ዘዳግም 7 – NASV & NSP

New Amharic Standard Version

ዘዳግም 7:1-26

አሕዛብን ማስወጣት

1አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ልትወርሳት ወደምትገባባት ምድር በሚያመጣህና ብዙዎችን ከአንተ የሚበልጡ ታላላቆችና ብርቱዎች የሆኑትን ሰባቱን አሕዛብ፦ ኬጢያውያንን፤ ጌርጌሳውያንን፣ አሞራውያንን፣ ከነዓናውያንን፣ ፌርዛውያንን፣ ኤዊያውያንንና ኢያቡሳውያንን ከፊትህ በሚያስወጣቸው ጊዜ፣ 2አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) በእጅህ አሳልፎ በሰጠህና አንተም ድል ባደረግሃቸው ጊዜ፣ ሁሉንም ፈጽመህ ደምስሳቸው7፥2 በዚህና በቍጥር 26 ላይ የዕብራይስጡ ቃል አንድን ነገር ወይም አንድን ሰው ሙሉ በሙሉ በማጥፋት ለእግዚአብሔር መስጠትን የሚያሳይ ነው።፤ ከእነርሱ ጋር አትዋዋል፤ አትራራላቸውም። 3ከእነርሱ ጋር ጋብቻ አታድርግ፤ ሴት ልጆችህን ለወንድ ልጆቻቸው አትስጥ፤ ወይም ለወንድ ልጆችህ ሴት ልጆቻቸውን አታምጣ፤ 4ምክንያቱም እኔን ከመከተል ልጆችህን መልሰው ሌሎችን አማልክት እንዲያመልኩ ስለሚያደርጉና ከዚህም የተነሣ የእግዚአብሔር (ያህዌ) ቍጣ በላይህ ነዶ፣ ፈጥኖ ስለሚያጠፋህ ነው። 5እንግዲህ በእነርሱ ላይ የምታደርጉት ይህ ነው፤ መሠዊያዎቻቸውን አፈራርሱ፤ የማምለኪያ ዐምዶቻቸውን7፥5 እዚህ ላይና በዚሁ መጽሐፍ በሌላ ስፍራ አሼራ የምትባለውን ጣዖት ምስል የሚያመለክት ነው። ሰባብሩ፤ የአሼራ ምስል ዐምዶቻቸውን ቍረጡ፤ ጣዖቶቻቸውንም በእሳት አቃጥሉ። 6አንተ ለአምላክህ ለእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ቅዱስ ሕዝብ ስለ ሆንህ፣ አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) የራሱ ሕዝብ፣ ርስትም እንድትሆንለት በምድር ላይ ከሚኖሩ ሕዝቦች ሁሉ መረጠህ።

7እግዚአብሔር (ያህዌ) እናንተን የወደዳችሁና የመረጣችሁ ከሌሎች ሕዝቦች በቍጥር ስለ በዛችሁ አይደለም፤ ቍጥራችሁማ ከሕዝቦች ሁሉ እጅግ አነስተኛ ነበር። 8ነገር ግን እናንተን በብርቱ እጅ ያወጣችሁ፣ ከባርነት ምድርና ከግብፅ ንጉሥ ከፈርዖን መዳፍ የተቤዣችሁ፣ እግዚአብሔር (ያህዌ) እናንተን ስለ ወደዳችሁና ለአባቶቻችሁ የማለላቸውን መሐላ ስለ ጠበቀ ነው። 9ስለዚህም አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) አምላክ (ኤሎሂም) መሆኑን ዕወቅ፤ እርሱ ለሚወድዱትና ትእዛዞቹን ለሚጠብቁት የፍቅሩን ኪዳን እስከ ሺሕ ትውልድ ድረስ የሚጠብቅ ታማኝ አምላክ (ኤሎሂም) ነው። 10ነገር ግን፣ የሚጠሉትን ዐይናቸው እያየ ይበቀላቸዋል፤ የሚጠሉትን ዐይናቸው እያየ ለመበቀል አይዘገይም። 11ስለዚህ በዛሬው ቀን የምሰጥህን ትእዛዙን፣ ሥርዐቱንና ሕግጋቱን ለመከተል ጥንቃቄ አድርግ።

