ዘፀአት 37 – NASV & BDS

New Amharic Standard Version

ዘፀአት 37:1-29

የኪዳኑ ታቦት

37፥1-9 ተጓ ምብ – ዘፀ 25፥10-20

1ባስልኤል ርዝመቱ ሁለት ክንድ ተኩል፣ ወርዱ አንድ ክንድ ተኩል37፥1 ከፍታው 1.1 ሜትር ወርዱና ርዝመቱ 0.7 ሜትር ያህል ማለት ነው።፣ ከፍታው አንድ ክንድ ተኩል የሆነ ታቦት ከግራር ዕንጨት ሠራ። 2በውስጥና በውጭ በንጹሕ ወርቅ ለበጠው፤ በዙሪያውም የወርቅ ክፈፍ አበጀለት። 3አራት የወርቅ ቀለበቶችን ሠርቶ ሁለት ቀለበቶችን በአንድ በኩል፣ ሁለት ቀለበቶችንም በሌላ በኩል አድርጎ ከአራቱ እግሮቹ ጋር አያያዛቸው። 4ከዚያም መሎጊያዎችን ከግራር ዕንጨት ሠርቶ በወርቅ ለበጣቸው። 5መሎጊያዎቹንም መሸከሚያ እንዲሆኑ በታቦቱ ጐንና ጐን ባሉት ቀለበቶች ውስጥ አስገባቸው።

6ርዝመቱ ሁለት ክንድ ተኩል37፥6 ርዝመቱ 1.1 ሜትር ወርዱ 1.1 ሜትር ያህል ማለት ነው።፣ ወርዱም አንድ ክንድ ተኩል የሆነ ከንጹሕ ወርቅ የስርየት መክደኛ ሠራ። 7ከዚያም ከተቀጠቀጠ ወርቅ ሁለት ኪሩቤልን ከመክደኛው ጫፎች ላይ ሠራ። 8አንዱን ኪሩብ በአንዱ ጫፍ ላይ፣ ሁለተኛውንም ኪሩብ በሌላው ጫፍ ላይ ሠራ፤ ከሁለቱ ጫፎች ላይ ከክዳኑ ጋር አንድ ወጥ አድርጎ ሠራቸው፤ 9ኪሩቤልም የስርየት ክዳኑን በመሸፈን ክንፋቸውን ወደ ላይ ዘርግተው ነበር፤ ኪሩቤል ወደ ስርየት መክደኛው እየተመለከቱ እርስ በርሳቸው ገጽ ለገጽ ነበሩ።

የኅብስት ማስቀመጫው ጠረጴዛ

37፥10-16 ተጓ ምብ – ዘፀ 25፥23-29

10ርዝመቱ ሁለት ክንድ፣ ወርዱ አንድ ክንድ፣ ከፍታውም አንድ ክንድ ተኩል የሆነ ጠረጴዛ ከግራር ዕንጨት ሠሩ37፥10 በዚህና በቍጥር 11-29 ባሉት ክፍሎች፣ ሥሩ11ከዚያም በንጹሕ ወርቅ በመለበጥ በዙሪያው የወርቅ ክፈፍ አበጁለት። 12በዙሪያውም ስፋቱ አንድ ስንዝር37፥12 ወደ 8 ሳንቲ ሜትር ያህል ማለት ነው። የሆነ ጠርዝ በማበጀት በጠርዙ ላይ የወርቅ ክፈፍ አደረጉበት። 13ለጠረጴዛው አራት የወርቅ ቀለበቶች አበጅተው አራቱ እግሮች ካሉበት ከአራቱ ማእዘኖች ጋር አያያዟቸው። 14ጠረጴዛውን ለመሸከም የሚያገለግሉትን መሎጊያዎች እንዲይዙ ቀለበቶቹ ከጠርዙ አጠገብ ሆኑ። 15ጠረጴዛውን ለመሸከም የሚያገለግሉት መሎጊያዎች ከግራር ዕንጨት የተሠሩና በወርቅ የተለበጡ ነበሩ። 16የጠረጴዛውን ዕቃዎች ይኸውም ዝርግ ሳሕኖችን፣ ድስቶችንና ጐድጓዳ ሳሕኖችን እንዲሁም የመጠጥ መሥዋዕቱ ማፍሰሻ የሆኑትን ማንቈርቈሪያዎች ከንጹሕ ወርቅ ሠሯቸው።

