ዘፀአት 33 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ዘፀአት 33:1-23

1ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን አለው፤ “አንተና ከግብፅ ያወጣኸው ሕዝብህ ይህን ስፍራ ለቅቃችሁ ‘ለዘርህ እሰጣለሁ’ በማለት ለአብርሃም፣ ለይስሐቅና ለያዕቆብ በመሐላ ተስፋ ወደ ገባሁላችሁ ምድር ሂዱ። 2መልአክን በፊትህ በመላክ፣ ከነዓናውያንን፣ አሞራውያንን፣ ኬጢያውያንን፣ ፌርዛውያንን፣ ኤዊያዊያንንና ኢያቡሳውያንን አስወጣለሁ። 3ማርና ወተት ወደምታፈስሰው ምድር ውጡ፤ ነገር ግን ዐንገተ ደንዳና ሕዝብ ስለ ሆናችሁ፣ በመንገድ ላይ እንዳላጠፋችሁ እኔ ከእናንተ ጋር አልሄድም።”

4ሕዝቡም እነዚህን አሳዛኝ ቃላት በሰሙ ጊዜ ይተክዙ ጀመር፤ ማንም ሰው አንዳች ጌጥ አላደረገም። 5እግዚአብሔርም (ያህዌ) ሙሴን፣ “እስራኤላውያንን፣ ‘እናንተ ዐንገተ ደንዳና ሕዝብ ናችሁ፤ ለአንዳፍታ እንኳ ከእናንተ ጋር አብሬአችሁ ብሄድ አጠፋችሁ ነበር፤ አሁንም ጌጣጌጦቻችሁን አውልቁ፤ እናንተን ምን ማድረግ እንዳለብኝ እወስናለሁ’ ብለህ ንገራቸው” አለው። 6ስለዚህ እስራኤላውያን በኮሬብ ተራራ ላይ ጌጣጌጦቻቸውን አወለቁ።

የመገናኛው ድንኳን

7ሙሴ “የመገናኛው ድንኳን” ብሎ የጠራውን በመውሰድ፣ ከሰፈሩ ውጭ ራቅ ባለ ቦታ ላይ ይተክለው ነበር። እግዚአብሔርን (ያህዌ) መጠየቅ የሚፈልግ ሁሉ ከሰፈሩ ውጭ ወዳለው ወደ መገናኛው ድንኳን ይሄድ ነበር። 8ሙሴ ወደ ድንኳኑ በወጣ ጊዜ ሕዝቡ በመነሣት ወደ ድንኳኑ እስኪገባ ድረስ በየድንኳኖቻቸው ደጃፍ ላይ ቆመው ይጠባበቁ ነበር። 9ሙሴ ወደ ድንኳኑ ገብቶ እግዚአብሔር (ያህዌ) ከሙሴ ጋር እየተነጋገረ ሳለ የደመናው ዐምድ ወርዶ በመግቢያው ላይ ይቆም ነበር። 10ሕዝቡ የደመናውን ዐምድ በድንኳኑ ደጃፍ ላይ ቆሞ ሲያዩት ሁሉም በየድንኳኖቻቸው ደጃፍ ላይ ቆመው ይሰግዱ ነበር። 11ሰው ከባልንጀራው ጋር እንደሚነጋገር እግዚአብሔር (ያህዌ) ከሙሴ ጋር ፊት ለፊት ይነጋገር ነበር፤ ከዚያም ሙሴ ወደ ሰፈሩ ይመለሳል፤ ረዳቱ የነበረው ብላቴናው የነዌ ልጅ ኢያሱ ግን ከድንኳኑ አይለይም ነበር።

ሙሴና የእግዚአብሔር ክብር

12ሙሴ እግዚአብሔርን (ያህዌ) አለው፤ “ ‘እነዚህን ሕዝብ ምራ’ ብለህ ነግረኸኝ ነበር፤ ከእኔ ጋር የምትልከው ማን እንደ ሆነ ግን አላሳወቅኸኝም፤ ‘አንተን በስም ዐውቅሃለሁ፤ በፊቴም ሞገስ አግኝተሃል’ ብለህ ነበር። 13በእኔ ደስ ተሰኝተህ ከሆነ፣ አንተን ዐውቅህና ያለ ማቋረጥ በፊትህ ሞገስ አገኝ ዘንድ መንገድህን አስተምረኝ፤ ይህ ሕዝብ የአንተ ሕዝብ መሆኑን አስታውስ።”

14እግዚአብሔር (ያህዌ) “ሀልዎቴ ከአንተ ጋር ይሄዳል፤ ዕረፍትም እሰጥሃለሁ” ብሎ መለሰ።

15ከዚያም ሙሴ እንዲህ አለው፤ “ሀልዎትህ ከእኛ ጋር ካልሄደ ከዚህ አትስደደን። 16አንተ ከእኛ ጋር ካልሄድህ፣ አንተ በእኔና በሕዝብህ መደሰትህን ሌላው እንዴት ያውቃል? እኔንና ሕዝብህንስ በገጸ ምድር ከሚገኙት ከሌሎቹ ሕዝቦች ሁሉ ልዩ የሚያደርገን ሌላ ምን አለ?”

