ዘፍጥረት 14 – NASV & NSP

New Amharic Standard Version

ዘፍጥረት 14:1-24

አብራም ሎጥን መታደጉ

1አምራፌል የሰናዖር14፥1 በ9 ላይ ያለውንም ጨምሮ ባቢሎንን ያመላክታል። ንጉሥ፣ አርዮክ የእላሳር ንጉሥ፣ ኮሎዶጎምር የኤላም ንጉሥ፣ ቲድዓል የጎይም ንጉሥ በነበሩበት ዘመን፣ 2ከሰዶም ንጉሥ ከበላ፣ ከገሞራ ንጉሥ ከብርሳ፣ ከአዳማ ንጉሥ ከሰነአብ፣ ከሰቦይ ንጉሥ ከሰሜበር፣ እንዲሁም ዞዓር ከተባለች ከቤላ ንጉሥ ጋር ለመዋጋት ወጡ። 3እነዚህ የኋለኞቹ አምስቱ ነገሥታት በሲዲም ሸለቆ፣ በጨው ባሕር14፥3 የሙት ባሕር ማለት ነው። ተሰበሰቡ። 4እነርሱም ዐሥራ ሁለት ዓመት ለኮሎዶጎምር ከተገዙ በኋላ በዐሥራ ሦስተኛው ዓመት ዐመፁ።

5በዐሥራ አራተኛው ዓመት ኮሎዶጎምርና ከርሱ ጋር የተባበሩት ነገሥታት ወጡ፤ ራፋይምን በአስጣሮት ቃርናይም፣ ዙዚምን በሃም፣ ኑሚምን በሴዊ ቂርያታይም፣ 6የሖር ሰዎችንም በተራራማው አገር በሴይር በረሓማ አጠገብ እስካለው እስከ ኤልፋራን ድረስ ድል አደረጓቸው። 7ከዚያም ተመልሰው ዐይን ሚስፖጥ ወደተባለው ወደ ቃዴስ መጡ፤ የአማሌቃውያንና በሐሴስ ታማር ይኖሩ የነበሩትን የአሞራውያንን ግዛት በሙሉ ድል አድርገው ያዙ።

8ከዚያም የሰዶም፣ የገሞራ፣ የአዳማ፣ የሰቦይ እንዲሁም ዞዓር የተባለችው የቤላ ነገሥታት በሲዲም ሸለቆ ሰራዊታቸውን አስተባበሩ። 9እነዚህ አምስቱ፣ በኤላም ንጉሥ በኮሎዶጎምር፣ በጎይም ንጉሥ በቲድዓል፣ በሰናዖር ንጉሥ በአምራፌል፣ በእላሳር ንጉሥ በአርዮክ፣ በእነዚህ በአራቱ ላይ ዘመቱባቸው። 10በሲዲም ሸለቆ ብዙ የቅጥራን ጕድጓዶች ስለ ነበሩ የሰዶምና የገሞራ ነገሥታት ሲሸሹ ከሰዎቻቸው አንዳንዶቹ በእነዚህ ጕድጓዶች ውስጥ ወደቁ፤ የቀሩትም ወደ ተራሮች ሸሹ። 11አራቱ ነገሥታትም በሰዶምና በገሞራ ያገኙትን ሀብትና ምግብ ሁሉ ዘርፈው ሄዱ። 12የአብራም ወንድም ልጅ ሎጥ፣ ሰዶም ይኖር ስለ ነበር እርሱንም ማርከው ንብረቱንም ዘርፈው ሄዱ።

13ከዚህም ያመለጠ አንድ ሰው መጥቶ ለዕብራዊው ለአብራም ይህን ነገረ፤ አብራም በዚያ ጊዜ ይኖር የነበረው በአሞራዊው መምሬ ታላላቅ ዛፎች አጠገብ ነበር። መምሬ፣ ወንድሞቹ14፥13 ወይም ዘመድ፤ ወይም ጓድ አስኮና አውናን የአብራም የኪዳን አጋሮቹ ነበሩ። 14አብራም የወንድሙን ልጅ መማረክ እንደ ሰማ በቤቱ ተወልደው አድገው የሠለጠኑ 318 ጦረኞች አሰልፎ እስከ ዳን ድረስ ገሠገሠ። 15አብራም ጠላቶቹን ለማጥቃት ሰራዊቱን ሌሊቱን በቡድን በቡድን ከፋፍሎ ከደማስቆ በስተ ሰሜን እስከሚገኘው እስከ ሖባ ድረስ አሳደዳቸው። 16አብራም ጠላት የማረከውን በሙሉ አስጣለ፤ የወንድሙን ልጅ ሎጥን፣ ንብረቱን እንዲሁም ሴቶቹንና ሌሎቹን ምርኮኞች አስመለሰ።

17አብራም ኮሎዶጎምርንና አብረውት የተሰለፉትን ነገሥታት ድል አድርጎ ሲመለስ፣ የሰዶም ንጉሥ፣ “የንጉሥ ሸለቆ” ተብሎ በሚጠራው በሴዊ ሸለቆ ሊቀበለው ወጣ።

