ዘፀአት 40 – NASV & KLB

New Amharic Standard Version

ዘፀአት 40:1-38

የማደሪያውን ድንኳን መትከል

1ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን አለው፤ 2“ማደሪያውን ይኸውም የመገናኛውን ድንኳን በወሩ የመጀመሪያ ቀን ትከለው፤ 3የምስክሩን ታቦት በውስጡ አኑር፤ ታቦቱንም በመጋረጃው ጋርደው። 4ጠረጴዛውንም ወደ ውስጥ አምጥተህ ዕቃዎቹን በላዩ ላይ አሰናዳ፤ ከዚያም መቅረዙን አስገብተህ መብራቶቹን በቦታቸው አስቀምጥ። 5የዕጣኑን የወርቅ መሠዊያ በምስክሩ ታቦት ፊት ለፊት አስቀምጠው፤ ከማደሪያውም መግቢያ ላይ መጋረጃውን አድርግ።

6“የሚቃጠል መሥዋዕት መሠዊያውን በማደሪያው መግቢያ ፊት ለፊት፣ በመገናኛው ድንኳን አስቀምጠው። 7የመታጠቢያውን ሰን በመገናኛው ድንኳንና በመሠዊያው መካከል አኑርበት፤ ውሃም አኑርበት። 8በዙሪያውም የአደባባዩን ቅጥር ትከል፤ መጋረጃውንም በአደባባዩ መግቢያ ላይ አድርገው።

9“ቅብዐ ዘይቱን ወስደህ ማደሪያውንና በውስጡ ያለውን ሁሉ ቅባ፤ እርሱንና ዕቃውን ሁሉ ቀድስ፤ የተቀደሰም ይሆናል። 10ከዚያም የሚቃጠል መሥዋዕት መሠዊያውንና ዕቃዎቹን ሁሉ ቅባ፤ መሠዊያውን ቀድስ፣ እጅግም የተቀደሰ ይሆናል። 11የመታጠቢያው ሰንና ማስቀመጫውን ቅባ፤ ቀድሳቸውም።

12“አሮንና ወንዶች ልጆቹን ወደ መገናኛው ድንኳን መግቢያ አምጥተህ በውሃ ዕጠባቸው። 13ከዚያም አሮንን የተቀደሰውን ልብስ አልብሰው፤ ካህን ሆኖ ያገለግለኝ ዘንድ ቅባው፤ ቀድሰውም። 14ወንዶች ልጆቹን አምጥተህ ሸሚዝ አልብሳቸው። 15ካህናት ሆነው ያገለግሉኝ ዘንድ ልክ አባታቸውን እንደ ቀባህ ቅባቸው፤ መቀባታቸውም በሚመጡት ትውልዶች ሁሉ ለሚቀጥል ክህነት ነው።” 16ሙሴ ሁሉንም ነገር ልክ እግዚአብሔር (ያህዌ) እንዳዘዘው አደረገ።

17እንዲሁም በሁለተኛው ዓመት፣ የመጀመሪያው ወር በገባ በመጀመሪያው ቀን የማደሪያው ድንኳን ተተከለ። 18ሙሴ የማደሪያውን ድንኳን በተከለ ጊዜ፣ መቆሚያዎቹን በቦታቸው አኖረ፤ ወጋግራዎቹን አቆመ፤ አግዳሚዎቹን አስገባ፤ ምሰሶዎቹንም ተከለ። 19ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) እንዳዘዘው ድንኳኑን በማደሪያው ላይ፣ መደረቢያውንም በድንኳኑ ላይ ዘረጋው።

20ምስክሩን ወስዶ በታቦቱ ውስጥ አስቀመጠው፤ መሎጊያዎቹንም ከታቦቱ ጋር አያያዛቸው፤ የስርየት መክደኛውንም በላዩ ላይ አደረገው። 21ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) እንዳዘዘው ታቦቱን ወደ ማደሪያው ድንኳን አስገብቶ መከለያ መጋረጃውን ሰቀለ፤ የምስክሩንም ታቦት ጋረደው።

