ዘፍጥረት 11 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዘፍጥረት 11:1-32

የባቤል ግንብ

1በዚያን ጊዜ ሰዎች ሁሉ የሚናገሩትና የሚግባቡበት ቋንቋ አንድ ብቻ ነበር። 2ሰዎቹም ምሥራቁን11፥2 ወይም ከምሥራቅ፣ በምሥራቅ ይዘው ሲጓዙ፣ በሰናዖር11፥2 ባቢሎንን ያመላክታል። አንድ ሜዳ አግኝተው በዚያ ሰፈሩ።

3እነርሱም እርስ በርሳቸው፣ “ኑ፤ ጡብ እንሥራ፤ እስኪበቃውም በእሳት እንተኵሰው” ተባባሉ። በድንጋይ ፈንታ ጡብ፣ ለማያያዣም ቅጥራን ተጠቀሙ። 4ከዚያም “ለስማችን መጠሪያ እንዲሆንና በምድር ላይ እንዳንበተን፣ ኑ፤ ከተማ፣ ሰማይ የሚደርስ ግንብም ለራሳችን እንሥራ” አሉ።

5እግዚአብሔር (ያህዌ) ግን ሰዎቹ ይሠሩ የነበሩትን ከተማና ግንብ ለማየት ወረደ። 6እግዚአብሔርም (ያህዌ) እንዲህ አለ፤ “እንዲህ እንደ አንድ ሕዝብ አንድ ቋንቋ በመናገር ይህን ማድረግ ከጀመሩ፣ ከእንግዲህ ያቀዱትን ሁሉ ማከናወን አያዳግታቸውም። 7ኑ እንውረድ፤ እርስ በርሳቸውም እንዳይግባቡ ቋንቋቸውን እንደበላልቀው።”

8ስለዚህ እግዚአብሔር (ያህዌ) በምድር ሁሉ ላይ በታተናቸው፤ ከተማዋንም መሥራት አቆሙ። 9እግዚአብሔር (ያህዌ) በዚያ የመላውን ዓለም ቋንቋ ስለ ደበላለቀ የከተማዪቱ ስም ባቤል11፥9 ባቢሎንን ያመላክታል። ባቤል የሚለው ቃል ድንግርታ የሚል ትርጕም ካለው የዕብራይስጥ ቃል ጋር አንድ ዐይነት ድምፅ አለው። ተባለ። ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) ሰዎቹን በምድር ሁሉ በተናቸው።

ከሴም እስከ አብራም

11፥10-27 ተጓ ምብ – ዘፍ 10፥21-321ዜና 1፥17-27

10የሴም ትውልድ ይህ ነው፦

ሁለት ዓመት ከጥፋት ውሃ በኋላ ሴም በ100 ዓመቱ አርፋክስድን ወለደ። 11ሴም፣ አርፋክስድን ከወለደ በኋላ 500 ዓመት ኖረ፤ ሌሎች ወንዶችና ሴቶች ልጆችን ወለደ።

12አርፋክስድ በ35 ዓመቱ ሳላን ወለደ፤ 13ሳላን ከወለደ በኋላ አርፋክስድ 403 ዓመት ኖረ፤ ሌሎች ወንዶችና ሴቶችን ወለደ።11፥12-13 ከዕብራይስጡ ጋር ተመሳሳይ ሲሆን፣ ሰብዓ ሊቃናት ግን (በተጨማሪ ሉቃ 3፥35-36 እና የዘፍ 10፥24 ማብ ይመ) እንዲሁ ይሉታል፤ 12 በ35 ዓመት ቃይናንን ወለደ፤ 13 ቃይናንን ከወለደ በኋላ፣ አርፋክስድ 430 ዓመት ኖረ፤ ሌሎች ወንዶችና ሴቶች ልጆችን ወለደ፤ ቃይናንም 130 ዓመት ከኖረ በኋላ ሳላን ወለደ፤ ሳላንን ከወለደ በኋላ፣ ቃይናን 330 ዓመት ኖረ፤ ሌሎች ወንዶችና ሴቶች ልጆችን ወለደ ይላል።

