ዘፍጥረት 23 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዘፍጥረት 23:1-20

የሣራ ሞት

1ሣራ አንድ መቶ ሃያ ሰባት ዓመት ኖረች፤ 2በከነዓን ምድር፣ በቂርያት አርባቅ ማለትም በኬብሮን ከተማ ሞተች፤ አብርሃምም ለሣራ ሊያለቅስና ሊያዝን መጣ።

3ከዚያም አብርሃም ከተቀመጠበት ከሚስቱ ሬሳ አጠገብ ተነሣ፤ ኬጢያውያንንም23፥3 ወይም የኬጢ ልጆች፤ 5፡7፡10፡16፡18 እና 20 እንዲሁ እንዲህ አላቸው፤ 4“እኔ ለአገሩ እንግዳ፣ ለሰዉ ባዳ ሆኜ በመካከላችሁ የምኖር ነኝና ለመቃብር የምትሆን ቦታ ሽጡልኝ፤ የሚስቴንም ሬሳ ልቅበርበት።”

5ኬጢያውያንም ለአብርሃም እንዲህ ሲሉ መለሱለት፤ 6“ስማን ጌታዬ፤ አንተ እኮ በእኛ ዘንድ እንደ ኀያል መስፍን ነህ፤ ከመቃብር ቦታችን በመረጥኸው ስፍራ ሬሳህን መቅበር ትችላለህ፤ ማናችንም ብንሆን የሞተብህን ሰው እንዳትቀብርበት የመቃብር ቦታችንን አንከለክልህም።”

7ከዚያም አብርሃም ተነሥቶ የአገሬውን ሕዝብ፣ ኬጢያውያንን እጅ ነሣ፤ 8እንዲህም አላቸው፤ “እንድቀብር ከፈቀዳችሁልኝ፣ አንዴ ስሙኝና የሰዓርን ልጅ ኤፍሮንን ስለ እኔ ሆናችሁ ለምኑልኝ። 9ይኸውም በዕርሻው ድንበር ላይ ያለችውን መክፈላ የተባለችውን ዋሻውን እንዲሸጥልኝ ነው፤ በመካከላችሁም የመቃብር ቦታ እንድትሆነኝ በሙሉ ዋጋ እንዲሸጥልኝ ለምኑልኝ።”

10ኬጢያዊው ኤፍሮንም እዚያው መካከላቸው ተቀምጦ ስለ ነበር፣ ወደ ከተማው በር መግቢያ መጥተው የተሰበሰቡት ኬጢያውያን በሙሉ እየሰሙ ለአብርሃም እንዲህ ሲል መለሰለት፤ 11“እንዲህ አይደለም ጌታዬ፤ አድምጠኝ፤ ዕርሻውን በውስጡ ካለው ዋሻ ጋር ውሰደው። እነሆ፤ በወገኖቼ ኬጢያውያን ፊት ሰጥቼሃለሁ፤23፥11 ወይም ሸጬልሃለሁ ሬሳህን ቅበርበት።”

12አብርሃም እንደ ገና የአገሬውን ሕዝብ እጅ ነሣና 13ሁሉም እየሰሙት፣ “የዕርሻውን ቦታ ዋጋ ልክፈል፤ እባክህን ተቀበለኝና ሬሳዬን ልቅበርበት” አለው።

14ኤፍሮንም ለአብርሃም እንዲህ ሲል መለሰለት፤ 15“ጌታዬ ስማኝ፤ የመሬቱ ዋጋማ አራት መቶ ጥሬ ብር23፥15 4.5 ኪሎ ግራም ገደማ ይሆናል ነው፤ ታዲያ ይህ በእኔና በአንተ መካከል ምን ቁም ነገር አለው? ይልቅስ ሬሳህን ቅበርበት” አለው።

16አብርሃምም፣ ኤፍሮን በኬጢያውያን ፊት በተናገረው ዋጋ ተስማማ፤ በወቅቱም የንግድ መለኪያ መሠረት አራት መቶ ጥሬ ብር መዘነለት።

17በዚህ ሁኔታ፣ በመምሬ አጠገብ በመክፈላ ያለው የኤፍሮን ዕርሻ ቦታ ከነዋሻው በክልሉ ካሉት ዛፎች ሁሉ ጭምር ለአብርሃም በርስትነት ተላለፈ፤ 18ወደ ከተማው በር በመጡት ኬጢያውያንም ሁሉ ፊት የአብርሃም ንብረት መሆኑም ተረጋገጠለት። 19ከዚህም በኋላ አብርሃም በከነዓን ምድር፣ በመምሬ አጠገብ፣ መክፈላ በተባለች ዕርሻ ውስጥ ባለችው ዋሻ የሚስቱን የሣራን ሬሳ ቀበረ፤ ይህችም ኬብሮን ናት። 20ስለዚህ ዕርሻውና ውስጡ የሚገኘው ዋሻ የመቃብር ቦታ እንዲሆን ከኬጢያውያን ለአብርሃም በርስትነት ተላለፈለት።

