ዘዳግም 9 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዘዳግም 9:1-29

የሕዝቡ አለመታዘዝ

1እስራኤል ሆይ፤ ስማ፤ ሰማይ ጠቀስ ቅጥር ያላቸው ታላላቅ ከተሞች ያሏቸውን፣ ከአንተ ይልቅ ታላቅና ብርቱ የሆኑትን አሕዛብ አስለቅቀህ ለመግባት ዮርዳኖስን አሁን ትሻገራለህ። 2ዔናቃውያን ብርቱና ቁመተ ረጃጅም ሕዝቦች ናቸው፤ ስለ እነርሱ ታውቃለህ፤ “ዔናቃውያንን ማን ሊቋቋማቸው ይችላል?” ሲባልም ሰምተሃል። 3ይሁን እንጂ እንደሚባላ እሳት ከፊትህ ቀድሞ የሚሻገረው አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) መሆኑን ዛሬ ርግጠኛ ሁን፤ እነርሱን ያጠፋቸዋል፤ በፊትህም ድል ያደርጋቸዋል፤ አንተም እግዚአብሔር (ያህዌ) በሰጠህ ተስፋ መሠረት ታስወጣቸዋለህ፤ በፍጥነትም ትደመስሳቸዋለህ። 4አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) እነርሱን ከፊትህ ካስወጣቸው በኋላ፣ “ይህችን ምድር እንድወርስ እግዚአብሔር (ያህዌ) ወደዚህ ያመጣኝ፣ ከጽድቄ የተነሣ ነው” ብለህ በልብህ አታስብ። በዚህ አይደለም፤ እነዚህን አሕዛብ እግዚአብሔር (ያህዌ) ከፊትህ የሚያሳድዳቸው በክፋታቸው ምክንያት ነው። 5ምድራቸውን ገብተህ የምትወርሳት ከጽድቅህ ወይም ከልብህ ቅንነት የተነሣ ሳይሆን፣ ለአባቶችህ ለአብርሃም፣ ለይስሐቅና ለያዕቆብ የማለላቸውን ቃል ለመፈጸም አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) እነዚህን አሕዛብ ከክፋታቸው የተነሣ ከፊትህ ስለሚያባርራቸው ነው። 6ስለዚህ አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ይህችን መልካም ምድር እንድትወርሳት የሚሰጥህ ከጽድቅህ የተነሣ አለመሆኑን አስተውል፤ አንተ ዐንገተ ደንዳና ነህና።

የወርቁ ጥጃ

7አምላክህን እግዚአብሔርን (ኤሎሂም ያህዌ) በምድረ በዳ እንዴት እንዳስቈጣኸው አስታውስ፤ ከቶም አትርሳ። ከግብፅ ከወጣህበት ዕለት አንሥቶ እዚህ ቦታ እስከ ደረስህበት ጊዜ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ላይ እንዳመፅህ ነህ። 8በኮሬብ እግዚአብሔርን (ያህዌ) ለቍጣ አነሣሣችሁት፤ እርሱም እናንተን ሊያጠፋችሁ እጅግ ተቈጣ። 9እኔም የድንጋይ ጽላቶቹን፣ እግዚአብሔር (ያህዌ) ከእናንተ ጋር የገባውን የኪዳን ጽላቶች ለመቀበል ወደ ተራራው በወጣሁ ጊዜ፣ እህል ሳልበላ፣ ውሃም ሳልጠጣ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ቈየሁ፤ 10በእግዚአብሔር ጣት የተጻፈባቸውን ሁለት የድንጋይ ጽላቶች እግዚአብሔር (ያህዌ) ሰጠኝ፤ በተሰበሰባችሁበት ዕለት እግዚአብሔር (ያህዌ) ከተራራው ላይ በእሳት ውስጥ ሆኖ ለእናንተ የነገራችሁ ትእዛዞች ሁሉ በእነርሱ ላይ ነበሩባቸው።

11አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ከተፈጸመ በኋላ፣ እግዚአብሔር (ያህዌ) ሁለቱን የድንጋይ ጽላቶች ማለትም የኪዳኑን ጽላቶች ሰጠኝ። 12ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ)፣ “ተነሣ፤ ከግብፅ ያወጣሃቸው ሕዝብህ ረክሰዋልና ፈጥነህ ከዚህ ውረድ፤ እኔ ካዘዝኋቸው ፈጥነው ፈቀቅ ብለዋል፤ ቀልጦ የተሠራ ጣዖትም ለራሳቸው አበጅተዋል” ብሎ ነገረኝ።

13ደግሞም እግዚአብሔር (ያህዌ) እንዲህ አለኝ፤ “ይህን ሕዝብ አይቼዋለሁ፤ በርግጥ ዐንገተ ደንዳና ሕዝብ ነው፣ 14አጠፋቸውና ስማቸውንም ከሰማይ በታች እደመስሰው ዘንድ ተወኝ፤ አንተንም ከእነርሱ ይልቅ ብርቱና ብዙ ሕዝብ አደርግሃለሁ።”

15ስለዚህ ተራራው በእሳት እየተቀጣጠለ ሳለ፣ ሁለቱን የቃል ኪዳን ጽላቶች በሁለቱም እጆቼ እንደ ያዝሁ9፥15 ወይም፣ ሁለቱም የቃል ኪዳን ጽላቶች ከእኔ ጋር ነበሩ፤ አንዱም በአንዱ፣ ሌላውም በሌላው እጄ ነበር ተብሎ መተርጐም ይችላል። ከተራራው ተመልሼ ወረድሁ። 16በርግጥ በአምላካችሁ በእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ላይ ኀጢአት ሠርታችሁ እንደ ነበር ተመለከትሁ፤ ቀልጦ የተሠራ የጥጃ ምስልም ለራሳችሁ አበጃችሁ፤ እግዚአብሔር (ያህዌ) እናንተን ካዘዛችሁ መንገድ በፍጥነት ወጥታችሁ ነበር። 17ስለዚህ ሁለቱን ጽላቶች ወስጄ ከእጆቼ አሽቀንጥሬ በፊታችሁ ሰባበርኋቸው።

18ከዚያም በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ክፉ ነገርን በመፈጸም ለቍጣ እንዲነሣሣ የሚያደርገውን ኀጢአት ሁሉ ስለ ሠራችሁ፣ እህል ውሃ ሳልቀምስ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት እንደ ገና በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት በግምባሬ ተደፋሁ። 19እናንተን ሊያጠፋችሁ ክፉኛ ተቈጥቶ ነበርና፣ እኔም የእግዚአብሔርን (ያህዌ) ቍጣና መዓት ፈራሁ፤ እግዚአብሔር (ያህዌ) ግን እንደ ገና ሰማኝ። 20እግዚአብሔር (ያህዌ) አሮንን ሊያጠፋው ክፉኛ ተቈጥቶ ነበር፤ በዚያን ጊዜ ለአሮንም ጸለይሁ። 21ደግሞም ያን የኀጢአት ሥራችሁን፣ አበጅታችሁት የነበረውን ጥጃ ወስጄ በእሳት አቃጠልሁት፤ ከዚያም ሰባብሬ እንደ ትቢያ ዱቄት እስኪሆን ድረስ ፈጭቼ ከተራራው በሚወርደው ጅረት ውስጥ በተንሁት።

22በተቤራም፣ በማሳህና በቂብሮት ሐታአዋ እግዚአብሔርን (ያህዌ) አስቈጣችሁት።

23እግዚአብሔር (ያህዌ) ከቃዴስ በርኔ ባስወጣችሁ ጊዜ፣ “ውጡ፤ የሰጠኋችሁንም ምድር ርስት አድርጋችሁ ውረሷት” አላችሁ። እናንተ ግን በአምላካችሁ በእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ትእዛዝ ላይ ዐመፃችሁ፤ እርሱን አልታመናችሁበትም፤ አልታዘዛችሁትምም። 24እኔ እናንተን ካወቅኋችሁ ጊዜ ጀምሮ፣ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ላይ እንዳመፃችሁ ናችሁ።

