ዘፀአት 10 – NASV & NUB

New Amharic Standard Version

ዘፀአት 10:1-29

የአንበጣ መንጋ መቅሠፍት

1ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤ “ተመልሰህ ወደ ፈርዖን ሂድ፤ እነዚህን ታምራዊ ምልክቶች በመካከላቸው ለማድረግ የፈርዖንንና የሹማምቱን ልብ አደንድኛለሁና፤ 2ይኸውም ግብፃውያንን እንዴት አድርጌ እንደ ቀጣኋቸውና በመካከላቸውም ምልክቶቼን እንዴት እንዳደረግሁ ለልጆቻችሁና ለልጅ ልጆቻችሁ እንድትነግሩና እኔ እግዚአብሔር (ያህዌ) መሆኔንም እንድታውቁ ነው።”

3ሙሴና አሮን ወደ ፈርዖን ሄደው እንዲህ አሉት፤ “የዕብራውያን አምላክ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) እንዲህ ይላል፤ ‘ራስህን በፊቴ ለማዋረድ እስከ መቼ እንቢ ትላለህ? ሕዝቤ ያመልኩኝ ዘንድ ልቀቃቸው። 4እንዳይሄዱ ብትከለክላቸው ነገ በአገርህ ላይ አንበጣዎችን አመጣለሁ። 5አንበጣዎቹም ምድሪቱ እስከማትታይ ድረስ ይሸፍኗታል፤ በመስክህ ላይ እያቈጠቈጠ ያለውን ዛፍ ሁሉ ሳይቀር ከበረዶ የተረፈውንም ጥቂቱን ሁሉ ይበሉታል። 6የአንተን፣ የሹማምትህንና የግብፃውያንን ቤቶች ሁሉ ይሞሏቸዋል፤ ይህም አባቶችህም ሆኑ ቅድመ አያቶችህ በዚህች ምድር ከሰፈሩበት ጊዜ ጀምሮ እስካሁን ድረስ ከቶ አይተውት የማያውቁት ነው።’ ” ሙሴም ተመለሰና ከፈርዖን ተለይቶ ሄደ።

7የፈርዖንም ሹማምት፣ “ይህ ሰው እስከ መቼ ወጥመድ ይሆንብናል? አምላካቸውን እግዚአብሔርን (ያህዌ) እንዲያመልኩ ሰዎቹን ልቀቃቸውና ይሂዱ። ግብፅ መጥፋቷን እስካሁን አልተገነዘብህምን?” አሉት።

8ከዚያም ሙሴና አሮን ወደ ፈርዖን እንዲመጡ ተደረገ፤ “ሂዱ አምላካችሁን እግዚአብሔርን (ያህዌ) አምልኩ፤ ነገር ግን መሄድ የሚገባቸው የትኞቹ ናቸው?” አለ።

9ሙሴም፣ “ለእግዚአብሔር (ያህዌ) በዓል ልናከብር ስለሆነ ወጣቶቻችንንና ሽማግሌዎቻችንን፣ ወንድና ሴት ልጆቻችንን፣ የበግና የፍየል መንጋዎቻችንን እንዲሁም የቀንድ ከብቶቻችንን ይዘን እንሄዳለን” አለ።

10ፈርዖንም እንዲህ አለ፤ “ከሴቶቻችሁና ከልጆቻችሁ ጋር እንድትሄዱ እለቅቃችኋለሁ፤ እግዚአብሔር (ያህዌ) ከእናንተ ጋር ይሁን፤ ነገር ግን ተንኰል አስባችኋል።10፥10 ወይም፣ ተጠንቀቁ፤ ችግር ተዘጋጅቶላችኋል 11አይሆንም፤ ወንዶቹ ብቻ እንዲሄዱና እግዚአብሔርን (ያህዌ) እንዲያመልኩ አድርጉ፤ የጠየቃችሁት ይህንኑ ነው።” ከዚያም ሙሴና አሮን ከፈርዖን ፊት እንዲወጡ ተደረገ።

12እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን፣ “የአንበጣ መንጋ ምድሪቱን እንዲወርር ከበረዶ የተረፈውን ሁሉና በማሳም ላይ የበቀለውን ሁሉ ጠርጎ እንዲበላ እጅህን በግብፅ አገር ላይ ዘርጋ” አለው።

