ዘፀአት 37 – NASV & PCB

New Amharic Standard Version

ዘፀአት 37:1-29

የኪዳኑ ታቦት

37፥1-9 ተጓ ምብ – ዘፀ 25፥10-20

1ባስልኤል ርዝመቱ ሁለት ክንድ ተኩል፣ ወርዱ አንድ ክንድ ተኩል37፥1 ከፍታው 1.1 ሜትር ወርዱና ርዝመቱ 0.7 ሜትር ያህል ማለት ነው።፣ ከፍታው አንድ ክንድ ተኩል የሆነ ታቦት ከግራር ዕንጨት ሠራ። 2በውስጥና በውጭ በንጹሕ ወርቅ ለበጠው፤ በዙሪያውም የወርቅ ክፈፍ አበጀለት። 3አራት የወርቅ ቀለበቶችን ሠርቶ ሁለት ቀለበቶችን በአንድ በኩል፣ ሁለት ቀለበቶችንም በሌላ በኩል አድርጎ ከአራቱ እግሮቹ ጋር አያያዛቸው። 4ከዚያም መሎጊያዎችን ከግራር ዕንጨት ሠርቶ በወርቅ ለበጣቸው። 5መሎጊያዎቹንም መሸከሚያ እንዲሆኑ በታቦቱ ጐንና ጐን ባሉት ቀለበቶች ውስጥ አስገባቸው።

6ርዝመቱ ሁለት ክንድ ተኩል37፥6 ርዝመቱ 1.1 ሜትር ወርዱ 1.1 ሜትር ያህል ማለት ነው።፣ ወርዱም አንድ ክንድ ተኩል የሆነ ከንጹሕ ወርቅ የስርየት መክደኛ ሠራ። 7ከዚያም ከተቀጠቀጠ ወርቅ ሁለት ኪሩቤልን ከመክደኛው ጫፎች ላይ ሠራ። 8አንዱን ኪሩብ በአንዱ ጫፍ ላይ፣ ሁለተኛውንም ኪሩብ በሌላው ጫፍ ላይ ሠራ፤ ከሁለቱ ጫፎች ላይ ከክዳኑ ጋር አንድ ወጥ አድርጎ ሠራቸው፤ 9ኪሩቤልም የስርየት ክዳኑን በመሸፈን ክንፋቸውን ወደ ላይ ዘርግተው ነበር፤ ኪሩቤል ወደ ስርየት መክደኛው እየተመለከቱ እርስ በርሳቸው ገጽ ለገጽ ነበሩ።

የኅብስት ማስቀመጫው ጠረጴዛ

37፥10-16 ተጓ ምብ – ዘፀ 25፥23-29

10ርዝመቱ ሁለት ክንድ፣ ወርዱ አንድ ክንድ፣ ከፍታውም አንድ ክንድ ተኩል የሆነ ጠረጴዛ ከግራር ዕንጨት ሠሩ37፥10 በዚህና በቍጥር 11-29 ባሉት ክፍሎች፣ ሥሩ11ከዚያም በንጹሕ ወርቅ በመለበጥ በዙሪያው የወርቅ ክፈፍ አበጁለት። 12በዙሪያውም ስፋቱ አንድ ስንዝር37፥12 ወደ 8 ሳንቲ ሜትር ያህል ማለት ነው። የሆነ ጠርዝ በማበጀት በጠርዙ ላይ የወርቅ ክፈፍ አደረጉበት። 13ለጠረጴዛው አራት የወርቅ ቀለበቶች አበጅተው አራቱ እግሮች ካሉበት ከአራቱ ማእዘኖች ጋር አያያዟቸው። 14ጠረጴዛውን ለመሸከም የሚያገለግሉትን መሎጊያዎች እንዲይዙ ቀለበቶቹ ከጠርዙ አጠገብ ሆኑ። 15ጠረጴዛውን ለመሸከም የሚያገለግሉት መሎጊያዎች ከግራር ዕንጨት የተሠሩና በወርቅ የተለበጡ ነበሩ። 16የጠረጴዛውን ዕቃዎች ይኸውም ዝርግ ሳሕኖችን፣ ድስቶችንና ጐድጓዳ ሳሕኖችን እንዲሁም የመጠጥ መሥዋዕቱ ማፍሰሻ የሆኑትን ማንቈርቈሪያዎች ከንጹሕ ወርቅ ሠሯቸው።

