ዘፀአት 33 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዘፀአት 33:1-23

1ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን አለው፤ “አንተና ከግብፅ ያወጣኸው ሕዝብህ ይህን ስፍራ ለቅቃችሁ ‘ለዘርህ እሰጣለሁ’ በማለት ለአብርሃም፣ ለይስሐቅና ለያዕቆብ በመሐላ ተስፋ ወደ ገባሁላችሁ ምድር ሂዱ። 2መልአክን በፊትህ በመላክ፣ ከነዓናውያንን፣ አሞራውያንን፣ ኬጢያውያንን፣ ፌርዛውያንን፣ ኤዊያዊያንንና ኢያቡሳውያንን አስወጣለሁ። 3ማርና ወተት ወደምታፈስሰው ምድር ውጡ፤ ነገር ግን ዐንገተ ደንዳና ሕዝብ ስለ ሆናችሁ፣ በመንገድ ላይ እንዳላጠፋችሁ እኔ ከእናንተ ጋር አልሄድም።”

4ሕዝቡም እነዚህን አሳዛኝ ቃላት በሰሙ ጊዜ ይተክዙ ጀመር፤ ማንም ሰው አንዳች ጌጥ አላደረገም። 5እግዚአብሔርም (ያህዌ) ሙሴን፣ “እስራኤላውያንን፣ ‘እናንተ ዐንገተ ደንዳና ሕዝብ ናችሁ፤ ለአንዳፍታ እንኳ ከእናንተ ጋር አብሬአችሁ ብሄድ አጠፋችሁ ነበር፤ አሁንም ጌጣጌጦቻችሁን አውልቁ፤ እናንተን ምን ማድረግ እንዳለብኝ እወስናለሁ’ ብለህ ንገራቸው” አለው። 6ስለዚህ እስራኤላውያን በኮሬብ ተራራ ላይ ጌጣጌጦቻቸውን አወለቁ።

የመገናኛው ድንኳን

7ሙሴ “የመገናኛው ድንኳን” ብሎ የጠራውን በመውሰድ፣ ከሰፈሩ ውጭ ራቅ ባለ ቦታ ላይ ይተክለው ነበር። እግዚአብሔርን (ያህዌ) መጠየቅ የሚፈልግ ሁሉ ከሰፈሩ ውጭ ወዳለው ወደ መገናኛው ድንኳን ይሄድ ነበር። 8ሙሴ ወደ ድንኳኑ በወጣ ጊዜ ሕዝቡ በመነሣት ወደ ድንኳኑ እስኪገባ ድረስ በየድንኳኖቻቸው ደጃፍ ላይ ቆመው ይጠባበቁ ነበር። 9ሙሴ ወደ ድንኳኑ ገብቶ እግዚአብሔር (ያህዌ) ከሙሴ ጋር እየተነጋገረ ሳለ የደመናው ዐምድ ወርዶ በመግቢያው ላይ ይቆም ነበር። 10ሕዝቡ የደመናውን ዐምድ በድንኳኑ ደጃፍ ላይ ቆሞ ሲያዩት ሁሉም በየድንኳኖቻቸው ደጃፍ ላይ ቆመው ይሰግዱ ነበር። 11ሰው ከባልንጀራው ጋር እንደሚነጋገር እግዚአብሔር (ያህዌ) ከሙሴ ጋር ፊት ለፊት ይነጋገር ነበር፤ ከዚያም ሙሴ ወደ ሰፈሩ ይመለሳል፤ ረዳቱ የነበረው ብላቴናው የነዌ ልጅ ኢያሱ ግን ከድንኳኑ አይለይም ነበር።

ሙሴና የእግዚአብሔር ክብር

12ሙሴ እግዚአብሔርን (ያህዌ) አለው፤ “ ‘እነዚህን ሕዝብ ምራ’ ብለህ ነግረኸኝ ነበር፤ ከእኔ ጋር የምትልከው ማን እንደ ሆነ ግን አላሳወቅኸኝም፤ ‘አንተን በስም ዐውቅሃለሁ፤ በፊቴም ሞገስ አግኝተሃል’ ብለህ ነበር። 13በእኔ ደስ ተሰኝተህ ከሆነ፣ አንተን ዐውቅህና ያለ ማቋረጥ በፊትህ ሞገስ አገኝ ዘንድ መንገድህን አስተምረኝ፤ ይህ ሕዝብ የአንተ ሕዝብ መሆኑን አስታውስ።”