መቅረዙ

37፥17-24 ተጓ ምብ – ዘፀ 25፥31-39

17መቅረዙን ከንጹሕ ወርቅ ሠሩት፤ መቆሚያውንና ዘንጉን ቀጥቅጠው አበጁት፤ የአበባ ቅርጽ ያላቸው ጽዋዎች፣ እንቡጦችና የፈኩ አበቦች ከእርሱ ጋር አንድ ወጥ ሆነው ተሠርተው ነበር። 18ሦስቱ በአንድ በኩል ሦስቱ በሌላ በኩል በመሆን ስድስት ቅርንጫፎች ከመቅረዙ ጐኖች ተሠርተው ነበር። 19ከእንቡጦችና ከፈኩ አበቦች ጋር የለውዝ አበባ የሚመስሉ ሦስት ጽዋዎች በአንዱ ቅርንጫፍ ላይ፣ ሦስቱ ደግሞ በሚቀጥለው ቅርንጫፍ ላይ ነበሩ፤ ከመቅረዙ ለወጡት ለስድስቱም ቅርንጫፎች ሁሉ እንዲሁ ነበር። 20እንቡጦችና የፈኩ አበቦች ያሉባቸው የለውዝ አበባ የሚመስሉ አራት ጽዋዎች በመቅረዙ ላይ ነበሩ። 21አንደኛው እንቡጥ ከመቅረዙ ወጣ ብለው በሚገኙት በመጀመሪያው ጥንድ ቅርንጫፎች ሥር፣ ሁለተኛውም እምቡጥ በሁለተኛው ጥንድ ሥር እንዲሁም ሦስተኛው እንቡጥ በሦስተኛው ጥንድ ሥር ነበር፤ በስድስቱም ቅርንጫፎች እንዲሁ ነበር። 22እንቡጦቹና ቅርንጫፎቹ ሁሉ ከንጹሕ ወርቅ ተሠርተው ከመቅረዙ ጋር አንድ ወጥ ነበሩ።

23የመቅረዙን ሰባት መብራቶች፣ እንዲሁም መኰስተሪያዎችንና የኵስታሪ ማስቀመጫዎችን ከንጹሕ ወርቅ ሠሩ። 24መቅረዙንና ዕቃዎቹን ሁሉ ከአንድ መክሊት37፥24 ወደ 34 ኪሎ ግራም ያህል ማለት ነው። ንጹሕ ወርቅ ሠሩ።

የዕጣን መሠዊያው

37፥25-28 ተጓ ምብ – ዘፀ 30፥1-5

25የዕጣን መሠዊያውን ከግራር ዕንጨት ሠሩ፤ ርዝመቱ አንድ ክንድ፣ ወርዱ አንድ ክንድ፣ ከፍታው ሁለት ክንድ37፥25 ርዝመቱ ወርዱ 0.5 ሜትር ከፍታው 0.9 ሜትር ያህል ማለት ነው። ነበር፤ ቀንዶቹም ከእርሱ ጋር አንድ ወጥ ሆነው ተሠርተው ነበር። 26ላዩን፣ ጐኖቹን ሁሉና ቀንዶቹን በንጹሕ ወርቅ ለበጧቸው፤ በዙሪያው የወርቅ ክፈፍ አበጁ። 27ለሸክም የሚሆኑትን መሎጊያዎች ለመያዝ ትይዩ የሆኑ ከክፈፉ ሥር ሁለት የወርቅ ቀለበቶችን ሠሩ። 28መሎጊያዎቹን ከግራር ዕንጨት ሠሩ፤ በወርቅም ለበጧቸው።

29እንዲሁም የተቀደሰውን ቅብዐ ዘይትና የሽቶ ቀማሚ ሥራ የሆነውን፣ ንጹሕና መልካም መዐዛ ያለውን ዕጣን ሠሩ።

La Bible du Semeur

Exode 37:1-29

Le coffre de l’alliance et le propitiatoire37.1 titre Pour les v. 1-9, voir 25.10-22. En hébreu, les mesures sont en coudées, sauf au v. 12, où il s’agit d’un palme. Au v. 24, le poids est d’un talent.

