให้ทูตของพระองค์นำเจ้าไป เพื่อเจ้าจะหาภรรยาให้ลูกชายของเราจากที่นั่น 8ถ้าหญิงนั้นไม่เต็มใจจะกลับมากับเจ้า เจ้าก็พ้นจากคำสาบานนี้ แต่อย่าพาลูกชายของเรากลับไปที่นั่นเด็ดขาด” 9ดังนั้นคนรับใช้จึงเอามือไว้ที่หว่างขาของอับราฮัมผู้เป็นนายและให้คำสาบานต่อเขาในเรื่องนี้

10แล้วคนรับใช้นั้นจึงนำอูฐของนายสิบตัวบรรทุกของมีค่าทุกประเภทจากนายของเขาออกเดินทางไปอารัมนาหะราอิม และมุ่งหน้าไปยังเมืองของนาโฮร์ 11เขาให้อูฐหมอบลงพักใกล้บ่อน้ำนอกเมือง ขณะนั้นใกล้เวลาเย็นแล้ว ซึ่งเป็นเวลาที่พวกผู้หญิงพากันออกมาตักน้ำ

12แล้วเขาอธิษฐานว่า “ข้าแต่พระยาห์เวห์พระเจ้าของอับราฮัมนายของข้าพระองค์ ขอประทานความสำเร็จแก่ข้าพระองค์ในวันนี้ และขอทรงเมตตาอับราฮัมนายของข้าพระองค์ตามที่ทรงสัญญาไว้ 13ดูเถิด ข้าพระองค์ยืนอยู่ที่ข้างบ่อน้ำนี้ และสาวๆ ในเมืองกำลังออกมาตักน้ำ 14ถ้าหากข้าพระองค์พูดกับหญิงสาวคนใดว่า ‘ขอน้ำในถังของเธอให้ฉันดื่มหน่อย’ แล้วนางตอบว่า ‘เชิญดื่มเถิด และฉันจะตักน้ำให้อูฐของท่านด้วย’ ก็ถือว่านางเป็นผู้ที่พระองค์ทรงเลือกสรรไว้ให้อิสอัคผู้รับใช้ของพระองค์ หากเป็นไปตามนี้ ข้าพระองค์ก็จะรู้ว่าพระองค์ได้ทรงเมตตานายของข้าพระองค์แล้ว”

15ขณะที่เขาอธิษฐานยังไม่ทันจบ เรเบคาห์ก็แบกถังน้ำใส่บ่าออกมา นางเป็นบุตรสาวของเบธูเอล ผู้เป็นบุตรชายของมิลคาห์ มิลคาห์เป็นภรรยาของนาโฮร์น้องชายของอับราฮัม 16เรเบคาห์เป็นหญิงงามมาก เป็นสาวพรหมจารี ไม่เคยหลับนอนกับผู้ชาย เธอลงไปที่บ่อน้ำ เติมน้ำเต็มถังแล้วก็ขึ้นมา

17คนรับใช้นั้นรีบวิ่งไปหานางและกล่าวว่า “ขอน้ำในถังของเธอให้ฉันหน่อยเถิด”

18นางตอบว่า “นายเจ้าข้า เชิญดื่มเถิด” แล้วนางก็รีบยกถังลงให้เขาดื่มทันที

19หลังจากให้เขาดื่มน้ำแล้ว นางก็พูดว่า “ฉันจะตักน้ำให้อูฐของท่านกินจนอิ่มด้วย” 20เธอจึงรีบเทน้ำทั้งหมดจากถังลงในราง แล้ววิ่งไปที่บ่อ ตักน้ำให้อูฐจนทุกตัวกินอิ่ม 21ชายนั้นเฝ้าสังเกตดูนางอยู่เงียบๆ เพื่อดูว่าองค์พระผู้เป็นเจ้าได้ทรงให้การเดินทางของเขาประสบความสำเร็จแล้วหรือไม่

22เมื่ออูฐทุกตัวกินน้ำอิ่มแล้ว เขาก็หยิบห่วงจมูกทองคำหนักราวสองสลึง24:22 ภาษาฮีบรูว่า 1 เบคา และกำไลทองคู่หนึ่งหนักราว 7 บาท24:22 ภาษาฮีบรูว่า 10 เชเขลออกมา 23และเขาถามว่า “เธอเป็นลูกเต้าเหล่าใคร กรุณาบอกฉันเถิดว่าที่บ้านบิดาของเธอมีที่ว่างให้พวกเราพักค้างคืนได้ไหม?”