13ስለዚህ ሙሴ በግብፅ አገር ላይ በትሩን ዘረጋ፤ እግዚአብሔርም (ያህዌ) በዚያን ቀንና ሌሊት በሙሉ በምድሪቱ ላይ የምሥራቅ ነፋስ እንዲነፍስ አደረገ፤ በማግሥቱም ነፋሱ አንበጣዎችን አመጣ። 14እነርሱም ግብፅን በሙሉ ወረሩ፤ ስፍር ቍጥር የሌላቸው ሆነው የሀገሪቱን ዳር ድንበር ሁሉ አለበሱ። እንዲህ ያለ የአንበጣ መዓት ከዚህ ቀደም አልነበረም፤ ወደ ፊትም ደግሞ አይኖርም። 15ምድሩ ሁሉ ጠቍሮ እስኪጨልም ድረስ አለበሱት። ከበረዶ የተረፈውን፣ በመስክ ላይ የበቀለውንና በዛፍ ላይ ያለውን ፍሬ ሁሉ ጠርገው በሉ። በግብፅ ምድር ሁሉ በዛፍ ላይ ወይም በተክል ላይ አንዳች ቅጠል አልተረፈም ነበር።

16ከዚያም ፈርዖን ሙሴንና አሮንን በፍጥነት አስጠርቶ እንዲህ አላቸው፤ “በአምላካችሁ በእግዚአብሔር (ያህዌ) በእናንተም ላይ ኀጢአት ሠርቻለሁ፤ 17እንግዲህ አሁን አንድ ጊዜ ደግሞ ኀጢአቴን ይቅር በሉኝና ይህን ቀሣፊ መዓት እንዲያስወግድልኝ አምላካችሁን እግዚአብሔርን (ያህዌ) ለምኑልኝ።”

18ሙሴም ከፈርዖን ዘንድ ወደ እግዚአብሔር (ያህዌ) ጸለየ። 19ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) ነፋሱን ወደ ብርቱ የምዕራብ ነፋስ ለወጠው፤ ያም ነፋስ አንበጣዎቹን እየነዳ ወደ ቀይ ባሕር10፥19 ዕብራይስጡ “ያም ሱፍ” ይለዋል የሸንበቆ ባሕር ማለት ነው። ከተታቸው፤ በግብፅ ምድር በየትኛውም ቦታ አንድም አንበጣ አልቀረም። 20እግዚአብሔር (ያህዌ) ግን የፈርዖንን ልብ አደነደነ፤ ፈርዖንም እስራኤላውያን እንዲሄዱ አልፈቀደም።

የጨለማ መቅሠፍት

21ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን፣ “በግብፅ ላይ ድቅድቅ ጨለማ እንዲወርድ እጅህን ወደ ሰማይ ዘርጋ” አለው። 22ሙሴም እጁን ወደ ሰማይ ዘረጋ፤ በመላው ግብፅ ላይ ለሦስት ቀናት ድቅድቅ ያለ ጨለማ ሆነ። 23በእነዚያ ሦስት ቀናት ውስጥ አንዱ ሌላውን ማየት ወይም ከነበረበት ቦታ መንቀሳቀስ አይችልም ነበር። ይሁን እንጂ እስራኤላውያን በሚኖሩበት ስፍራ ሁሉ ብርሃን ነበር።

24ከዚያም ፈርዖን ሙሴን አስጠርቶ፣ “ሄዳችሁ እግዚአብሔርን (ያህዌ) አምልኩ፤ ሴቶቻችሁና ልጆቻችሁ ሳይቀሩ አብረዋችሁ ይሂዱ፤ በጎቻችሁ፣ ፍየሎቻችሁና የጋማ ከብቶቻችሁ ብቻ እዚሁ ይቅሩ” አለው።

25ሙሴም እንዲህ አለው፤ “ለአምላካችን ለእግዚአብሔር (ያህዌ) መሥዋዕትና የሚቃጠል መሥዋዕት እንድንሠዋ ፍቀድልን፤ 26እንስሶቻችን ሁሉ አብረው መሄድ አለባቸው። አንድ ሰኰና እንኳ አይቀርም። ከእንስሶቻችን መካከል ለአምላካችን ለእግዚአብሔር (ያህዌ) አምልኮ የምናቀርባቸው ይኖራሉ፤ ሆኖም እዚያ ከመድረሳችን በፊት እግዚአብሔርን (ያህዌ) ለማምለክ የምናቀርባቸው እንስሳት የትኞቹ እንደ ሆኑ አስቀድመን ለይተን ማወቅ አንችልም።”

27ነገር ግን እግዚአብሔር (ያህዌ) የፈርዖንን ልብ አደነደነ፤ ፈርዖንም ሕዝቡን መልቀቅ አልፈቀደም። 28ፈርዖን ሙሴን፣ “ከፊቴ ጥፋ! ሁለተኛ እኔ ዘንድ እንዳትደርስ! ፊቴን ባየህበት በዚያ ቀን ፈጽመህ እንደምትሞት ዕወቅ” አለው።

29ሙሴም፣ “እንዳልከው ይሁን፤ እኔም ዳግመኛ ከፊትህ አልደርስም” አለው።

Swedish Contemporary Bible

2 Moseboken 10:1-29

Gräshoppor täcker landet

1Då sa Herren till Mose: ”Gå tillbaka till farao! Jag har gjort både honom och hans hovmän hårda, för att jag ska kunna göra dessa tecken mitt ibland dem 2och för att du ska kunna berätta för dina barn och barnbarn om de stora gärningar jag gjorde bland egypterna och vilka tecken jag gjorde bland dem. Så ska ni inse att jag är Herren.”