12እነዚህን ሕግጋት ብታዳምጥና በጥንቃቄ ብትጠብቃቸው፣ አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ለአባቶችህ እንደ ማለላቸው ከአንተ ጋር የገባውን የፍቅር ኪዳኑን ይጠብቃል። 13ይወድሃል፤ ይባርክሃል፤ ያበዛሃልም። ለአንተ ለመስጠት ለአባቶችህ በማለላቸው ምድር የማሕፀንህን ፍሬ፣ የምድርህን ሰብል፣ እህልህን፣ አዲሱን ወይንና ዘይት፤ የከብት መንጋህን ጥጆች፣ የበግና የፍየል መንጋህን ግልገሎች ይባርካል። 14ከሕዝቦች ሁሉ የበለጠ አንተ ትባረካለህ፤ ከአንተ ወይም ከከብቶችህ መካከል የማይወልድ ወንድ ወይም ሴት አይኖርም። 15እግዚአብሔር (ያህዌ) ከማናቸውም በሽታ ነጻ ያደርግሃል፤ በግብፅ የምታውቃቸውን እነዚያን አሠቃቂ በሽታዎች በሚጠሉህ ሁሉ ላይ እንጂ በአንተ ላይ አያመጣብህም። 16አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) በእጅህ አሳልፎ የሚሰጥህን ሕዝቦች ሁሉ ማጥፋት አለብህ፤ አትዘንላቸው፤ ወጥመድ ስለሚሆኑብህም አማልክታቸውን አታምልክ።

17“እነዚህ አሕዛብ ከእኛ ይልቅ ጠንካሮች ስለ ሆኑ፣ እንዴት አድርገን እናስወጣቸዋለን?” ብለህ በልብህ ታስብ ይሆናል።

18ነገር ግን አትፍራቸው፤ አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) በፈርዖንና በግብፅ ሁሉ ላይ ያደረገውን በሚገባ አስታውስ። 19ታላላቅ ፈተናዎችን፣ ታምራዊ ምልክቶችንና ድንቅ ነገሮችን አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) አንተን ያወጣበትን ብርቱ እጅና የተዘረጋች ክንድ በገዛ ዐይንህ አይተሃል። አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) አሁን በምትፈራቸው ሕዝቦች ሁሉ ላይ ያንኑ ያደርጋል። 20ይልቁንም አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) በሕይወት ተርፈው፣ ከአንተ የተደበቁት እንኳ እስኪጠፉ ድረስ በመካከላቸው ተርብ ይሰድድባቸዋል። 21በመካከልህ ያለው አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ታላቅና የሚያስፈራ አምላክ (ኤሎሂም) ስለሆነ አያስደንግጡህ። 22አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) እነዚህን ሕዝቦች ጥቂት በጥቂት ከፊትህ ያስወጣቸዋል፤ የዱር አራዊቱ ቍጥር በአካባቢህ እንዳይበራከት ሁሉንም በአንድ ጊዜ ማጥፋት አይፈቀድልህም፤ 23አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ግን እስኪጠፉ ድረስ ከባድ ትርምስ ፈጥሮባቸው በእጅህ አሳልፎ ይሰጥሃል። 24ነገሥታታቸውን በእጅህ ይጥላቸዋል፤ ስማቸውንም ከሰማይ በታች ታጠፋለህ። እስክትደመስሳቸው ድረስ አንተን መቋቋም የሚችል አንድም ሰው የለም። 25የአማልክታቸውን ምስሎች በእሳት አቃጥል፤ በላያቸው የሚገኘውን ብርና ወርቅ አትመኝ፤ ለራስህ አታድርግ፤ አለዚያ በአምላክህ በእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ዘንድ አስጸያፊ ስለሆነ ያሰናክልሃል። 26አስጸያፊ ነገርን ወደ ቤትህ ወይም ወደ ራስህ አታምጣ፤ አለዚያ አንተም እንደ እርሱ ለጥፋት ትዳረጋለህ፤ ፈጽመህ ጥላው፤ ተጸየፈውም፤ ለጥፋት የተለየ ነውና።