14ሳላ በ30 ዓመቱ ዔቦርን ወለደ፤ 15ዔቦርን ከወለደ በኋላ ሳላ 403 ዓመት ኖረ፤ ሌሎች ወንዶችና ሴቶች ልጆችን ወለደ።

16ዔቦር በ34 ዓመቱ ፋሌቅን ወለደ፤ 17ፋሌቅን ከወለደ በኋላ ዔቦር 430 ዓመት ኖረ፤ ሌሎች ወንዶችና ሴቶች ልጆችን ወለደ።

18ፋሌቅ በ30 ዓመቱ ራግውን ወለደ፤ 19ራግውን ከወለደ በኋላ ፋሌቅ 209 ዓመት ኖረ፤ ሌሎች ወንዶችና ሴቶች ልጆችን ወለደ።

20ራግው በ32 ዓመቱ ሴሮሕን ወለደ፤ 21ሴሮሕን ከወለደ በኋላ ራግው 207 ዓመት ኖረ፤ ሌሎች ወንዶችና ሴቶች ልጆችን ወለደ።

22ሴሮሕ በ30 ዓመቱ ናኮርን ወለደ፤ 23ናኮርን ከወለደ በኋላ ሴሮሕ 200 ዓመት ኖረ፤ ሌሎች ወንዶችና ሴቶች ልጆችን ወለደ።

24ናኮር በ29 ዓመቱ ታራን ወለደ፤ 25ታራን ከወለደ በኋላ ናኮር 119 ዓመት ኖረ፤ ሌሎች ወንዶችና ሴቶች ልጆችን ወለደ።

26ታራ 70 ዓመት ከሆነው በኋላ አብራምን፣ ናኮርንና ሐራንን ወለደ።

27የታራ ትውልድ ይህ ነው፦

ታራ፣ አብራምን ናኮርንና ሐራንን ወለደ፤

ሐራንም ሎጥን ወለደ። 28ሐራን፣ አባቱ ታራ ገና በሕይወት እንዳለ በከለዳውያን ምድር በምትገኘው በተወለደባት ከተማ በዑር ሞተ። 29አብራምና ናኮር ሁለቱም ሚስት አገቡ፤ የአብራም ሚስት ሦራ ስትባል፣ የናኮር ሚስት ደግሞ ሚልካ ትባል ነበር፤ ሚልካም የሐራን ልጅ ናት፤ ሐራንም የሚልካና የዮስካ አባት ነበረ። 30ሦራ መካን ነበረች፤ ልጅ አልነበራትም።

31ታራ ልጁን አብራምን፣ ሐራን የወለደውን የልጅ ልጁን ሎጥን እንዲሁም የአብራምን ሚስት ምራቱን ሦራን ይዞ ወደ ከነዓን ለመሄድ በከለዳውያን ምድር ከምትገኘው ከዑር አብረው ወጡ፤ ነገር ግን ካራን በደረሱ ጊዜ በዚያ ተቀመጡ።

32ታራ 205 ዓመት ኖሮ በካራን ሞተ።

Thai New Contemporary Bible

ปฐมกาล 11:1-32

หอบาเบล

1ครั้งนั้นทั้งโลกใช้ภาษาเดียวกัน ใช้ถ้อยคำเหมือนกัน 2เมื่อมนุษย์ย้ายถิ่นฐานไปทางทิศตะวันออก11:2 หรือจากทิศตะวันออกหรือในทิศตะวันออก พวกเขาพบที่ราบในดินแดนชินาร์11:2 คือ บาบิโลน จึงตั้งหลักแหล่งอยู่ที่นั่น

3พวกเขาพูดกันว่า “มาเถิด ให้เราทำอิฐและเผาจนสุก” พวกเขาใช้อิฐแทนหินและใช้ยางมะตอยแทนปูน 4แล้วพวกเขาพูดว่า “มาเถิด ให้เราสร้างเมืองที่มีหอสูงขึ้นถึงฟ้าสำหรับพวกเรา เพื่อเราจะได้สร้างชื่อให้กับตนเองและไม่ต้องกระจายไปทั่วทั้งโลก”

5แต่องค์พระผู้เป็นเจ้าเสด็จลงมาเพื่อทอดพระเนตรเมืองและหอคอยซึ่งพวกเขากำลังสร้าง 6องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่า “คนเหล่านี้เป็นชนชาติเดียวกัน พูดภาษาเดียวกัน ยังริเริ่มทำงานได้ถึงเพียงนี้ ต่อไปถ้าเขาวางแผนจะทำอะไรก็จะทำได้ทุกอย่าง 7มาเถิด ให้เราลงไปทำให้เขามีภาษาสับสนแตกต่างกันออกไป เพื่อเขาจะได้ไม่เข้าใจกัน”

8ดังนั้นองค์พระผู้เป็นเจ้าจึงทรงทำให้พวกเขากระจัดกระจายจากที่นั่นออกไปทั่วทั้งโลก และพวกเขาก็หยุดสร้างเมืองนั้น 9ด้วยเหตุนี้เมืองนั้นจึงได้ชื่อว่าบาเบล11:9 คือ บาบิโลน คำว่าบาเบลมีเสียงคล้ายคำภาษาฮีบรูที่มีความหมายว่าสับสน เพราะที่นั่นเป็นที่ที่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงกระทำให้ภาษาของโลกสับสนแตกต่างกันออกไป องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงทำให้พวกเขากระจัดกระจายไปอาศัยอยู่ทั่วทั้งโลก