24นางตอบเขาว่า “ฉันเป็นลูกสาวของเบธูเอล บุตรชายของมิลคาห์กับนาโฮร์” 25และนางกล่าวต่อไปว่า “เรามีฟางกับอาหารสัตว์มากมาย พร้อมทั้งที่ว่างให้ท่านพักค้างคืนด้วย”

26แล้วเขาจึงก้มลงกราบนมัสการองค์พระผู้เป็นเจ้า 27และกล่าวว่า “สรรเสริญพระยาห์เวห์ พระเจ้าของอับราฮัมนายของข้าพระองค์ ผู้ไม่ได้ทรงละทิ้งความเมตตาและความซื่อสัตย์ของพระองค์ต่อนายของข้าพระองค์ ส่วนข้าพระองค์นั้น องค์พระผู้เป็นเจ้าได้ทรงนำข้าพระองค์ให้เดินทางมาถึงบ้านพี่น้องนายของข้าพระองค์”

28นางจึงวิ่งกลับไปบอกเรื่องนี้แก่คนที่บ้านของมารดา 29เรเบคาห์มีพี่ชายคนหนึ่งชื่อลาบัน แล้วลาบันรีบรุดมาพบชายนั้นที่บ่อน้ำ 30ทันทีที่เขาเห็นห่วงจมูกและกำไลที่ข้อมือของน้องสาว และได้ฟังเรเบคาห์เล่าสิ่งที่ชายคนนั้นพูดกับนางแล้ว เขาก็ออกไปหาชายคนนั้นและพบเขายืนอยู่ข้างบ่อน้ำกับฝูงอูฐ 31ลาบันกล่าวว่า “มาเถิด ท่านผู้ที่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงอวยพร ทำไมท่านจึงยืนอยู่ข้างนอกตรงนี้? เราได้จัดบ้านไว้และเตรียมที่สำหรับฝูงอูฐแล้ว”

32ชายนั้นจึงไปที่บ้าน มีคนมาปลดสัมภาระลงจากฝูงอูฐ ให้ฟางและอาหารแก่พวกมัน และจัดหาน้ำมาให้เขาและคนของเขาล้างเท้า 33แล้วยกอาหารมาตั้งตรงหน้าชายนั้น แต่เขากล่าวว่า “ข้าพเจ้าจะยังไม่รับประทานจนกว่าจะได้บอกให้ท่านรู้ถึงสิ่งที่ข้าพเจ้าจำเป็นจะต้องพูด”

ลาบันกล่าวว่า “ถ้าอย่างนั้น จงบอกเราเถิด”

34เขาจึงพูดว่า “ข้าพเจ้าเป็นคนรับใช้ของอับราฮัม 35องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงอวยพรนายของข้าพเจ้าอย่างล้นเหลือ จนท่านกลายเป็นคนมั่งคั่ง พระองค์ประทานฝูงแกะ ฝูงวัว อูฐ ลา เงินและทอง ตลอดจนคนรับใช้ชายหญิง 36ต่อมานางซาราห์ภรรยาของนายคลอดลูกชายคนหนึ่งให้นายเมื่อนาง24:36 หรือเขาอายุมากแล้ว และนายยกทรัพย์สมบัติทั้งหมดให้ลูกคนนี้ 37แล้วนายก็ให้ข้าพเจ้าสาบานและกล่าวว่า ‘เจ้าจะต้องไม่หาลูกสาวของชาวคานาอันซึ่งเป็นเจ้าของดินแดนที่เราอาศัยอยู่นี้มาเป็นภรรยาของลูกชายเรา 38แต่จงไปยังครอบครัวบิดาของเรา ไปยังญาติพี่น้องของเรา และหาภรรยาให้ลูกชายของเรา’

39“แล้วข้าพเจ้าก็ถามนายว่า ‘ถ้าหญิงนั้นไม่ยอมตามข้าพเจ้ามาเล่า?’