22ሙሴ ጠረጴዛውን በመገናኛው ድንኳን ውስጥ፣ ከማደሪያው በስተ ሰሜን ከመጋረጃው ውጭ አኖረው፤ 23እግዚአብሔር (ያህዌ) እንዳዘዘውም ኅብስቱን በላዩ ላይ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት አኖረ።

24መቅረዙን በመገናኛው ድንኳን ውስጥ ከጠረጴዛው ትይዩ ከማደሪያው ድንኳን በስተ ደቡብ በኩል አኖረው፤ 25እግዚአብሔር (ያህዌ) እንዳዘዘውም መብራቶቹን በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት አበራ።

26ሙሴ የወርቅ መሠዊያውን በመገናኛው ድንኳን ውስጥ ከመጋረጃው ፊት ለፊት አኖረው፤ 27እግዚአብሔር (ያህዌ) እንዳዘዘውም መልካም መዐዛ ያለውን ዕጣን አጠነበት። 28ከዚያም መጋረጃውን በማደሪያው ድንኳን መግቢያ ላይ ሰቀለው።

29የሚቃጠል መሥዋዕት መሠዊያውንም በማደሪያው፣ በመገናኛው ድንኳን መግቢያ ላይ አኖረው፤ እግዚአብሔር (ያህዌ) እንዳዘዘውም የሚቃጠለውን መሥዋዕትና የእህሉን መሥዋዕት በላዩ ላይ አቀረበ።

30የመታጠቢያውን ሰን በመገናኛው ድንኳንና በመሠዊያው መካከል አስቀመጠ፤ ለመታጠቢያም ውሃ አደረገበት፤ 31ሙሴና አሮን፣ ወንዶች ልጆቹም እጆቻቸውንና እግሮቻቸውን ይታጠቡበት ነበር። 32እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዳዘዘው ወደ መገናኛው ድንኳን በገቡና ወደ መሠዊያው በቀረቡ ቍጥር ይታጠቡ ነበር።

33ከዚያም ሙሴ በማደሪያውና በመሠዊያው ዙሪያ አደባባዩን ተከለ፤ በአደባባዩም መግቢያ ላይ መጋረጃውን ሰቀለ፤ እንደዚህ አድርጎ ሙሴ ሥራውን ፈጸመ።

የእግዚአብሔር ክብር

34ከዚያም ደመናው የመገናኛውን ድንኳን ሸፈነ፤ የእግዚአብሔርም (ያህዌ) ክብር ማደሪያውን ሞላ። 35ደመናው በላዩ ላይ ስለ ነበረና የእግዚአብሔርም (ያህዌ) ክብር ማደሪያውን ስለ ሞላው፣ ሙሴ ወደ መገናኛው ድንኳን መግባት አልቻለም።

36በእስራኤላውያን ጕዞ ሁሉ ደመናው ከማደሪያው ላይ በተነሣ ጊዜ፣ ይጓዙ ነበር፤ 37ደመናው ካልተነሣ ግን፣ እስከሚነሣበት ቀን ድረስ አይጓዙም ነበር። 38ስለዚህ በጕዟቸው ሁሉ ወቅት፣ በእስራኤል ቤት ፊት ሁሉ የእግዚአብሔር (ያህዌ) ደመና በቀን ከማደሪያው በላይ፣ በሌሊትም እሳቱ በደመናው ውስጥ ነበር።

Korean Living Bible

출애굽기 40:1-38

성막을 세움

1여호와께서 모세에게 말씀하셨다.

2“너는 정월 초하룻날에 성막을 세우고

3그 안에 법궤를 들여놓은 다음 휘장을 쳐서 그 궤를 가려라.

4그리고 상을 들여놓고 그 위에 얹을 것을 차려 놓고 또 등대를 들여놓아 불을 켜고

5향단을 법궤 앞에 놓고 성막 출입구 휘장을 달아라.

6“너는 제물을 태워 바칠 번제단을 성막 출입구 앞에 놓고

7넓적한 물통을 성막과 번제단 사이에 놓은 후 그 속에 물을 채워라.

8그런 다음 포장을 쳐서 뜰을 만들고 뜰 출입구 막을 달아라.

