ዘፀአት 15 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

ዘፀአት 15:1-27

የሙሴና የማርያም መዝሙር

1ከዚያም ሙሴና እስራኤላውያን ይህን መዝሙር ለእግዚአብሔር (ያህዌ) ዘመሩ፤

“ከፍ ከፍ ብሎ ከብሯልና፣

ለእግዚአብሔር (ያህዌ) እዘምራለሁ፤

ፈረሱንና ፈረሰኛውን፣

በባሕር ውስጥ ጥሏልና።

2እግዚአብሔር (ያህ) ብርታቴና ዝማሬዬ ነው፤

ድነቴም ሆነልኝ፤

እርሱ አምላኬ ነው፤ አመሰግነዋለሁ፤

የአባቴ አምላክ (ኤሎሂም) ነው፤ እኔም ከፍ ከፍ አደርገዋለሁ።

3እግዚአብሔር (ያህዌ) ተዋጊ ነው፤

ስሙም እግዚአብሔር (ያህዌ) ነው።

4የፈርዖንን ሠረገሎችና ሰራዊት፣

ባሕር ውስጥ ጣላቸው፤

ምርጥ የሆኑት የፈርዖን ሹማምት፣

ቀይ ባሕር ውስጥ ሰጠሙ።

5ቀላያትንም ለበሱ፤

እንደ ድንጋይ ወደ ጥልቁ ወረዱ።

6አቤቱ እግዚአብሔር (ያህዌ) ሆይ፤

ቀኝ እጅህ በግርማ ከበረ፤

አቤቱ እግዚአብሔር (ያህዌ) ሆይ፤

ቀኝ እጅህ ጠላትን አደቀቀ።

7“በግርማህ ታላቅነት፣

የተቃወሙህን ጣልኻቸው፤

ቍጣህን ሰደድህ፤

እንደ ገለባም በላቸው።

8በአፍንጫህ እስትንፋስ፣

ውሆች ተቈለሉ፤

ፈሳሾችም እንደ ግድግዳ ቆሙ፤

የጥልቁ ውሃ ባሕሩ ውስጥ ረጋ።

9ጠላት፣ ‘አሳድዳቸዋለሁ፤

እማርካቸዋለሁ፤

ምርኮን እካፈላለሁ፤

ነፍሴ በእነርሱ ትጠግባለች፤

ሰይፌን እመዝዛለሁ፤

እጄም ትደመስሳቸዋለች አለ።’

10አንተ ግን እስትንፋስህን አነፈስህ፤

ባሕርም ከደናቸው፤

በኀያላን ውሆች፣

እንደ ብረት ሰጠሙ።

11አቤቱ እግዚአብሔር (ያህዌ) ሆይ፤

ከአማልክት መካከል፣ እንደ አንተ ማን አለ?

በቅድስናው የከበረ፣

በክብሩ የሚያስፈራ፣

ድንቆችን የሚያደርግ፣

እንደ አንተ ማን አለ?

12“ቀኝ እጅህን ዘረጋህ፤

ምድርም ዋጠቻቸው።

13በማይለወጠው ፍቅርህ፣

የተቤዥሃቸው ሕዝብህን ትመራለህ፤

እነርሱን በብርታትህ፣

ወደ ቅዱስ ማደሪያህ ትመራቸዋለህ።

14አሕዛብ ይሰማሉ፤ ይንቀጠቀጡማል፤

የፍልስጥኤምን ሕዝብ ሥቃይ ይይዛቸዋል።

15የኤዶምም አለቆች ይርዳሉ፤

የሞአብ አለቆች በእንቅጥቃጤ ይያዛሉ፤

የከነዓን ሕዝብ ይቀልጣሉ።

16አቤቱ እግዚአብሔር (ያህዌ) ሆይ፤ ሕዝብህ

እስከሚያልፉ ድረስ፣

የተቤዠኻቸው ሕዝብህ እስኪያልፉ ድረስ፣

ድንጋጤና ሽብር በእነርሱ ላይ ይመጣል፤

በክንድህ ብርታት፣

እንደ ድንጋይ የማይንቀሳቀሱ ይሆናሉ።

17እግዚአብሔር (ያህዌ) ሆይ፤ ማደሪያህ

እንዲሆን በሠራኸው ስፍራ፣

ጌታ (አዶናይ) ሆይ፤ እጆችህ በሠሩት መቅደስ፣

በርስትህ ተራራ ላይ፣ ታመጣቸዋለህ፤ ትተክላቸዋለህም።

18እግዚአብሔር (ያህዌ)

ከዘላለም እስከ ዘላለም ይነግሣል።”

19የፈርዖን ፈረሶች፣ ሠረገሎቹና15፥19 ወይም፣ ሠረገለኞች ፈረሰኞቹ ወደ ባሕሩ በገቡ ጊዜ እግዚአብሔር (ያህዌ) የባሕሩን ውሃ በላያቸው ላይ መለሰባቸው፤ እስራኤላውያን ግን በባሕሩ ውስጥ በደረቅ ምድር ተሻገሩ። 20ከዚያም የአሮን እኅት ነቢዪቱ ማርያም ከበሮዋን አንሥታ ያዘች፤ የቀሩትም ሴቶች ሁሉ ከበሮ ይዘው እያሸበሸቡ ተከተሏት። 21ማርያምም፣

“ፈረሱንና ፈረሰኛውን፣

በባሕር ውስጥ ጥሏል፤ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) ዘምሩ፤

እጅግ ከፍ ከፍ ብሏልና”