40“นายตอบว่า ‘องค์พระผู้เป็นเจ้าผู้ที่เราดำเนินชีวิตอยู่ในทางของพระองค์นั้นจะทรงส่งทูตของพระองค์ไปกับเจ้า และจะทรงทำให้การเดินทางของเจ้าประสบความสำเร็จ เพื่อเจ้าจะสามารถหาภรรยาให้ลูกชายของเราจากญาติพี่น้องของเรา และจากครอบครัวบิดาของเรา 41เมื่อเจ้าไปหาญาติพี่น้องของเราแล้ว เจ้าก็พ้นจากคำสาบานที่ให้กับเรา ถึงแม้ว่าพวกเขาไม่ยอมยกนางให้เจ้า เจ้าก็จะพ้นจากคำสาบาน’

42“วันนี้เมื่อข้าพเจ้ามาถึงบ่อน้ำก็อธิษฐานว่า ‘ข้าแต่พระยาห์เวห์ พระเจ้าของอับราฮัมนายของข้าพระองค์ ถ้าเป็นพระประสงค์ของพระองค์ โปรดให้การเดินทางของข้าพระองค์ครั้งนี้ประสบความสำเร็จ 43ดูเถิด ข้าพระองค์กำลังยืนอยู่ข้างบ่อน้ำ ถ้าหญิงสาวคนหนึ่งออกมาตักน้ำ และข้าพระองค์พูดกับนางว่า “กรุณาให้ฉันดื่มน้ำจากถังของเธอสักหน่อยเถิด” 44และถ้านางตอบว่า “เชิญดื่มเถิด และฉันจะตักน้ำให้อูฐของท่านด้วย” ก็ขอให้นางเป็นผู้ที่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงเลือกสรรไว้ให้ลูกชายของนายข้าพเจ้า’

45“ก่อนที่ข้าพเจ้าจะจบคำอธิษฐานในใจ เรเบคาห์เดินออกมาพร้อมกับแบกถังน้ำบนบ่า นางเดินไปที่บ่อน้ำและตักน้ำ แล้วข้าพเจ้าก็พูดกับนางว่า ‘ขอน้ำให้ฉันดื่มหน่อยเถิด’

46“นางก็รีบยกถังลงมาจากบ่าและบอกว่า ‘เชิญดื่มเถิด และฉันจะตักน้ำให้ฝูงอูฐของท่านด้วย’ ดังนั้นข้าพเจ้าจึงดื่ม และนางก็ตักน้ำให้ฝูงอูฐด้วย

47“ข้าพเจ้าถามนางว่า ‘เธอเป็นลูกเต้าเหล่าใคร?’

“นางก็ตอบว่า ‘เป็นลูกสาวของเบธูเอล ผู้เป็นบุตรของนาโฮร์กับมิลคาห์’

“ข้าพเจ้าจึงสวมห่วงที่จมูกของนางและสวมกำไลที่แขนของนาง 48แล้วข้าพเจ้าก็ก้มลงกราบนมัสการองค์พระผู้เป็นเจ้าข้าพเจ้าสรรเสริญพระยาห์เวห์ พระเจ้าของอับราฮัมนายของข้าพเจ้า พระองค์ทรงนำข้าพเจ้ามาถูกทางเพื่อจะได้นำหลานสาวของน้องชายนายข้าพเจ้าไปให้แก่ลูกชายของเขา 49บัดนี้ ถ้าท่านจะกรุณานายของข้าพเจ้า ขอบอกข้าพเจ้า และถ้าท่านจะปฏิเสธ ก็โปรดบอกข้าพเจ้าเถิด เพื่อข้าพเจ้าจะได้รู้ว่าควรทำอย่างไรต่อไป”

50ลาบันกับเบธูเอลจึงตอบว่า “เรื่องนี้เป็นมาจากองค์พระผู้เป็นเจ้าไม่ว่าจะดีหรือร้ายก็ขอให้เป็นไปตามนั้น 51เรเบคาห์อยู่นี่ พานางไปเถิด ให้นางไปเป็นภรรยาลูกชายเจ้านายของท่าน ตามที่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงนำ”