จากเชมถึงอับราม

(ปฐก.10:21-31; 1พศด.1:17-27)

10นี่คือเรื่องราวเชื้อสายของเชม

สองปีหลังจากน้ำท่วม เมื่อเชมอายุได้ 100 ปีก็มีบุตรชาย11:10 ภาษาเดิมว่าได้เป็นบิดาของซึ่งคำว่าบิดาอาจจะมีความหมายว่าบรรพบุรุษเช่นเดียวกับข้อ 11-25ชื่ออารปัคชาด 11หลังจากนั้นเชมมีชีวิตต่อไปอีก 500 ปี และมีบุตรชายหญิงอีกหลายคน

12เมื่ออารปัคชาดอายุได้ 35 ปีก็มีบุตรชายชื่อเชลาห์ 13หลังจากนั้นเขามีชีวิตต่อไปอีก 403 ปี และมีบุตรชายหญิงอีกหลายคน11:13 ฉบับ LXX. ว่า35 ปี เขามีบุตรชื่อไคนัน 13หลังจากนั้นเขามีอายุต่อไปอีก 430 ปี มีบุตรชายหญิงอีกหลายคน แล้วเขาก็ตาย เมื่อไคนันมีอายุได้ 130 ปีเขามีบุตรชื่อเชลาห์ หลังจากนั้นเขามีชีวิตต่อไปอีก 330 ปี และมีบุตรชายหญิงอีกหลายคน (ดูลก.3:35-36 และเชิงอรรถของปฐก.10:24)

14เมื่อเชลาห์อายุได้ 30 ปีก็มีบุตรชายชื่อเอเบอร์ 15หลังจากนั้นเขามีชีวิตต่อไปอีก 403 ปี และมีบุตรชายหญิงอีกหลายคน

16เมื่อเอเบอร์อายุได้ 34 ปีก็มีบุตรชายชื่อเปเลก 17หลังจากนั้นเขามีชีวิตต่อไปอีก 430 ปี และมีบุตรชายหญิงอีกหลายคน

18เมื่อเปเลกอายุได้ 30 ปีก็มีบุตรชายชื่อเรอู 19หลังจากนั้นเขามีชีวิตต่อไปอีก 209 ปี และมีบุตรชายหญิงอีกหลายคน

20เมื่อเรอูอายุได้ 32 ปีก็มีบุตรชายชื่อเสรุก 21หลังจากนั้นเขามีชีวิตต่อไปอีก 207 ปี และมีบุตรชายหญิงอีกหลายคน

22เมื่อเสรุกอายุได้ 30 ปีก็มีบุตรชายชื่อนาโฮร์ 23หลังจากนั้นเขามีชีวิตต่อไปอีก 200 ปี และมีบุตรชายหญิงอีกหลายคน

24เมื่อนาโฮร์อายุได้ 29 ปีก็มีบุตรชายชื่อเทราห์ 25หลังจากนั้นเขามีชีวิตต่อไปอีก 119 ปี และมีบุตรชายหญิงอีกหลายคน

26หลังจากที่เทราห์อายุ 70 ปี เขาก็มีบุตรชายชื่ออับราม นาโฮร์ และฮาราน

27นี่คือเรื่องราวเชื้อสายของเทราห์

เทราห์มีบุตรชายชื่ออับราม นาโฮร์ และฮาราน ฮารานมีบุตรชายชื่อโลท 28ขณะที่เทราห์บิดาของเขายังมีชีวิตอยู่ ฮารานได้สิ้นชีวิตลงที่เมืองเออร์ของชาวเคลเดียซึ่งเป็นบ้านเกิดของเขา 29ทั้งอับรามและนาโฮร์แต่งงานมีครอบครัว ภรรยาของอับรามชื่อซาราย ภรรยาของนาโฮร์ชื่อมิลคาห์ ซึ่งเป็นบุตรีของฮารานผู้เป็นบิดาของทั้งมิลคาห์และอิสคาห์ 30นางซารายนั้นไม่มีบุตรเพราะเป็นหมัน

31เทราห์พาบุตรชายชื่ออับราม หลานชายชื่อโลทซึ่งเป็นบุตรชายของฮาราน และบุตรสะใภ้ชื่อซาราย ซึ่งเป็นภรรยาของอับรามบุตรชายของเขา ออกจากเมืองเออร์ของชาวเคลเดียเพื่อไปคานาอัน แต่เมื่อมาถึงเมืองฮารานก็ตั้งถิ่นฐานที่นั่น

32เทราห์มีชีวิตอยู่ 205 ปี แล้วเขาก็ตายที่เมืองฮาราน