14እግዚአብሔር (ያህዌ) “ሀልዎቴ ከአንተ ጋር ይሄዳል፤ ዕረፍትም እሰጥሃለሁ” ብሎ መለሰ።

15ከዚያም ሙሴ እንዲህ አለው፤ “ሀልዎትህ ከእኛ ጋር ካልሄደ ከዚህ አትስደደን። 16አንተ ከእኛ ጋር ካልሄድህ፣ አንተ በእኔና በሕዝብህ መደሰትህን ሌላው እንዴት ያውቃል? እኔንና ሕዝብህንስ በገጸ ምድር ከሚገኙት ከሌሎቹ ሕዝቦች ሁሉ ልዩ የሚያደርገን ሌላ ምን አለ?”

17እግዚአብሔርም (ያህዌ) ሙሴን፣ “በአንተ ደስ ስላለኝና በስም ስለማውቅህ፣ የጠየቅኸውን ያንኑ አደርጋለሁ” አለው።

18ከዚያም ሙሴ “እባክህ፤ ክብርህን አሳየኝ” አለው።

19እግዚአብሔር (ያህዌ) እንዲህ አለ፤ “መልካምነቴ ሁሉ በፊትህ እንዲያልፍ አደርጋለሁ፤ በፊትህም ስሜን እግዚአብሔርን (ያህዌ) ዐውጃለሁ፤ ለምምረው ምሕረት አደርጋለሁ፤ ለምራራለትም ርኅራኄ አደርጋለሁ፤ 20ነገር ግን፣ ማንም እኔን አይቶ መኖር ስለማይችል፣ ፊቴን ማየት አትችልም።”

21ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) እንዲህ አለ፤ “በአጠገቤ ስፍራ አለ አንተም በዐለት ላይ ትቆማለህ፤ 22ክብሬ በዚያ ሲያልፍ በዐለቱ ስንጥቅ ውስጥ አደርግሃለሁ፤ በዚያም እስከማልፍ ድረስ በእጄ እጋርድሃለሁ፤ 23ከዚያም እጄን አነሣለሁ፤ ጀርባዬንም ታያለህ፤ ፊቴ ግን መታየት የለበትም።”

Thai New Contemporary Bible

อพยพ 33:1-23

1แล้วองค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับโมเสสว่า “จงไปจากที่นี่ ทั้งเจ้ากับเหล่าประชากรซึ่งเจ้าพาออกมาจากอียิปต์ และไปยังดินแดนที่เราสัญญาโดยปฏิญาณไว้กับอับราฮัม อิสอัค และยาโคบว่า ‘เราจะยกดินแดนนี้ให้แก่วงศ์วานของเจ้า’ 2เราจะส่งทูตมานำหน้าเจ้าทั้งหลายและขับไล่ชาวคานาอัน ชาวอาโมไรต์ ชาวฮิตไทต์ ชาวเปริสซี ชาวฮีไวต์ และชาวเยบุสออกไป 3จงไปยังดินแดนอันอุดมด้วยน้ำนมและน้ำผึ้ง แต่เราจะไม่ไปกับพวกเจ้า เพราะเจ้าทั้งหลายเป็นชนชาติที่ดื้อด้าน เกรงว่าเราจะทำลายพวกเจ้าเสียระหว่างทาง”

4เมื่อปวงประชากรได้ยินคำที่น่าทุกข์ใจเช่นนี้ก็พากันโศกเศร้าคร่ำครวญและไม่มีผู้ใดสวมเครื่องประดับเลย 5เพราะองค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับโมเสสว่า “จงบอกชนอิสราเอลว่า ‘เจ้าทั้งหลายเป็นคนดื้อด้าน ถ้าเราไปกับพวกเจ้าแม้สักครู่เดียว เราอาจจะทำลายพวกเจ้า บัดนี้จงถอดเครื่องประดับออก จนกว่าเราจะตกลงใจได้ว่าจะทำอย่างไรกับพวกเจ้าดี’ ” 6ดังนั้นชนอิสราเอลจึงถอดเครื่องประดับออกที่ภูเขาโฮเรบ

