ዘፍጥረት 16 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዘፍጥረት 16:1-16

አጋርና እስማኤል

1የአብራም ሚስት ሦራ፣ ልጆች አልወለደችለትም ነበር፤ እርሷም አጋር የምትባል ግብፃዊት አገልጋይ ነበረቻት። 2አብራምንም፣ “እግዚአብሔር (ያህዌ) ልጅ እንዳልወልድ አድርጎኛል። ምናልባት በእርሷ በኩል ልጆች አገኝ እንደሆን ሄደህ ከአገልጋዬ ጋር ተኛ” አለችው።

አብራምም ሦራ ባለችው ተስማማ። 3አብራም በከነዓን ምድር ዐሥር ዓመት ከኖረ በኋላ ሚስቱ ሦራ ግብፃዊት አገልጋይዋን አጋርን ሚስት እንድትሆነው ለባሏ ሰጠችው። 4አብራምም ከአጋር ጋር ተኛ፤ እርሷም ፀነሰች። አጋርም ነፍሰ ጡር መሆኗን ባወቀች ጊዜ እመቤቷን መናቅ ጀመረች። 5ሦራም አብራምን፣ “ለደረሰብኝ በደል ተጠያቂው አንተ ነህ፤ አገልጋዬ ዕቅፍህ ውስጥ እንድትገባ እኔው ሰጠሁህ፤ አሁን ግን ይኸው ማርገዟን ስታውቅ ትንቀኝ ጀመር፤ እግዚአብሔር (ያህዌ) በአንተና በእኔ መካከል ይፍረድ” አለችው።

6አብራምም፣ “አገልጋይሽ እንደ ሆነች በእጅሽ ውስጥ ናት፤ የፈለግሽውን አድርጊባት” አላት። ከዚያም ሦራ ስላሠቃየቻት አጋር ጥላት ኰበለለች።

7የእግዚአብሔር (ያህዌ) መልአክ አጋርን በአንድ የውሃ ምንጭ አጠገብ በምድረ በዳ አገኛት፤ ምንጩም ወደ ሱር በሚወስደው መንገድ ዳር ነበር። 8መልአኩም፣ “የሦራ አገልጋይ አጋር ሆይ፤ ከየት መጣሽ? ወዴትስ ትሄጃለሽ?” አላት፤

እርሷም፣ “ከእመቤቴ ከሦራ ኰብልዬ መምጣቴ ነው” ብላ መለሰች።

9የእግዚአብሔርም (ያህዌ) መልአክ፣ “ወደ እመቤትሽ ተመለሽ፤ ለእርሷም ተገዥላት” አላት። 10ደግሞም መልአኩ፣ “ዘርሽን እጅግ አበዛለሁ፤ ከብዛቱም የተነሣ ሊቈጠር አይችልም” አላት።

11የእግዚአብሔርም (ያህዌ) መልአክ በተጨማሪ እንዲህ አላት፤

“እነሆ፤ ፀንሰሻል፤

ወንድ ልጅ ትወልጃለሽ፤

እግዚአብሔር (ያህዌ) ችግርሽን ተመልክቷል፤

ስሙን እስማኤል16፥11 እስማኤል ማለት እግዚአብሔር ይሰማል ማለት ነው። ትዪዋለሽ።

12እርሱም እንደ ዱር አህያ ይሆናል፤

እጁንም ባገኘው ሰው ሁሉ ላይ ያነሣል፤

ያገኘውም ሁሉ እጁን ያነሣበታል፤

ከወንድሞቹ ሁሉ ጋር እንደ ተጣላ ይኖራል።”16፥12 ወይም በስተ ምሥራቅ ይኖራል

13እርሷም ያናገራትን እግዚአብሔርን (ያህዌ)፣ “ኤልሮኢ” ብላ ጠራችው፤ ምክንያቱም “የሚያየኝን አሁን አየሁት”16፥13 ወይም ኋላውን አየሁት ብላ ነበርና። 14ከዚህ የተነሣ የዚያ ምንጭ ስም፣ “ብኤርለሃይሮኢ”16፥14 ብኤርለሃይሮኢ ማለት የሚያየኝ የሕያው ምንጭ ማለት ነው። ተብሎ ተጠራ፤ እስካሁንም በቃዴስና በባሬድ መካከል ይገኛል።

15አጋር ለአብራም ወንድ ልጅ ወለደችለት፤ አብራምም ስሙን እስማኤል ብሎ ጠራው። 16አብራም፣ አጋር እስማኤልን በወለደች ጊዜ ዕድሜው 86 ዓመት ነበር።