25እግዚአብሔር (ያህዌ) እናንተን እንደሚያጠፋችሁ ተናግሮ ስለ ነበር፣ በእነዚያ አርባ ቀናትና አርባ ሌሊቶች በእግዚአብሔር ፊት በግንባሬ ተደፋሁ፤ 26እንዲህም በማለት ወደ እግዚአብሔር (ያህዌ) ጸለይሁ፤ “ጌታ እግዚአብሔር ሆይ (አዶናይ ያህዌ) በታላቅ ኀይልህ የተቤዠኸውንና በኀያል ክንድህ ከግብፅ ያወጣኸውን፣ ያንተ ርስት የሆነውን ሕዝብህን አታጥፋ። 27ባሪያዎችህን አብርሃምን፣ ይስሐቅንና ያዕቆብን ዐስብ፤ የዚህን ሕዝብ ልበ ደንዳናነት፣ ክፋትና ኀጢአት አትመልከት። 28አለዚያ እኛን ካመጣህበት ምድር ያሉ ሰዎች ‘እግዚአብሔር (ያህዌ) ተስፋ ወደ ሰጣቸው ምድር ሊያገባቸው ስላልቻለና ስለ ጠላቸው፣ በምድረ በዳ ሊገድላቸው አወጣቸው’ ይላሉ። 29ነገር ግን እነርሱ በታላቅ ኀይልህና በተዘረጋች ክንድህ ያወጣሃቸው ሕዝብህና ርስትህ ናቸው።”

Thai New Contemporary Bible

เฉลยธรรมบัญญัติ 9:1-29

ไม่ใช่เพราะความชอบธรรมของอิสราเอล

1อิสราเอลเอ๋ย จงฟังเถิด บัดนี้ท่านกำลังจะข้ามแม่น้ำจอร์แดนเข้าไปยึดครองดินแดนของชนชาติต่างๆ ที่ฟากข้างโน้นซึ่งยิ่งใหญ่และเข้มแข็งกว่าท่านมากนัก เมืองของเขาใหญ่โต มีปราการสูงเสียดฟ้า 2พวกเขาสูงใหญ่และแข็งแรงเพราะพวกเขาคือมนุษย์ยักษ์อานาค! ท่านรู้และเคยได้ยินผู้คนกล่าวกันว่า “ใครจะต่อสู้พวกมนุษย์ยักษ์อานาคได้?” 3แต่วันนี้จงมั่นใจว่าพระยาห์เวห์พระเจ้าของพวกท่านคือผู้ที่จะนำหน้าท่านไปเหมือนไฟเผาผลาญ พระองค์จะทรงทำลายล้างพวกเขา ปราบพวกเขาลงต่อหน้าท่าน และท่านจะขับไล่และกวาดล้างพวกเขาออกไปโดยเร็ว ตามที่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงสัญญาไว้กับท่าน