መቅረዙ

37፥17-24 ተጓ ምብ – ዘፀ 25፥31-39

17መቅረዙን ከንጹሕ ወርቅ ሠሩት፤ መቆሚያውንና ዘንጉን ቀጥቅጠው አበጁት፤ የአበባ ቅርጽ ያላቸው ጽዋዎች፣ እንቡጦችና የፈኩ አበቦች ከእርሱ ጋር አንድ ወጥ ሆነው ተሠርተው ነበር። 18ሦስቱ በአንድ በኩል ሦስቱ በሌላ በኩል በመሆን ስድስት ቅርንጫፎች ከመቅረዙ ጐኖች ተሠርተው ነበር። 19ከእንቡጦችና ከፈኩ አበቦች ጋር የለውዝ አበባ የሚመስሉ ሦስት ጽዋዎች በአንዱ ቅርንጫፍ ላይ፣ ሦስቱ ደግሞ በሚቀጥለው ቅርንጫፍ ላይ ነበሩ፤ ከመቅረዙ ለወጡት ለስድስቱም ቅርንጫፎች ሁሉ እንዲሁ ነበር። 20እንቡጦችና የፈኩ አበቦች ያሉባቸው የለውዝ አበባ የሚመስሉ አራት ጽዋዎች በመቅረዙ ላይ ነበሩ። 21አንደኛው እንቡጥ ከመቅረዙ ወጣ ብለው በሚገኙት በመጀመሪያው ጥንድ ቅርንጫፎች ሥር፣ ሁለተኛውም እምቡጥ በሁለተኛው ጥንድ ሥር እንዲሁም ሦስተኛው እንቡጥ በሦስተኛው ጥንድ ሥር ነበር፤ በስድስቱም ቅርንጫፎች እንዲሁ ነበር። 22እንቡጦቹና ቅርንጫፎቹ ሁሉ ከንጹሕ ወርቅ ተሠርተው ከመቅረዙ ጋር አንድ ወጥ ነበሩ።

23የመቅረዙን ሰባት መብራቶች፣ እንዲሁም መኰስተሪያዎችንና የኵስታሪ ማስቀመጫዎችን ከንጹሕ ወርቅ ሠሩ። 24መቅረዙንና ዕቃዎቹን ሁሉ ከአንድ መክሊት37፥24 ወደ 34 ኪሎ ግራም ያህል ማለት ነው። ንጹሕ ወርቅ ሠሩ።

የዕጣን መሠዊያው

37፥25-28 ተጓ ምብ – ዘፀ 30፥1-5

25የዕጣን መሠዊያውን ከግራር ዕንጨት ሠሩ፤ ርዝመቱ አንድ ክንድ፣ ወርዱ አንድ ክንድ፣ ከፍታው ሁለት ክንድ37፥25 ርዝመቱ ወርዱ 0.5 ሜትር ከፍታው 0.9 ሜትር ያህል ማለት ነው። ነበር፤ ቀንዶቹም ከእርሱ ጋር አንድ ወጥ ሆነው ተሠርተው ነበር። 26ላዩን፣ ጐኖቹን ሁሉና ቀንዶቹን በንጹሕ ወርቅ ለበጧቸው፤ በዙሪያው የወርቅ ክፈፍ አበጁ። 27ለሸክም የሚሆኑትን መሎጊያዎች ለመያዝ ትይዩ የሆኑ ከክፈፉ ሥር ሁለት የወርቅ ቀለበቶችን ሠሩ። 28መሎጊያዎቹን ከግራር ዕንጨት ሠሩ፤ በወርቅም ለበጧቸው።

29እንዲሁም የተቀደሰውን ቅብዐ ዘይትና የሽቶ ቀማሚ ሥራ የሆነውን፣ ንጹሕና መልካም መዐዛ ያለውን ዕጣን ሠሩ።

Persian Contemporary Bible

خروج 37:1-29

ساختن صندوق عهد

(خروج 25‏:10‏-22)