18የልዑል እግዚአብሔር (ኤል-ኤልዮን) ካህን የነበረው የሳሌም14፥18 ኢየሩሳሌም ናት ንጉሥ መልከጼዴቅም እንጀራና የወይን ጠጅ ይዞ ወጣ፤ 19አብራምንም እንዲህ ሲል ባረከው፤

“ሰማይንና ምድርን የፈጠረ14፥19 ወይም በ22 ላይ ያለውንም ጨምሮ ባለቤት ሊሆን ይችላል። ልዑል

እግዚአብሔር (ኤል-ኤልዮን) አብራምን ይባርክ፤

20ጠላቶችህን አሳልፎ በእጅህ የሰጠህ፣

ልዑል እግዚአብሔር (ኤል-ኤልዮን) ይባረክ።”

አብራምም ካመጣው ሁሉ ዐሥራትን ሰጠው።

21የሰዶም ንጉሥም አብራምን፣ “ሰዎቹን ለእኔ ስጠኝ፤ ንብረቱን ግን ለራስህ አስቀር” አለው።

22አብራም ግን ለሰዶም ንጉሥ እንዲህ አለው፤ “ሰማይንና ምድርን ወደ ፈጠረ ወደ እግዚአብሔር (ያህዌ)፣ ወደ ልዑል አምላክ (ኤል-ኤልዮን) እጆቼን አንሥቻለሁ፤ 23‘አብራምን አበለጸግሁት’ እንዳትል፣ ብጣሽ ክርም ሆነ የጫማ ማሰሪያ እንኳ ከአንተ አንዳች አልፈልግም። 24ሰዎቼ ከበሉትና ከእኔ ጋር ከሄዱት ሰዎች ድርሻ በስተቀር ለራሴ አንዳች ነገር አልቀበልም፤ አውናን፣ ኤስኮልና መምሬ ድርሻቸውን ይውሰዱ።”

New Serbian Translation

1. Мојсијева 14:1-24

Аврам избавља Лота

1У те дане, Амрафел цар Сенара, Ариох цар Еласара, Кедор-Лаомер цар Елама и Тидал цар Гојима, 2поведу рат против Бере, цара содомског, Варсе, цара гоморског, Шинаба, цара Адме, Симовора, цара Севојима и цара Вале, то јест Соара. 3Сви се они скупе у долину Сидим, где је Мртво море14,3 Дословно: Слано море.. 4Дванаест година су били потчињени Кедор-Лаомеру, али тринаесте године се побуне.

5Четрнаесте године дође Кедор-Лаомер с царевима што су му били савезници и потуку Рефаимце у Астарот-Карнајиму, Зузејце у Аму и Емијце на равници киријатајимској, 6те Хоријце на њиховој гори Сир, близу Ел-Фарана, што је покрај пустиње. 7Онда се врате назад и дођу у Ен-Миспат, то јест Кадис, и освоје целу област Амаличана и Аморејаца, који су живели у Хасасон-Тамару.

8Тада се дигне цар Содоме, цар Гоморе, цар Адме, цар Севојима и цар Вале, то јест Соара, па заметну битку против оних у долини Сидим: 9Кедор-Лаомера, цара Елама, Тидала, цара Гојима, Амрафела, цара Сенара, Ариоха, цара Еласара – четири цара против петорице. 10Долина Сидим је била пуна јама са смолом. Цареви Содоме и Гоморе, бежећи, упадну у њих, а остали побегну у горе. 11А победници однесу сва добра Содоме и Гоморе и сву храну, па оду. 12Одвели су и Лота, Аврамовог синовца, који је живео у Содоми, са свим његовим добрима.

13Али неки бегунац дође и све исприча Авраму Јеврејину, док је боравио код храстова Аморејца Мамрије, брата Есхола и Анера, који су били његови савезници. 14Кад је Аврам чуо да му је синовац заробљен, сабере своје људе вичне боју – рођене у његовом дому – њих три стотине осамнаест, па крене у потеру до Дана. 15Онда их је поделио у две групе, па је ноћу напао ону војску и потукао је. Гонио их је све до Хове, северно од Дамаска 16и повратио сав плен. Вратио је и свога синовца, Лота, са његовим добрима, жене и остали свет.

Мелхиседек благосиља Аврама

17Кад се након победе над Кедор-Лаомером и царевима који су били с њим, Аврам вратио у долину Саве, то јест у Царску долину, изађе му у сусрет цар Содоме.

18Тада Мелхиседек, цар Салима, донесе хлеб и вино. Он је био свештеник Бога Свевишњега. 19Он благослови Аврама рекавши:

„Нека Бог Свевишњи,

створитељ неба и земље, благослови Аврама!

20Нека је благословен Бог Свевишњи,

што теби у руке изручи непријатеље твоје!“

Аврам му тада даде десетак од свега.

21А цар содомски рече Авраму: „Мени дај људе, а ти узми добра.“ 22Али Аврам му рече: „Подижем руку пред Господом, Богом Свевишњим, створитељем неба и земље, 23да нећу узети ни кончића с ремена од обуће, нити ишта што ти припада, да не би рекао: ’Ја сам учинио Аврама богатим!’ 24За себе нећу ништа, осим што су моји момци појели. Део плена нека узму људи који су пошли са мном – Анер, Есхол и Мамрије.“