1Betsaléel fabriqua le coffre en bois d’acacia ; il avait cent vingt-cinq centimètres de long, soixante-quinze centimètres de large et soixante-quinze centimètres de haut. 2Il le plaqua d’or pur à l’intérieur et à l’extérieur et le garnit d’une bordure d’or tout autour. 3Il coula pour lui quatre anneaux d’or qu’il fixa à ses quatre coins, deux de chaque côté. 4Il fit des barres en bois d’acacia qu’il plaqua d’or. 5Il les engagea dans les anneaux le long des côtés du coffre pour qu’on puisse le porter.

6Il fit le propitiatoire en or pur. Il avait cent vingt-cinq centimètres de long et soixante-quinze centimètres de large. 7Il façonna au marteau deux chérubins en or massif qu’il fixa aux deux extrémités du propitiatoire 8de manière à ce qu’ils fassent corps avec lui. 9Les chérubins déployaient leurs ailes vers le haut pour couvrir le propitiatoire et se faisaient face, le regard dirigé vers le propitiatoire.

La table et ses accessoires37.10 Pour les v. 10-16, voir 25.23-30.

10Betsaléel fabriqua la table en bois d’acacia, d’un mètre de long, de cinquante centimètres de large et de soixante-quinze centimètres de haut. 11Il la plaqua d’or pur et garnit son pourtour d’une bordure d’or. 12Il lui fit un cadre de huit centimètres qu’il garnit d’une bordure d’or. 13Il coula quatre anneaux d’or qu’il fixa aux quatre coins près des quatre pieds de la table. 14Il plaça ces anneaux tout près du cadre pour recevoir les barres destinées à porter la table. 15Il fit les barres en bois d’acacia et les plaqua d’or. Elles servaient à transporter la table. 16Il fit d’or pur les accessoires qu’on devait mettre sur la table, les plats, les coupes, les bols et les carafes qui servaient aux libations.

Le chandelier et ses lampes37.17 Pour les v. 17-24, voir 25.31-40.

17Il fabriqua le chandelier en or pur ; le chandelier, son pied et sa tige furent travaillés au marteau ; des coupelles, calices et corolles en étaient issus. 18Six branches en partaient latéralement, trois de chaque côté. 19Chaque branche portait trois coupelles en forme de fleur d’amandier avec un calice et une corolle. Il en était ainsi des six branches du chandelier. 20Le pied portait quatre coupelles en forme de fleur d’amandier avec un calice et une corolle : 21il y avait un calice sous chacune des trois paires de branches du chandelier, correspondant aux six branches sortant du chandelier. 22Ces calices et ces branches faisaient corps avec lui : le tout était fait d’une seule masse d’or pur martelé.

23Il fabriqua aussi les sept lampes avec les pincettes et les mouchettes en or pur. 24On employa trente kilogrammes d’or pur pour le chandelier et tous ses accessoires.

L’autel des parfums et le parfum

25Betsaléel fabriqua l’autel des parfums en bois d’acacia, il était carré, de cinquante centimètres de côté, et était relevé aux angles de quatre cornes en saillie. Il avait un mètre de hauteur. 26Il en plaqua d’or pur le plateau, les parois tout autour et les cornes et le garnit d’une bordure d’or qui en faisait le tour. 27Il lui fit deux anneaux d’or qu’il fixa sous la bordure de part et d’autre, sur les deux parois, pour recevoir les barres servant à transporter l’autel. 28Il fit ces barres en bois d’acacia plaqué d’or37.28 Pour les v. 25-28, voir 30.1-10.. 29Il fit faire l’huile d’onction sainte et le parfum aromatique pur par un parfumeur37.29 Voir 30.22-28..