52เมื่อคนรับใช้ของอับราฮัมได้ยินเช่นนั้นก็ก้มกราบลงถึงพื้นนมัสการองค์พระผู้เป็นเจ้า 53แล้วคนรับใช้หยิบแก้วแหวนเงินทองและเสื้อผ้าอาภรณ์ให้นางเรเบคาห์ และให้ของขวัญล้ำค่าต่างๆ แก่พี่ชายและมารดาของนาง 54แล้วคนรับใช้นั้นกับคนของเขาก็กินดื่มและพักค้างคืนที่นั่น

เมื่อพวกเขาตื่นขึ้นในเช้าวันต่อมา คนรับใช้นั้นจึงกล่าวว่า “โปรดส่งข้าพเจ้ากลับไปหานายของข้าพเจ้าเถิด”

55แต่พี่ชายและมารดาของเรเบคาห์ตอบว่า “ขอให้นางอยู่กับเราอีกสักสิบวันแล้วท่าน24:55 หรือนางค่อยไป”

56แต่คนรับใช้นั้นกล่าวกับพวกเขาว่า “อย่ารั้งข้าพเจ้าไว้เลย ในเมื่อองค์พระผู้เป็นเจ้าประทานความสำเร็จแก่การเดินทางของข้าพเจ้าแล้ว ขอได้ส่งข้าพเจ้ากลับไปหานายของข้าพเจ้าเถิด”

57แล้วพวกเขาจึงกล่าวว่า “ให้เราเรียกนางมาถามดู” 58ดังนั้นพวกเขาจึงเรียกเรเบคาห์มาถามว่า “เจ้าจะไปกับชายผู้นี้หรือไม่?”

นางตอบว่า “ฉันจะไป”

59พวกเขาจึงส่งเรเบคาห์น้องสาวของเขาไปพร้อมกับพี่เลี้ยงของนางและคนรับใช้ของอับราฮัมกับคนของเขา 60พวกเขาอวยพรเรเบคาห์และกล่าวกับนางว่า

“น้องเอ๋ย ขอให้ลูกหลานของเจ้าทวีขึ้น

เป็นแสนเป็นล้าน

ขอให้วงศ์วานของเจ้าครอบครอง

ประตูเมืองของศัตรู”

61จากนั้นเรเบคาห์กับบรรดาสาวใช้ของนางก็เตรียมตัวไว้พร้อมและขึ้นอูฐออกเดินทางกลับไปพร้อมกับคนรับใช้นั้น ดังนั้นคนรับใช้ก็พาเรเบคาห์จากไป

62ฝ่ายอิสอัคกลับมาจากเบเออร์ลาไฮรอย เพราะเขาอยู่ในเนเกบ 63เย็นวันหนึ่งเขาออกไปที่ท้องทุ่ง เดินคิดใคร่ครวญอยู่ และเมื่อเขาเงยหน้าขึ้นก็เห็นขบวนอูฐกำลังเคลื่อนเข้ามา 64เรเบคาห์ก็เงยหน้าขึ้นมองเห็นอิสอัค นางลงมาจากอูฐ 65และถามคนรับใช้นั้นว่า “ชายคนที่เดินลัดทุ่งมาหาเรานั้นคือใคร?”

คนรับใช้นั้นตอบว่า “ท่านเป็นนายของข้าพเจ้า” นางจึงหยิบผ้ามาคลุมหน้า

66แล้วคนรับใช้นั้นก็เล่าทุกสิ่งที่เขาทำให้อิสอัคฟัง 67อิสอัคก็นำเรเบคาห์เข้าไปในเต็นท์ที่ซาราห์ผู้เป็นมารดาของเขาเคยอาศัย และแต่งงานกับเรเบคาห์ ดังนั้นนางจึงมาเป็นภรรยาของเขา และเขารักนาง และอิสอัคก็คลายความเศร้าโศกที่มารดาของเขาเสียชีวิต