4เมื่อพระยาห์เวห์พระเจ้าของท่านได้ทรงขับไล่พวกเขาออกไปพ้นหน้าท่านแล้ว อย่านึกในใจว่า “องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงนำเรามายึดครองดินแดนนี้เพราะความชอบธรรมของเรา” เปล่าเลย เป็นเพราะความชั่วร้ายของชนชาติเหล่านี้ต่างหาก องค์พระผู้เป็นเจ้าจึงทรงขับไล่พวกเขาออกไปต่อหน้าท่าน 5ที่พวกท่านจะเข้ายึดครองดินแดนของเขาได้ ไม่ใช่เพราะความชอบธรรมหรือความสัตย์ธรรมของท่าน แต่เป็นเพราะความชั่วร้ายของชนชาติเหล่านี้ พระยาห์เวห์พระเจ้าของท่านทั้งหลายจึงทรงขับไล่พวกเขาออกไปต่อหน้าท่าน เพื่อให้เป็นไปตามคำปฏิญาณที่ทรงให้ไว้กับบรรพบุรุษของท่าน คืออับราฮัม อิสอัค และยาโคบ 6พึงเข้าใจเถิดว่าที่พระยาห์เวห์พระเจ้าของท่านประทานดินแดนอันอุดมสมบูรณ์นี้ให้ท่านครอบครอง ไม่ใช่เพราะความชอบธรรมของท่าน เพราะที่จริงท่านเป็นประชากรที่ดื้อรั้นหัวแข็ง

ลูกวัวทองคำ

7จงระลึกเสมอและอย่าลืมที่ท่านเคยยั่วยุพระพิโรธของพระยาห์เวห์พระเจ้าของท่านในถิ่นกันดาร ตั้งแต่วันที่ท่านออกจากอียิปต์จนมาถึงที่นี่ ท่านกบฏขัดขืนองค์พระผู้เป็นเจ้าเสมอมา 8ท่านยั่วยุพระพิโรธขององค์พระผู้เป็นเจ้าที่โฮเรบ ทำให้พระองค์กริ้วจนจะทำลายท่านอยู่แล้ว 9ครั้งนั้นข้าพเจ้าขึ้นไปบนภูเขาเพื่อรับแผ่นศิลาจารึกพันธสัญญาซึ่งองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงทำไว้กับพวกท่าน ข้าพเจ้าอยู่บนภูเขาสี่สิบวันสี่สิบคืน ไม่ได้รับประทานอาหารหรือดื่มน้ำเลย 10องค์พระผู้เป็นเจ้าประทานศิลาสองแผ่นซึ่งจารึกด้วยนิ้วของพระองค์ เป็นบทบัญญัติทั้งปวงที่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงประกาศออกมาจากไฟบนภูเขาแก่ท่านในวันชุมนุมประชากรนั้น

11เมื่อครบสี่สิบวันสี่สิบคืน องค์พระผู้เป็นเจ้าประทานศิลาสองแผ่นเป็นศิลาพันธสัญญาแก่ข้าพเจ้า 12แล้วองค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสสั่งข้าพเจ้าว่า “จงลงไปจากที่นี่โดยเร็วเพราะประชากรของเจ้าที่เจ้านำออกมาจากอียิปต์ได้เสื่อมทรามไปแล้ว พวกเขาหันเหจากสิ่งที่เราบัญชาไปอย่างรวดเร็ว และหล่อโลหะทำรูปเคารพขึ้นมา”

13และองค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับข้าพเจ้าว่า “เราได้เห็นชนชาตินี้แล้ว เป็นชนชาติที่ดื้อรั้นหัวแข็งจริงๆ! 14อย่ามาห้ามเรา เพราะเราจะทำลายและลบชื่อพวกเขาออกจากใต้ฟ้า และเราจะทำให้เจ้าเป็นชนชาติที่เข้มแข็งและมีจำนวนมากมายกว่าพวกเขา”

15ข้าพเจ้าจึงกลับลงมาจากภูเขาซึ่งมีไฟลุกโชน และถือศิลาแห่งพันธสัญญาสองแผ่นมาด้วย 16เมื่อข้าพเจ้ามองดูก็เห็นว่าท่านได้ทำบาปต่อพระยาห์เวห์พระเจ้าของท่าน ท่านได้หล่อรูปลูกวัวไว้เป็นรูปเคารพสำหรับพวกท่านเอง ท่านหันออกจากทางที่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงบัญชานั้นอย่างรวดเร็ว 17ข้าพเจ้าจึงเหวี่ยงแผ่นศิลาทั้งสองทิ้ง ทำให้ศิลาแตกเป็นเสี่ยงๆ ต่อหน้าต่อตาท่าน