Thai New Contemporary Bible

ปฐมกาล 23:1-20

ซาราห์สิ้นชีวิต

1ซาราห์มีชีวิตอยู่จนอายุ 127 ปี นี่คือช่วงชีวิตของนางซาราห์ 2นางตายที่คีริยาทอารบา (คือเฮโบรน) ในดินแดนคานาอัน อับราฮัมไว้ทุกข์ให้ซาราห์และคร่ำครวญอาลัยถึงนาง

3แล้วอับราฮัมลุกขึ้นจากข้างศพภรรยาและกล่าวกับคนฮิตไทต์23:3 หรือลูกหลานของเฮทเช่นเดียวกับข้อ 5,7,10,16,18 และ 20ว่า 4“ข้าพเจ้าเป็นคนต่างด้าวต่างแดนในหมู่พวกท่าน ขอที่ดินผืนหนึ่งของท่านให้แก่ข้าพเจ้าไว้ใช้เป็นสุสานเถิด เพื่อข้าพเจ้าจะได้ฝังผู้ตายของข้าพเจ้า”

5คนฮิตไทต์ตอบอับราฮัมว่า 6“นายเจ้าข้า ขอฟังเราเถิด ท่านเป็นเจ้านายผู้ทรงอำนาจในหมู่พวกเรา เชิญฝังผู้ตายของท่านในอุโมงค์ฝังศพที่ดีที่สุดของเรา ไม่มีผู้ใดห้ามท่านฝังผู้ตายของท่านในอุโมงค์ฝังศพของเขา”

7อับราฮัมลุกขึ้นน้อมคำนับชาวแผ่นดินฮิตไทต์ 8เขากล่าวกับคนเหล่านั้นว่า “ถ้าท่านเต็มใจให้ข้าพเจ้าฝังผู้ตายของข้าพเจ้า ก็ขอได้โปรดฟังข้าพเจ้าและวิงวอนเอโฟรนบุตรของโศหาร์แทนข้าพเจ้า 9เพื่อเขาจะขายถ้ำมัคเปลาห์ซึ่งอยู่ตรงปลายทุ่งของเขาแก่ข้าพเจ้า ขอให้เขาขายให้ข้าพเจ้าเต็มราคาเพื่อเป็นสุสานท่ามกลางพวกท่าน”

10ฝ่ายเอโฟรนคนฮิตไทต์ก็นั่งอยู่ในหมู่ชนของเขา และเขาตอบอับราฮัมให้คนฮิตไทต์ทุกคนซึ่งมาชุมนุมกันที่ประตูเมืองนั้นได้ยินด้วย 11เขากล่าวว่า “อย่าเลยนายเจ้าข้า โปรดฟังข้าพเจ้าเถิด ข้าพเจ้าให้23:11 คำว่าให้ทั้งสามแห่งในข้อนี้อาจแปลว่าขายก็ได้ที่ดินผืนนี้แก่ท่าน และข้าพเจ้าให้ถ้ำในที่ดินนั้นแก่ท่าน ข้าพเจ้าให้ที่แห่งนี้แก่ท่านต่อหน้าประชาชนของข้าพเจ้า จงฝังผู้ตายของท่านเถิด”

12อับราฮัมจึงน้อมคำนับชาวแผ่นดินนั้นอีกครั้ง 13แล้วตอบเอโฟรนให้คนอื่นๆ ได้ยินด้วยว่า “โปรดฟังข้าพเจ้า ข้าพเจ้าจะจ่ายเงินค่าที่ดินผืนนี้ โปรดรับไว้เถิด เพื่อข้าพเจ้าจะได้ฝังผู้ตายของข้าพเจ้าที่นั่น”

14เอโฟรนตอบอับราฮัมว่า 15“นายเจ้าข้า โปรดฟังข้าพเจ้า ที่ดินนั้นราคา 400 เชเขล23:15 1 เชเขล คือเงินหนักประมาณ 11.5 กรัม มีค่าเท่ากับค่าแรงสองเดือน เช่นเดียวกับข้อ 16 แต่นั่นมีความหมายอะไรระหว่างเรากับท่าน? เชิญฝังผู้ตายของท่านเถิด”

16อับราฮัมตกลงตามข้อเสนอของเอโฟรน จึงชั่งเงินจ่ายให้ตามราคาที่เขาบอกต่อหน้าคนฮิตไทต์ คือเงิน 400 เชเขลตามน้ำหนักที่พวกพ่อค้าใช้กันในเวลานั้น

17ดังนั้นที่ดินของเอโฟรนในมัคเปลาห์ใกล้มัมเร คือทั้งท้องทุ่งและถ้ำในที่ดินผืนนั้น และต้นไม้ทั้งหมดที่อยู่ริมทุ่งได้ถูกโอนกรรมสิทธิ์ 18มาเป็นสมบัติของอับราฮัมต่อหน้าคนฮิตไทต์ทั้งหมดที่มาชุมนุมกันที่ประตูเมือง 19จากนั้นอับราฮัมจึงฝังศพซาราห์ภรรยาของเขาในถ้ำที่อยู่ในทุ่งมัคเปลาห์ใกล้มัมเร (ซึ่งอยู่ที่เมืองเฮโบรน) ในดินแดนคานาอัน 20ดังนั้นคนฮิตไทต์ได้โอนทุ่งและถ้ำในที่ดินผืนนั้นให้เป็นกรรมสิทธิ์ของอับราฮัมเพื่อใช้เป็นสุสาน