เต็นท์นัดพบ

7โมเสสเคยตั้งเต็นท์หลังหนึ่งไว้นอกค่าย ไกลออกมาหน่อยหนึ่ง ซึ่งเรียกว่า “เต็นท์นัดพบ” ทุกคนที่ต้องการคำปรึกษาจากองค์พระผู้เป็นเจ้าจะไปที่เต็นท์นัดพบซึ่งอยู่นอกค่ายนั้น 8เมื่อใดก็ตามที่โมเสสออกไปที่เต็นท์นัดพบ ประชากรทั้งหมดจะลุกขึ้นยืนอยู่ตรงทางเข้าเต็นท์ของตนคอยดูจนโมเสสเข้าไปในเต็นท์นัดพบ 9เมื่อโมเสสเข้าไป เสาเมฆจะเคลื่อนมาหยุดอยู่ตรงทางเข้าขณะที่องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับโมเสส 10ทุกครั้งที่ประชากรเห็นเสาเมฆอยู่ที่ทางเข้าเต็นท์นัดพบ พวกเขาทุกคนก็จะยืนนมัสการอยู่ที่ทางเข้าเต็นท์ของตน 11องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับโมเสสต่อหน้าเหมือนเพื่อนคุยกัน หลังจากนั้นโมเสสจะกลับมาที่ค่ายพัก แต่โยชูวาบุตรนูนชายหนุ่มผู้ช่วยของโมเสสยังคงอยู่ในเต็นท์

โมเสสกับพระเกียรติสิริขององค์พระผู้เป็นเจ้า

12โมเสสกราบทูลองค์พระผู้เป็นเจ้าว่า “พระองค์ตรัสกับข้าพระองค์ว่า ‘จงนำประชากรเหล่านี้ไป’ แต่พระองค์ยังไม่ได้บอกเลยว่าจะทรงส่งผู้ใดไปกับข้าพระองค์ พระองค์ตรัสว่า ‘เรารู้จักชื่อของเจ้าและเจ้าเป็นที่โปรดปรานของเรา’ 13หากพระองค์ทรงพอพระทัยข้าพระองค์ ขอทรงสอนทางของพระองค์ เพื่อข้าพระองค์จะรู้จักพระองค์และเป็นที่โปรดปรานของพระองค์สืบไป นอกจากนี้ขอทรงระลึกว่าชนชาตินี้เป็นประชากรของพระองค์”

14องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสตอบว่า “เราเองจะไปกับเจ้าและให้เจ้าได้หยุดพัก”

15โมเสสจึงกราบทูลว่า “หากพระองค์ไม่ได้เสด็จไปกับข้าพระองค์ทั้งหลายก็ขออย่าให้ข้าพระองค์ทั้งหลายเคลื่อนไปจากที่นี่เลย 16หากพระองค์ไม่ได้เสด็จไปด้วย ใครเล่าจะทราบได้ว่าข้าพระองค์และประชากรของพระองค์เป็นที่โปรดปรานและแตกต่างจากประชากรอื่นใดบนพื้นโลก?”

17องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับโมเสสว่า “เราจะทำตามที่เจ้าขอ เพราะเจ้าเป็นที่โปรดปรานของเรา และเรารู้จักชื่อของเจ้า”

18โมเสสจึงกราบทูลว่า “บัดนี้ขอทรงสำแดงพระเกียรติสิริของพระองค์แก่ข้าพระองค์”

19และองค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่า “เราจะให้ความดีทั้งหมดของเราประจักษ์แจ้งต่อหน้าเจ้า และเราจะประกาศนามของเรา คือพระยาห์เวห์ต่อหน้าเจ้า เราจะเมตตาใครก็จะเมตตาคนนั้น เราจะกรุณาใครก็จะกรุณาคนนั้น 20แต่เจ้าไม่อาจเห็นหน้าเราเพราะมนุษย์เห็นเราแล้วไม่อาจมีชีวิตอยู่ได้”

21แล้วองค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่า “มีที่แห่งหนึ่งอยู่ใกล้เราซึ่งเจ้าจะยืนบนก้อนหินได้ 22และเมื่อเกียรติสิริของเราผ่านไป เราจะซ่อนเจ้าไว้ในซอกหินและเอามือบังเจ้าไว้จนกว่าเราจะผ่านไป 23แล้วเราจึงจะเอามือออก เจ้าจะเห็นหลังของเรา แต่เจ้าจะเห็นหน้าของเราไม่ได้”