New Serbian Translation

5. Мојсијева 7:1-26

Потпуно одвојење од многобожачких народа

1Јер кад те Господ, Бог твој, уведе у земљу коју идеш да освојиш, па истераш пред собом многе народе: Хетите, Гергешане, Аморејце, Хананце, Фережане, Евејце, Јевусејце – седам народа бројнијих и јачих од тебе – 2и кад их Господ, Бог твој, преда у твоје руке, и ти их поразиш, изврши над њима клето уништење. Не склапај савез са њима, нити им исказуј милости. 3Не ступај у брак с њима. Своје ћерке не удаји за њихове синове, нити узимај њихове ћерке за своје синове, 4јер ће оне одвратити твоје синове од мене, да би служили другим боговима. Тада ће Господњи гнев планути против вас, па ће те брзо истребити. 5Него, овако ћете поступати с њима: порушите њихове жртвенике, оборите њихове стубове, посеците њихове Аштартине стубове и спалите њихове кипове.

Израиљ – народ посвећен Богу

6Јер, ти си народ посвећен Господу, Богу своме. Тебе је Господ, Бог твој, изабрао од свих народа који су на земљи да будеш његов народ, његова најдрагоценија својина. 7Господ вас није заволео и изабрао зато што сте бројнији од других народа – у ствари, ви сте били најмањи од свих народа – 8него зато што вас Господ воли и држи заклетву којом се заклео вашим оцима. Зато вас је Господ извео моћном руком и избавио вас из куће ропства, из руку фараона, цара египатскога. 9Стога, знај да је Господ, Бог твој, прави Бог, верни Бог који држи свој савез и исказује милост до хиљаду колена онима који га воле и држе његове заповести.

10А онима који га мрзе узвраћа понаособ и уништава их;

ономе који га мрзи узвраћа без одлагања.

11Зато, држи заповести, прописе и уредбе које ти данас заповедам да их вршиш.

Благослови за послушност

12Ако будеш слушао ове уредбе, те их будеш држао и вршио, Господ, Бог твој, ће држати свој савез и милост, за које се заклео твојим оцима. 13Тада ће те волети и благосиљати те и умножити те. Благословиће плод твоје утробе, плод твоје земље, твоје жито, младо вино и уље, телад твојих крава и прираст твоје ситне стоке, на земљи за коју се заклео твојим оцима да ће је дати теби. 14Од свих народа ти ћеш бити најблагословенији. Међу тобом неће бити јаловога ни јалове, нити међу твојом стоком. 15Господ ће отклонити од тебе сваку болест. Он те неће ударити опаким пошастима египатским за које знаш, али ће ударити њима оне који те мрзе. 16Уништи све народе које ти је предао Господ, Бог твој. Нека се твоје око не сажаљева над њима. Не служи њиховим боговима, јер ће ти то бити замка.

17Можда ћеш рећи у себи: ’Ови народи су бројнији од мене. Како ћу их истерати?’ 18Не бој их се, него се сети шта је Господ, Бог твој, учинио фараону и целом Египту! 19Својим си очима видео велике невоље, знакове и чудеса, снажну руку и испружену мишицу, којима те је Господ, Бог твој, извео. Тако ће Господ, Бог твој, учинити са свим народима којих се бојиш. 20Шта више, Господ, Бог твој, ће послати стршљене на њих, док не изгину преостали који се буду крили од тебе. 21Не плаши их се, јер је Господ, Бог твој, у твојој средини. Он је Бог, велики и страшни! 22Господ, Бог твој, изгониће ове народе пред тобом мало по мало. Нећеш моћи да их брзо истребиш, да се звери не би размножиле против тебе. 23Господ, Бог твој, ће их предати теби; унеће међу њих велику пометњу, док не буду истребљени. 24Он ће предати у твоје руке њихове цареве да истребиш њихово име под небом. Нико неће моћи да ти се супротстави док их не уништиш. 25Кипове њихових богова спали! Не пожели њихово сребро и злато што је на њима; не узимај га да не би упао у замку, јер је то одвратно Господу, Богу твоме. 26Не уноси грдобу7,26 Грдоба је погрдна реч за идола. у своју кућу, да не би као она био ударен клетим уништењем. Нека ти буде мрска и одвратна, јер је одређена за клето уништење.