እያለች ዘመረችላቸው።

የማራና የኤሊም ውሃ

22ከዚያም ሙሴ እስራኤልን ከቀይ ባሕር እየመራቸው ወደ ሱር ምድረ በዳ ሄዱ፤ ለሦስት ቀናት ውሃ ሳያገኙም በምድረ በዳ ተጓዙ። 23ማራ በደረሱ ጊዜ ውሃው መራራ ስለ ነበር ሊጠጡት አልቻሉም፤ ቦታው ማራ ተብሎ የተጠራውም ከዚህ የተነሣ ነው።15፥23 ማራ ማለት መራራ ማለት ነው። 24ሕዝቡም በሙሴ ላይ በማጕረምረም፣ “ምን እንጠጣ?” አሉ።

25ከዚያም ሙሴ ወደ እግዚአብሔር (ያህዌ) ጮኸ፤ እግዚአብሔር (ያህዌ) አንዲት ዛፍ አሳየው፤ ዕንጨቷንም ወደ ውሃው ጣላት፤ ውሃውም ጣፋጭ ሆነ።

በዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) ሕግና ሥርዐት አበጀላቸው፤ በዚያም ስፍራ ፈተናቸው። 26እርሱም አለ፤ “የአምላካችሁን እግዚአብሔር (ያህዌ) ድምፅ በጥንቃቄ ብትሰሙ፣ በፊቱም ትክክል የሆነውን ብትፈጽሙ፣ ትእዛዞቹን ልብ ብትሉና ሥርዐቱንም ሁሉ ብትጠብቁ፣ በግብፃውያን ላይ ያመጣሁባቸውን ማንኛውንም ዐይነት በሽታ በእናንተ ላይ አላመጣም፤ ፈዋሻችሁ እኔ እግዚአብሔር (ያህዌ) ነኝና።”

27ከዚያም ዐሥራ ሁለት ምንጮችና ሰባ የዘንባባ ዛፎች ወዳሉበት ወደ ኤሊም መጡ፤ እነርሱም በውሃው አጠገብ በዚያ ሰፈሩ።

Japanese Contemporary Bible

出エジプト記 15:1-27

15

勝利の歌

1その時、モーセとイスラエル人は主をたたえる歌をうたいました。

「主の勝利をたたえ、心から喜び歌おう。主は馬も人も、海に投げ込んだ。

2主は私の力、私の歌、私の救いだ。私は、私の神、主をたたえよう。先祖の神、主をあがめよう。

3主は兵士。まことに主と呼ぶにふさわしい。

4主はエジプト王の戦車と軍勢を滅ぼした。えり抜きの将校たちもおぼれ死んだ。

5水にのまれ、石のように海の底へ沈んだ。

6おお、主の右の手は力と栄光に満ち、敵を粉みじんに打ち砕く。

7その輝かしい御力によって、主は立ち向かう敵をすべて滅ぼした。主の怒りの火は激しく、彼らはわらのように燃え尽きた。

8主が息を吹きかけると、水は真っ二つに分かれた! 水は壁となってそそり立ち、海を二つに分けた。

9敵は言った。『あとを追え。彼らを滅ぼせ。剣のえじきにし、戦利品を分け合おう。』

10だが、それもつかの間、風が巻き上がり、海が彼らをのみ込んだ。彼らは大海に沈んだ、まるで鉛のように。

11主のような神がほかにいるだろうか。主のようにすばらしく、聖なる方がほかにいるだろうか。奇跡を行われる主のようにたたえられ、恐れられる神がほかにいるだろうか。

12主が手を伸ばすと、大地は彼らをのみ込んだ。

13自ら買い取った国民を、主は導いてくださった。聖なる地に優しく導いてくださった。

14国々はこの話を聞いておののく。ペリシテ人は恐れ、

15エドムの王たちは驚きまどい、モアブの君たちは震え上がり、カナン人は恐怖のとりことなった。

16だれもが驚き恐れた。主の大きな力を恐れ、敵もわれわれを襲わない。主が買い取った国民は、何の心配もなく外国人の間を通る。

17主はその国民を導き、神の山に植えてくださる。畏れ多くも、主ご自身の地、われわれのために備えてくださった聖なる地に。

18主は永遠に世界を治める。」

19ファラオの馬と騎手と戦車が、海の中を進もうとした時、水の壁はくずれ、彼らの頭上に覆いかぶさったのです。しかしイスラエル人は、乾いた地を渡りました。

20アロンの姉で女預言者のミリヤムが、タンバリンを手に、女たちの先頭に立って踊り始めました。

21ミリヤムは歌いました。

「主の勝利をたたえ、心から喜び歌おう。

主は馬も人も海に投げ込んだ。」

マラの水

22このあとモーセは人々を率いて、紅海からさらにシュルの荒野へ出ました。三日間、水のない日が続きました。 23やっとマラに着きましたが、水はあるものの苦くてとても飲めません。それで、マラ〔「苦い」の意〕という名がついたのです。 24人々はモーセに不平を言い立てました。「何とかしてくれ! のどが渇いて死にそうだ。」

25モーセは主に助けを求めました。すると、主は彼に一本の木を示し、それを水に投げ入れなさいと命じるのです。そのとおりにすると、水は甘くなりました。

このマラで、主はモーセを試みました。 26「もしもあなたがわたしに従い、正しいことを行うなら、エジプト人を悩ませた病気であなたが苦しまなくてすむようにしよう。わたしはあなたを癒やす主である。」

27こうして一行がエリムに着くと、そこには泉が十二と、なつめやしの木が七十本ありました。その泉のそばで、彼らは野営しました。