ዘፀአት 11 – NASV & CARS

New Amharic Standard Version

ዘፀአት 11:1-10

በበኵሮች ላይ የወረደ መቅሠፍት

1እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤ “በፈርዖንና በግብፅ ላይ አንድ ሌላ መቅሠፍት አወርድባቸዋለሁ፤ ከዚያም በኋላ ፈርዖን ይለቅቃችኋል፤ ሲለቅቃችሁም አንዳችሁን ሳያስቀር ያስወጣችኋል። 2ለእስራኤል ሕዝብ፣ ለወንዶቹም ሆነ ለሴቶቹ የብርና የወርቅ ዕቃዎች ከየጎረቤቶቻቸው ስጡን ብለው እንዲወስዱ ንገራቸው።” 3እግዚአብሔርም (ያህዌ) እስራኤላውያን በግብፃውያን ዘንድ ሞገስ እንዲያገኙ አደረጋቸው። ሙሴም በግብፅ ምድር በፈርዖን ሹማምትና በመላው ሕዝብ ዘንድ እጅግ የተከበረ ሰው ሆነ።

4ከዚህ በኋላ ሙሴ እንዲህ አለ፤ “እግዚአብሔር (ያህዌ) የሚለው ይህ ነው፤ ‘እኩለ ሌሊት ሲሆን በመላው የግብፅ ምድር ላይ ዐልፋለሁ። 5በዙፋኑ ላይ ከተቀመጠው ከፈርዖን ልጅ አንሥቶ የወፍጮ መጅ ገፊ እስከ ሆነችው እስከ ባሪያዪቱ ልጅ ድረስ በግብፅ ምድር በኵር ሆኖ የተወለደ ወንድ ልጅ ሁሉ ይሞታል፤ እንዲሁም የቀንድ ከብቱ በኵር በሙሉ ያልቃል። 6በግብፅ ምድር ሁሉ ከዚህ በፊት ያልተሰማ ወደ ፊትም የማይሰማ ታላቅ ዋይታ ይሆናል። 7በእስራኤላውያን ዘንድ ግን በሰውም ሆነ በእንስሳት ላይ ውሻ እንኳ አይጮኽባቸውም።’ በዚህም እግዚአብሔር (ያህዌ) በግብፃውያንና በእስራኤላውያን መካከል ልዩነት የሚያደርግ መሆኑን ታውቃላችሁ። 8ሹማምትህ በሙሉ ወደ እኔ ይመጣሉ፤ እጅ እየነሡም ‘አንተም ሆንህ የምትመራቸው ሰዎች በሙሉ ውጡልን’ ብለው ይለምኑኛል፤ እኔም ከዚያ በኋላ እሄዳለሁ።” ከዚያም ሙሴ በታላቅ ቍጣ ከፈርዖን ዘንድ ወጣ።

9እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን “ድንቅ ሥራዎቼ በግብፅ ምድር በብዛት ይታዩ ዘንድ ፈርዖን እናንተን አይሰማችሁም” አለው። 10ሙሴና አሮንም እነዚህን ድንቅ ታምራት በፈርዖን ፊት አደረጉ። ነገር ግን እግዚአብሔር (ያህዌ) የፈርዖንን ልብ አደነደነ፤ ፈርዖንም እስራኤላውያን ከአገሩ ለቅቀው እንዲሄዱ አልፈቀደም።

Священное Писание

Исход 11:1-10

Предсказание десятого наказания

1Вечный сказал Мусе:

– Я покараю фараона и Египет ещё лишь раз. После этого он отпустит вас и не просто отпустит, а выгонит. 2Скажи народу, чтобы мужчины и женщины попросили у соседей серебряных и золотых вещей.

3(Вечный расположил сердца египтян к народу Исраила, самого же Мусу приближённые фараона и народ считали великим человеком в Египте.)

4Муса передал фараону:

– Так говорит Вечный: «Около полуночи Я пройду по Египту, 5и все первенцы в Египте умрут – от первенца фараона, наследника престола, до первенца рабыни у жерновов. Умрёт даже первородный приплод скота. 6По всему Египту будет громкий плач, подобного которому не бывало прежде и не будет впредь. 7Но на исраильтян и на их скот даже собака не залает». Тогда вы увидите, какое различие делает Вечный между Египтом и Исраилом. 8Твои приближённые придут, поклонятся мне и скажут: «Уходи ты и весь народ, который следует за тобой!» После этого я уйду, – и Муса в гневе вышел от фараона.

9Вечный сказал Мусе:

– Я сделаю так, что фараон не станет слушать тебя, и тогда Я покажу Египту ещё больше чудес.

10Муса и Харун сотворили перед фараоном все эти чудеса, но Вечный сделал сердце фараона упрямым, и он не отпустил исраильтян из своей страны.