ዘፀአት 37 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ዘፀአት 37:1-29

የኪዳኑ ታቦት

37፥1-9 ተጓ ምብ – ዘፀ 25፥10-20

1ባስልኤል ርዝመቱ ሁለት ክንድ ተኩል፣ ወርዱ አንድ ክንድ ተኩል37፥1 ከፍታው 1.1 ሜትር ወርዱና ርዝመቱ 0.7 ሜትር ያህል ማለት ነው።፣ ከፍታው አንድ ክንድ ተኩል የሆነ ታቦት ከግራር ዕንጨት ሠራ። 2በውስጥና በውጭ በንጹሕ ወርቅ ለበጠው፤ በዙሪያውም የወርቅ ክፈፍ አበጀለት። 3አራት የወርቅ ቀለበቶችን ሠርቶ ሁለት ቀለበቶችን በአንድ በኩል፣ ሁለት ቀለበቶችንም በሌላ በኩል አድርጎ ከአራቱ እግሮቹ ጋር አያያዛቸው። 4ከዚያም መሎጊያዎችን ከግራር ዕንጨት ሠርቶ በወርቅ ለበጣቸው። 5መሎጊያዎቹንም መሸከሚያ እንዲሆኑ በታቦቱ ጐንና ጐን ባሉት ቀለበቶች ውስጥ አስገባቸው።

6ርዝመቱ ሁለት ክንድ ተኩል37፥6 ርዝመቱ 1.1 ሜትር ወርዱ 1.1 ሜትር ያህል ማለት ነው።፣ ወርዱም አንድ ክንድ ተኩል የሆነ ከንጹሕ ወርቅ የስርየት መክደኛ ሠራ። 7ከዚያም ከተቀጠቀጠ ወርቅ ሁለት ኪሩቤልን ከመክደኛው ጫፎች ላይ ሠራ። 8አንዱን ኪሩብ በአንዱ ጫፍ ላይ፣ ሁለተኛውንም ኪሩብ በሌላው ጫፍ ላይ ሠራ፤ ከሁለቱ ጫፎች ላይ ከክዳኑ ጋር አንድ ወጥ አድርጎ ሠራቸው፤ 9ኪሩቤልም የስርየት ክዳኑን በመሸፈን ክንፋቸውን ወደ ላይ ዘርግተው ነበር፤ ኪሩቤል ወደ ስርየት መክደኛው እየተመለከቱ እርስ በርሳቸው ገጽ ለገጽ ነበሩ።

የኅብስት ማስቀመጫው ጠረጴዛ

37፥10-16 ተጓ ምብ – ዘፀ 25፥23-29

10ርዝመቱ ሁለት ክንድ፣ ወርዱ አንድ ክንድ፣ ከፍታውም አንድ ክንድ ተኩል የሆነ ጠረጴዛ ከግራር ዕንጨት ሠሩ37፥10 በዚህና በቍጥር 11-29 ባሉት ክፍሎች፣ ሥሩ11ከዚያም በንጹሕ ወርቅ በመለበጥ በዙሪያው የወርቅ ክፈፍ አበጁለት። 12በዙሪያውም ስፋቱ አንድ ስንዝር37፥12 ወደ 8 ሳንቲ ሜትር ያህል ማለት ነው። የሆነ ጠርዝ በማበጀት በጠርዙ ላይ የወርቅ ክፈፍ አደረጉበት። 13ለጠረጴዛው አራት የወርቅ ቀለበቶች አበጅተው አራቱ እግሮች ካሉበት ከአራቱ ማእዘኖች ጋር አያያዟቸው። 14ጠረጴዛውን ለመሸከም የሚያገለግሉትን መሎጊያዎች እንዲይዙ ቀለበቶቹ ከጠርዙ አጠገብ ሆኑ። 15ጠረጴዛውን ለመሸከም የሚያገለግሉት መሎጊያዎች ከግራር ዕንጨት የተሠሩና በወርቅ የተለበጡ ነበሩ። 16የጠረጴዛውን ዕቃዎች ይኸውም ዝርግ ሳሕኖችን፣ ድስቶችንና ጐድጓዳ ሳሕኖችን እንዲሁም የመጠጥ መሥዋዕቱ ማፍሰሻ የሆኑትን ማንቈርቈሪያዎች ከንጹሕ ወርቅ ሠሯቸው።