1بصل‌ئيل، صندوق عهد را از چوب اقاقيا كه درازای آن يک متر و ۲۵ سانتی متر و پهنا و بلندی آن هر كدام هفتاد و پنج سانتی متر بود، ساخت. 2بيرون و درون آن را با طلای خالص پوشانيد و نواری از طلا دور لبهٔ آن كشيد. 3برای صندوق چهار حلقه از طلا آماده كرد و آنها را در چهار گوشهٔ قسمت پايين آن متصل نمود، يعنی در هر طرف دو حلقه. 4‏-5بعد دو چوب بلند تهيه شده از درخت اقاقيا با روكش طلا برای برداشتن صندوق فراهم ساخت و چوبها را در داخل حلقه‌های دو طرف صندوق گذاشت.

6سرپوش صندوق يعنی تخت رحمت را به درازای يک متر و ده سانتيمتر و پهنای هفتاد سانتيمتر، از طلای خالص درست كرد. 7‏-8سپس دو مجسمهٔ فرشته از طلا در دو سر تخت رحمت ساخت. فرشته‌ها را طوری روی تخت رحمت ساخت كه با آن يكپارچه شد. 9مجسمهٔ فرشته‌ها، روبروی هم و نگاهشان به طرف تخت و بالهايشان بر بالای آن گسترده بود.

ساختن ميز نان مقدس

(خروج 25‏:23‏-30)

10آنگاه بصل‌ئيل، ميز نان مقدس را از چوب اقاقيا به درازای يک متر و پهنای نيم متر و بلندی ۷۵ سانتی متر ساخت. 11آن را با روكشی از طلای خالص پوشانيد و قابی از طلا بر دور تا دور لبهٔ آن نصب كرد. 12حاشيهٔ دور لبهٔ ميز را به پهنای چهار انگشت درست كرد و دور حاشيه را با قاب طلا پوشانيد. 13‏-14چهار حلقه از طلا برای ميز ساخت و حلقه‌ها را به چهار گوشهٔ بالای پايه‌های ميز نصب كرد. اين حلقه‌ها برای چوبهايی بود كه به هنگام برداشتن و جابه‌جا كردن ميز می‌بايست در آنها قرار گيرد. 15اين چوبها را از درخت اقاقيا با روكش طلا ساخت. 16همچنين بشقابها، كاسه‌ها، جامها و پياله‌هايی از طلای خالص برای ريختن هدايای نوشيدنی درست كرد تا آنها را روی ميز بگذارند.

ساختن چراغدان

(خروج 25‏:31‏-40)

17چراغدان را نيز از طلای خالص درست كرد. پايه و بدنهٔ آن را يكپارچه و از طلای خالص ساخت و نقش گلهای روی آن را نيز كه شامل كاسبرگ و غنچه بود از طلا درست كرد. 18بر بدنهٔ چراغدان شش شاخه قرار داشت، يعنی در هر طرف سه شاخه. 19روی هر يک از شاخه‌ها سه گل بادامی شكل بود. 20‏-21خود بدنه را با چهار گل بادامی شكل تزيين كرد طوری كه گلها بين شاخه‌ها و بالا و پايين آنها قرار گرفتند. 22تمام اين نقشها و شاخه‌ها و بدنه از يک تكه طلای خالص بود. 23هفت چراغ آن و انبرها و سينی‌هايش را از طلای خالص ساخت. 24برای ساختن اين چراغدان و لوازمش سی و چهار كيلو طلا به کار رفت.

ساختن قربانگاه بخور

(خروج 30‏:1‏-5)

25قربانگاه بخور را به شكل چهارگوش به ضلع نيم متر و بلندی يک متر از چوب اقاقيا درست كرد. آن را طوری ساخت كه در چهار گوشهٔ آن چهار زائده به شكل شاخ بود. 26روكش قربانگاه و شاخهای آن از طلای خالص بود. قابی دور تا دور آن از طلا درست كرد. 27در دو طرف قربانگاه، زير قاب طلايی، دو حلقه از طلا برای قرار گرفتن چوبها ساخت تا با آنها قربانگاه را حمل كنند. 28اين چوبها از درخت اقاقيا تهيه شده بود و روكش طلا داشت.

تهيهٔ روغن مسح و بخور

(خروج 30‏:22‏-38)

29سپس روغن مسح مقدس و بخور خالص معطر را تهيه كرد.