Thai New Contemporary Bible

ปฐมกาล 16:1-16

ฮาการ์กับอิชมาเอล

1นางซารายภรรยาของอับรามไม่มีบุตรให้แก่อับราม แต่นางมีสาวใช้ชาวอียิปต์ชื่อฮาการ์ 2นางจึงกล่าวกับอับรามว่า “ดูสิองค์พระผู้เป็นเจ้าไม่ยอมให้ฉันมีลูก จงไปนอนกับสาวใช้ของฉัน บางทีฉันจะมีลูกผ่านทางนาง”

อับรามก็ฟังคำของนางซาราย 3ฉะนั้นหลังจากที่อับรามอาศัยอยู่ที่คานาอันได้สิบปี นางซารายภรรยาของเขาจึงนำนางฮาการ์สาวใช้ชาวอียิปต์มาให้สามีของนาง ให้เป็นภรรยาของเขา 4เขาก็หลับนอนกับฮาการ์และนางก็ตั้งครรภ์

เมื่อนางรู้ว่าตนตั้งครรภ์แล้วก็เริ่มดูถูกนายหญิง 5ซารายจึงพูดกับอับรามว่า “ท่านต้องรับผิดชอบต่อเรื่องแย่ๆ ที่เกิดขึ้นกับฉัน ฉันมอบสาวใช้ของฉันไว้ในอ้อมอกของท่าน พอนางท้อง ท่านก็ปล่อยให้นางดูถูกฉัน ขอองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงตัดสินความระหว่างท่านกับฉันว่าใครผิดใครถูก”

6อับรามจึงตอบว่า “สาวใช้ของเจ้าก็อยู่ในมือของเจ้า จงทำกับนางตามที่เจ้าเห็นควรเถิด” นางซารายจึงกดขี่ข่มเหงฮาการ์ ดังนั้นนางฮาการ์จึงหลบลี้หนีหน้าไป

7ทูตขององค์พระผู้เป็นเจ้าพบนางฮาการ์ในทะเลทรายใกล้บ่อน้ำพุซึ่งอยู่ริมทางที่จะไปเมืองชูร์ 8และทูตนั้นพูดว่า “ฮาการ์ สาวใช้ของซาราย เจ้ามาจากไหนและกำลังจะไปที่ไหน?”

นางตอบว่า “ข้าพเจ้ากำลังหนีนางซารายนายหญิงของข้าพเจ้า”

9แล้วทูตขององค์พระผู้เป็นเจ้ากล่าวกับนางว่า “จงกลับไปหานายหญิงของเจ้าและยอมอยู่ใต้อาณัติของนาง” 10ทูตขององค์พระผู้เป็นเจ้ากล่าวอีกว่า “เราจะเพิ่มลูกหลานของเจ้าให้มากมายจนนับไม่ถ้วน”

11ทูตขององค์พระผู้เป็นเจ้ากล่าวกับนางอีกว่า

“บัดนี้เจ้ากำลังตั้งครรภ์

และเจ้าจะมีบุตรชาย

เจ้าจะตั้งชื่อเขาว่าอิชมาเอล16:11 แปลว่าพระเจ้าทรงได้ยิน

เพราะองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงได้ยินความทุกข์ระทมของเจ้า

12เขาจะเป็นดั่งลาป่าในมือมนุษย์

มือของเขาจะต่อสู้กับทุกคน

และมือของทุกคนก็จะต่อสู้กับเขา

และชีวิตของเขาจะต้องประจันหน้า

กับ16:12 หรือชีวิตของเขาจะอยู่ทางด้านตะวันออก / ของพี่น้องทั้งปวงของเขา”

13นางเรียกพระนามองค์พระผู้เป็นเจ้าผู้ตรัสกับนางว่า “พระองค์ทรงเป็นพระเจ้าผู้ทอดพระเนตรเห็นข้าพระองค์” และนางพูดว่า “บัดนี้ฉันได้เห็น16:13 หรือได้เห็นข้างหลังของพระองค์ผู้ทรงเห็นฉัน” 14บ่อน้ำนั้นจึงได้ชื่อว่าเบเออร์ลาไฮรอย16:14 แปลว่าบ่อแห่งพระองค์ผู้ทรงพระชนม์อยู่ ผู้ทอดพระเนตรเห็นข้าพระองค์ ตั้งอยู่ระหว่างคาเดชกับเบเรด

15ฮาการ์คลอดบุตรชายคนหนึ่งให้แก่อับราม และอับรามตั้งชื่อบุตรที่นางให้กำเนิดว่าอิชมาเอล 16อับรามอายุ 86 ปีเมื่อฮาการ์ให้กำเนิดอิชมาเอลแก่เขา