3Mose och Aron gick än en gång till farao och talade med honom: ”Så säger Herren, hebréernas Gud: ’Hur länge tänker du vägra att böja dig för mig? Släpp mitt folk så att de kan tillbe inför mig. 4Om du fortfarande vägrar att släppa iväg dem, ska jag imorgon bitti sända gräshoppor över ditt land. 5De ska täcka marken så att man inte kan se den och de ska äta upp allt som blev kvar efter haglet. De ska gnaga av alla träd som växer på era marker. 6De kommer att fylla alla hus, dina och dina hovmäns hus, ja, alla egypters hus. Något sådant har varken dina fäder eller förfäder sett sedan de bosatte sig i landet.’ ”

Sedan gick Mose därifrån.

7Faraos hovmän frågade honom: ”Hur länge ska den där mannen få vara en snara för oss? Låt folket gå och tillbe Herren, sin Gud! Märker du inte att hela Egypten håller på att gå under?”

8Då lät farao hämta tillbaka Mose och Aron. ”Ni får väl gå och tillbe Herren, er Gud, då!” sa han. ”Men vilka är det som ska gå?”

9”Vi vill gå allesammans, både unga och gamla”, svarade Mose. ”Vi vill ta med våra söner och döttrar och all vår boskap och våra hjordar, eftersom vi ska fira en högtid till Herrens ära.”

10”Ja, nog behöver ni att Herren är med er om ni ska få mig att låta er gå och ta med barnen!” sa farao. ”Det syns att ni har onda tankar! 11Aldrig i livet! Nej, ni män kan gå och tillbe Herren, för det var ju det ni ville.” Och så körde man ut dem därifrån.

12Då sa Herren till Mose: ”Räck ut din hand över Egyptens land, så ska gräshoppor komma över hela landet och äta upp allt som haglet lämnade kvar.”

13Och Mose räckte ut sin stav, och Herren lät en östlig vind blåsa över landet hela dagen och hela natten, och när det blev morgon hade vinden fört med sig gräshopporna. 14De täckte hela landet och slog ner överallt i Egypten. Det var den värsta gräshoppsinvasionen någonsin och man kommer aldrig att få se något liknande igen. 15Gräshopporna täckte hela landet, marken var alldeles svart, och de åt upp all växtlighet och all frukt på träden som fanns kvar efter haglet. De lämnade inget grönt kvar, varken på träden eller på marken någonstans i hela Egypten.

16Då skickade farao ilbud efter Mose och Aron och sa till dem: ”Jag har syndat mot Herren, er Gud, och mot er. 17Förlåt min synd bara den här gången och be Herren, er Gud, att han tar bort denna dödsplåga från mig.”

18Mose gick från farao och bad till Herren, 19och Herren sände en kraftig västanvind som blåste ut alla gräshopporna i Sävhavet10:19 Se 1 Kung 9:26. Sedan fanns det inte en enda gräshoppa kvar i hela Egypten. 20Men Herren gjorde än en gång farao lika orubblig, och han vägrade låta folket gå.

Mörker över landet i tre dagar

21Då sa Herren till Mose: ”Lyft upp din hand mot himlen, så ska jag sända ett väldigt mörker, som man riktigt kan ta på10:21 Grundtextens innebörd är något osäker..” 22Mose lyfte sin hand mot himlen, och det kom ett tjockt mörker över hela Egypten i tre dagar. 23Folk kunde inte se varandra eller röra sig på tre dagar, men där israeliterna bodde var det ljust.

24Farao skickade då efter Mose och sa: ”Gå och fira gudstjänst åt Herren, men låt era får och er boskap stanna här. Barnen får ni ta med er.”

25”Nej”, sa Mose. ”Du måste låta oss ta med slaktoffer och brännoffer som vi kan offra åt Herren, vår Gud. 26Vi måste få med oss vår boskap. Inte en klöv ska lämnas kvar. Vi måste offra av vår boskap åt Herren, vår Gud, och vi vet inte vad för slags offer vi ska offra, förrän vi är där.”

27Men Herren gjorde farao lika hård som förut. Inte heller den här gången lät han dem gå.

28”Försvinn härifrån, och låt mig aldrig se dig igen”, sa farao åt Mose. ”Kommer du hit en gång till ska du dö.”

29”Du har helt rätt”, sa Mose. ”Du kommer aldrig att se mig igen.”