18แล้วอีกครั้งหนึ่งที่ข้าพเจ้าหมอบกราบลงต่อหน้าองค์พระผู้เป็นเจ้าสี่สิบวันสี่สิบคืน ไม่กินไม่ดื่มอะไรเพราะบาปทั้งปวงที่ท่านได้ทำ ท่านได้ทำสิ่งที่ชั่วร้ายในสายพระเนตรขององค์พระผู้เป็นเจ้าเป็นการยั่วยุให้พระองค์ทรงพระพิโรธ 19ข้าพเจ้าเกรงกลัวพระพิโรธโกรธกริ้วขององค์พระผู้เป็นเจ้าเพราะพระองค์กริ้วจนจะทำลายท่านอยู่แล้ว แต่องค์พระผู้เป็นเจ้าก็ทรงฟังข้าพเจ้าอีกครั้ง 20และองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงพระพิโรธอาโรนมากจนจะทรงทำลายเขา แต่ในครั้งนั้นข้าพเจ้าอธิษฐานเผื่ออาโรนด้วย 21ข้าพเจ้าจึงเอาสิ่งผิดบาปของพวกท่านคือรูปลูกวัวซึ่งท่านสร้างขึ้นนั้นเผาทิ้งและบดเป็นผุยผง ทิ้งลงในลำธารซึ่งไหลลงมาจากภูเขา

22ท่านยังได้ทำให้องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงพระพิโรธอีกที่ทาเบราห์ ที่มัสสาห์ และที่ขิบโรทหัทธาอาวาห์

23เมื่อองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงส่งท่านออกจากคาเดชบารเนียและตรัสสั่งว่า “จงเข้าไปครอบครองดินแดนที่เราให้เจ้า” แต่ท่านกบฏขัดขืนพระบัญชาของพระยาห์เวห์พระเจ้าของท่าน ท่านไม่ไว้วางใจและไม่เชื่อฟังพระองค์ 24ท่านกบฏต่อองค์พระผู้เป็นเจ้าเสมอมาตั้งแต่ข้าพเจ้ารู้จักท่านแล้ว

25ข้าพเจ้าจึงหมอบกราบลงต่อหน้าองค์พระผู้เป็นเจ้าตลอดสี่สิบวันสี่สิบคืน เพราะองค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่าจะทรงทำลายท่าน 26ข้าพเจ้าอธิษฐานต่อองค์พระผู้เป็นเจ้าว่า “ข้าแต่พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิต ขออย่าทำลายประชากรของพระองค์อันเป็นกรรมสิทธิ์ของพระองค์เองซึ่งทรงไถ่โดยฤทธานุภาพอันยิ่งใหญ่ และทรงนำออกมาจากอียิปต์โดยพระหัตถ์อันทรงฤทธิ์ 27ขอทรงระลึกถึงอับราฮัม อิสอัค และยาโคบผู้รับใช้ของพระองค์ โปรดทรงมองข้ามความดื้อรั้นหัวแข็ง ความชั่วร้าย และบาปของคนเหล่านี้ 28มิฉะนั้นประเทศซึ่งพระองค์ทรงนำพวกเราออกมาจะกล่าวว่า ‘เพราะองค์พระผู้เป็นเจ้าไม่สามารถพาพวกเขาไปยังดินแดนที่ทรงสัญญาไว้ และเพราะพระองค์ทรงเกลียดพวกเขา จึงทรงพาพวกเขาเข้าไปตายในถิ่นกันดาร’ 29แต่พวกเขาเป็นประชากรของพระองค์ เป็นกรรมสิทธิ์ของพระองค์ซึ่งทรงนำออกมาโดยฤทธานุภาพอันยิ่งใหญ่และพระกรที่เหยียดออก”