9“그리고 너는 거룩한 기름을 가져다가 성막과 그 안에 있는 모든 것에 발라 성막과 그 모든 기구를 신성하게 하라. 그러면 그것이 거룩해질 것이다.

10너는 또 그 기름을 번제단과 그 모든 기구에 발라 그 제단을 신성하게 하라. 그 단이 아주 거룩해질 것이다.

11그리고 넓적한 물통과 그 받침에도 기름을 발라 그것들을 거룩하게 하라.

12“너는 또 아론과 그의 아들들을 성막 입구로 데려다가 그들을 물로 씻긴 다음

13아론에게 거룩한 옷을 입히고 그에게 기름을 붓고 거룩하게 하여 제사장으로서 나를 섬기게 하라.

14그리고 너는 그의 아들들에게 속옷을 입히고

15또 아론에게 기름을 부은 것처럼 그들에게도 기름을 부어 제사장으로서 나를 섬기게 하라. 그들이 기름 부음을 받음으로써 그들의 제사장직은 영구히 계승되어 그 후손들이 대대로 제사장이 될 것이다.”

16그래서 모세는 모든 일을 여호와께서 자기에게 명령하신 대로 하였는데

17그들이 이집트를 떠나온 지 2년째가 되는 해 정월 초하룻날에 성막이 세워졌다.

18모세는 성막을 세울 때 받침들을 놓고 널빤지를 세웠으며 그 가로대를 끼우고 또 기둥을 세웠다.

19그런 다음 그는 성막 위에 막을 펴고 그 위에 덮개를 덮어 여호와께서 자기에게 명령하신 대로 하였다.

20그는 또 십계명이 기록된 두 돌판을 궤 속에 넣고 운반채를 궤의 고리에 꿰고 그 궤의 뚜껑인 속죄소를 궤 위에 얹었다.

21그러고서 그는 궤를 성막 안에 들여놓고 여호와께서 자기에게 명령하신 대로 휘장을 쳐서 그 40:21 또는 ‘증거궤’법궤를 가렸다.

22모세는 또 성막의 그 휘장 밖에 북쪽으로 상을 놓고

23여호와께서 자기에게 명령하신 대로 여호와께 바친 빵을 그 상 위에 차려 놓았다.

24그리고 그는 성막 안의 남쪽인 상 맞은편에 등대를 놓고

25여호와 앞에서 등잔에 불을 켜 여호와께서 명령하신 대로 하였다.

26그는 또 향단을 성막 안의 휘장 앞에 두고

27그 위에 향을 피워 여호와께서 명령하신 대로 하였다.

28그리고 그는 성막 입구에 휘장을 달고

29성막 출입구 앞에 제물을 태워 바칠 번제단을 놓았으며 그 위에 짐승을 불에 태워 바치는 번제와 곡식으로 드리는 소제를 드려 여호와께서 자기에게 말씀하신 대로 하였다.

30그는 또 물통을 성막과 제단 사이에 두고 거기에 물을 채웠으며

31모세와 아론과 그의 아들들은 그 물로

32성막에 들어갈 때나 단에 가까이 갈 때 손발을 씻어 여호와께서 모세에게 명령하신 대로 하였다.

33그리고 모세는 성막과 제단 주위에 포장을 쳐서 뜰을 만들고 뜰의 출입구 막을 달아 모든 일을 끝마쳤다.

여호와의 영광

34그러자 구름이 성막에 덮이고 여호와의 영광의 광채가 성막을 가득 채웠다.

35모세는 성막 위에 덮인 그 구름과 성막 안에 가득한 그 영광의 광채 때문에 성막에 들어갈 수가 없었다.

36이스라엘 백성은 구름이 성막 위에서 떠오를 때마다 계속 행진하였으나

37구름이 떠오르지 않을 때에는 그 구름이 떠오를 때까지 떠나지 않았다.

38이와 같이 이스라엘 백성이 다 보는 가운데 낮에는 여호와의 구름이 성막 위에 있고 밤에는 구름 가운데 불이 있었다. 이것은 그들이 길을 가는 동안 줄곧 계속되었다.