17እግዚአብሔርም (ያህዌ) ሙሴን፣ “በአንተ ደስ ስላለኝና በስም ስለማውቅህ፣ የጠየቅኸውን ያንኑ አደርጋለሁ” አለው።

18ከዚያም ሙሴ “እባክህ፤ ክብርህን አሳየኝ” አለው።

19እግዚአብሔር (ያህዌ) እንዲህ አለ፤ “መልካምነቴ ሁሉ በፊትህ እንዲያልፍ አደርጋለሁ፤ በፊትህም ስሜን እግዚአብሔርን (ያህዌ) ዐውጃለሁ፤ ለምምረው ምሕረት አደርጋለሁ፤ ለምራራለትም ርኅራኄ አደርጋለሁ፤ 20ነገር ግን፣ ማንም እኔን አይቶ መኖር ስለማይችል፣ ፊቴን ማየት አትችልም።”

21ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) እንዲህ አለ፤ “በአጠገቤ ስፍራ አለ አንተም በዐለት ላይ ትቆማለህ፤ 22ክብሬ በዚያ ሲያልፍ በዐለቱ ስንጥቅ ውስጥ አደርግሃለሁ፤ በዚያም እስከማልፍ ድረስ በእጄ እጋርድሃለሁ፤ 23ከዚያም እጄን አነሣለሁ፤ ጀርባዬንም ታያለህ፤ ፊቴ ግን መታየት የለበትም።”

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

出埃及記 33:1-23

1耶和華對摩西說:「我曾向亞伯拉罕以撒雅各起誓,應許把迦南賜給他們的後代。現在你和你從埃及領出來的百姓要動身去那裡。 2我必差遣天使走在你們前面,趕出當地的迦南人、亞摩利人、人、比利洗人、希未人和耶布斯人, 3帶你們進入那奶蜜之鄉。但我不會跟你們一起去,免得我在途中就把你們滅絕了,因為你們是頑固不化的百姓。」

4百姓聽見這壞消息,都非常哀傷,不再佩戴飾物了。 5耶和華對摩西說:「你去向以色列百姓宣佈,『你們這些頑固不化的人,我就是跟你們在一起待一刻,都恐怕會滅絕你們。現在你們要摘下自己身上的飾物,我再決定怎樣處置你們。』」 6因此,以色列百姓從何烈山開始就不再佩戴飾物了。

耶和華的會幕

7摩西通常把帳幕支搭在營外離百姓較遠的地方,摩西稱帳幕為會幕。凡求問耶和華的,都會去那裡。 8摩西離營去會幕的時候,百姓就都一同起來,各人站在自己的帳篷門口目送摩西走進會幕。 9摩西進入會幕後,便有雲柱降下來,停在會幕門口,耶和華就跟摩西說話。 10每當百姓看見這景象,他們都站在自己的帳篷門口敬拜耶和華。 11在會幕內,耶和華跟摩西面對面說話,好像兩個朋友談話一樣。然後,摩西返回營中,但他的年輕助手、的兒子約書亞仍然留在會幕。

耶和華的榮耀

12摩西對耶和華說:「你吩咐我帶領這些百姓,卻沒有告訴我你將要派誰與我同去,只說,『我憑名字認識你,你在我面前蒙了恩。』 13我若已經在你面前蒙恩,就求你把你的道路指示我,好讓我認識你,繼續在你面前蒙恩。求你顧念這些百姓是你的子民。」 14耶和華回答他說:「我必親自與你同去,使你平安穩妥。」 15摩西說:「你若不與我們同去,就不要讓我們離開這裡。 16你若不與我們同去,誰會知道我和你的子民在你面前蒙了恩呢?豈不是因為你的同在才使我們不同於地上其他民族嗎?」

17耶和華回答說:「我答應你的請求,因為你在我面前蒙了恩,我憑名字認識你。」 18摩西說:「求你向我彰顯你的榮耀。」 19耶和華說:「我必叫你看見我一切的美善,我要在你面前宣告我的名——耶和華,我要恩待誰就恩待誰,我要憐憫誰就憐憫誰。 20但你不能看我的臉,因為凡看見的,都不能存活。 21你要站在我旁邊的磐石上, 22我的榮耀經過你面前的時候,我會先把你安置在石縫裡,用我的手遮掩你,直到我從你面前走過。 23然後我會收回我的手,你就可以看見我的背,但看不到我的臉。」