መቅረዙ

37፥17-24 ተጓ ምብ – ዘፀ 25፥31-39

17መቅረዙን ከንጹሕ ወርቅ ሠሩት፤ መቆሚያውንና ዘንጉን ቀጥቅጠው አበጁት፤ የአበባ ቅርጽ ያላቸው ጽዋዎች፣ እንቡጦችና የፈኩ አበቦች ከእርሱ ጋር አንድ ወጥ ሆነው ተሠርተው ነበር። 18ሦስቱ በአንድ በኩል ሦስቱ በሌላ በኩል በመሆን ስድስት ቅርንጫፎች ከመቅረዙ ጐኖች ተሠርተው ነበር። 19ከእንቡጦችና ከፈኩ አበቦች ጋር የለውዝ አበባ የሚመስሉ ሦስት ጽዋዎች በአንዱ ቅርንጫፍ ላይ፣ ሦስቱ ደግሞ በሚቀጥለው ቅርንጫፍ ላይ ነበሩ፤ ከመቅረዙ ለወጡት ለስድስቱም ቅርንጫፎች ሁሉ እንዲሁ ነበር። 20እንቡጦችና የፈኩ አበቦች ያሉባቸው የለውዝ አበባ የሚመስሉ አራት ጽዋዎች በመቅረዙ ላይ ነበሩ። 21አንደኛው እንቡጥ ከመቅረዙ ወጣ ብለው በሚገኙት በመጀመሪያው ጥንድ ቅርንጫፎች ሥር፣ ሁለተኛውም እምቡጥ በሁለተኛው ጥንድ ሥር እንዲሁም ሦስተኛው እንቡጥ በሦስተኛው ጥንድ ሥር ነበር፤ በስድስቱም ቅርንጫፎች እንዲሁ ነበር። 22እንቡጦቹና ቅርንጫፎቹ ሁሉ ከንጹሕ ወርቅ ተሠርተው ከመቅረዙ ጋር አንድ ወጥ ነበሩ።

23የመቅረዙን ሰባት መብራቶች፣ እንዲሁም መኰስተሪያዎችንና የኵስታሪ ማስቀመጫዎችን ከንጹሕ ወርቅ ሠሩ። 24መቅረዙንና ዕቃዎቹን ሁሉ ከአንድ መክሊት37፥24 ወደ 34 ኪሎ ግራም ያህል ማለት ነው። ንጹሕ ወርቅ ሠሩ።

የዕጣን መሠዊያው

37፥25-28 ተጓ ምብ – ዘፀ 30፥1-5

25የዕጣን መሠዊያውን ከግራር ዕንጨት ሠሩ፤ ርዝመቱ አንድ ክንድ፣ ወርዱ አንድ ክንድ፣ ከፍታው ሁለት ክንድ37፥25 ርዝመቱ ወርዱ 0.5 ሜትር ከፍታው 0.9 ሜትር ያህል ማለት ነው። ነበር፤ ቀንዶቹም ከእርሱ ጋር አንድ ወጥ ሆነው ተሠርተው ነበር። 26ላዩን፣ ጐኖቹን ሁሉና ቀንዶቹን በንጹሕ ወርቅ ለበጧቸው፤ በዙሪያው የወርቅ ክፈፍ አበጁ። 27ለሸክም የሚሆኑትን መሎጊያዎች ለመያዝ ትይዩ የሆኑ ከክፈፉ ሥር ሁለት የወርቅ ቀለበቶችን ሠሩ። 28መሎጊያዎቹን ከግራር ዕንጨት ሠሩ፤ በወርቅም ለበጧቸው።

29እንዲሁም የተቀደሰውን ቅብዐ ዘይትና የሽቶ ቀማሚ ሥራ የሆነውን፣ ንጹሕና መልካም መዐዛ ያለውን ዕጣን ሠሩ።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

出埃及記 37:1-29

約櫃

1比撒列用皂莢木造了一個櫃,長一點一米,寬六十六釐米,高六十六釐米。 2這櫃子裡外都包上純金,還鑲了一圈金邊。 3他造了四個金環,安在櫃的四個腳上,每邊兩個環, 4又用皂莢木造了兩根橫杠,外面包上金, 5然後把橫杠穿過櫃旁的金環,便於抬櫃。 6他用純金造施恩座,長一點一米,寬六十六釐米。 7又在施恩座的兩端用金子打造兩個基路伯天使, 8這兩個基路伯天使跟施恩座連在一起, 9在施恩座的兩端,面對面朝向施恩座,向上展開翅膀遮蓋施恩座。

桌子

10他用皂莢木造了一張桌子,長八十八釐米,寬四十四釐米,高六十六釐米。 11整張桌子都包上純金,四周鑲上金邊。 12在桌子四周造一個八釐米寬的外框,上面也鑲上金邊。 13他又造四個金環,安在桌子四角的桌腿上, 14金環靠近外框,以便穿橫杠抬桌子。 15他用皂莢木造兩根橫杠,外面包金,用來抬桌子。 16又用純金造桌子上的器具,就是盤、碟及獻酒用的杯和瓶。

17他用純金造了一座燈臺,燈臺的燈座、燈柱、油杯、花瓣和花苞都是用一塊純金打成的。 18燈臺兩邊各伸出三個分枝,共有六個分枝。 19每個分枝都伸出三個杏花形狀、有花瓣和花苞的油杯,六個分枝都是這樣。 20燈臺上有四個杏花形狀、有花瓣和花苞的杯。 21燈臺上每一對分枝的相連處有花苞,三對分枝都是這樣。 22整座燈臺,包括一切裝飾,都是用一塊純金打成的。 23他又用純金為這座燈臺造了七個燈盞,以及燈剪和燈花盤。 24造整座燈臺和燈臺的器具共用了三十四公斤純金。

造香壇

25他又用皂莢木造了一座方形的香壇,長寬各四十五釐米,高九十釐米,壇的四角與壇連成一體, 26壇頂、壇的四面和壇上的角狀物包上純金,四周鑲上金邊。 27他造了兩個金環,安在壇兩側的金邊下面, 28又用皂莢木造橫杠,包上金,穿在兩個環裡,用來抬香壇。

29他又用調製香料的方法製作聖膏油和純淨芬芳的香。