ዘዳግም 34 – NASV & NIVUK

New Amharic Standard Version

ዘዳግም 34:1-12

የሙሴ መሞት

1ሙሴ ከሞዓብ ሜዳ ተነሥቶ ለኢያሪኮ ትይዩ ወደ ሆነው ፈስጋ ጫፍ፣ ወደ ናባው ተራራ ወጣ። በዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) ምድሪቱን ሁሉ አሳየው፤ ይኸውም ከገለዓድ እስከ ዳን፣ 2ንፍታሌምን ሁሉ፣ የኤፍሬምንና የምናሴን ግዛት፣ እስከ ምዕራብ ባሕር34፥2 ይኸውም የሜዲትራንያን ባሕር ነው። ድረስ ያለውን የይሁዳን ምድር ሁሉ፣ 3ኔጌብንና የዘንባባ ከተማ ከሆነችው ከኢያሪኮ ሸለቆ እስከ ዞዓር ያለውን ምድር ሁሉ ነው። 4ከዚያም በኋላ እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን “ለአብርሃም፣ ለይስሐቅና ለያዕቆብ፣ ‘ለዘሮቻችሁ እሰጣለሁ’ ብዬ በመሐላ ቃል የገባሁላቸው ምድር ይህች ናት። በዐይንህ እንድታያት አድርጌአለሁ፤ ነገር ግን ወደዚያ አትሻገርም” አለው።

5እግዚአብሔር (ያህዌ) እንደ ተናገረው የእግዚአብሔር (ያህዌ) አገልጋይ ሙሴ በሞዓብ ምድር ሞተ። 6በሞዓብ ምድር በቤተ ፌጎር ፊት ለፊት ባለው ሸለቆ ቀበረው34፥6 ወይም፣ ተቀበረ ብሎ መተርጐም ይቻላል።፤ ይሁን እንጂ መቃብሩ የት እንደ ሆነ እስከ ዛሬ ማንም አያውቅም። 7ሙሴ በሞተ ጊዜ ዕድሜው መቶ ሃያ ዓመት ነበር፤ ሆኖም ዐይኑ አልፈዘዘም፤ ጕልበቱም አልደከመም። 8የልቅሶውና የሐዘኑ ጊዜ እስኪያበቃ ድረስ፣ እስራኤላውያን በሞዓብ ሜዳ ሠላሳ ቀን አለቀሱለት።

9ሙሴ እጆቹን ጭኖበት ነበርና፣ የነዌ ልጅ ኢያሱ በጥበብ መንፈስ ተሞላ። ስለዚህ እስራኤላውያን አደመጡት፤ እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን አዝዞት የነበረውንም ሁሉ አደረጉ።

10እግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ለፊት ያወቀው እንደ ሙሴ ያለ ነቢይ ከዚያ ወዲህ በእስራኤል አልተነሣም። 11እግዚአብሔር (ያህዌ) ልኮት፣ እነዚያን ታምራዊ ምልክቶችና ድንቆች ሁሉ በግብፅ በፈርዖን፣ በሹማምቱና በምድሪቱ ሁሉ ላይ እንዲያደርግ የላከውን ያደረገ ማንም ሰው አልነበረም። 12ሙሴ በእስራኤል ሁሉ ፊት ያሳየውን ታላቅ ኀይል ያሳየ ወይም ያደረገውን አስፈሪ ተግባር የፈጸመ ማንም ሰው የለም።

New International Version – UK

Deuteronomy 34:1-12

The death of Moses

1Then Moses climbed Mount Nebo from the plains of Moab to the top of Pisgah, opposite Jericho. There the Lord showed him the whole land – from Gilead to Dan, 2all of Naphtali, the territory of Ephraim and Manasseh, all the land of Judah as far as the Mediterranean Sea, 3the Negev and the whole region from the Valley of Jericho, the City of Palms, as far as Zoar. 4Then the Lord said to him, ‘This is the land I promised on oath to Abraham, Isaac and Jacob when I said, “I will give it to your descendants.” I have let you see it with your eyes, but you will not cross over into it.’

5And Moses the servant of the Lord died there in Moab, as the Lord had said. 6He buried him34:6 Or He was buried in Moab, in the valley opposite Beth Peor, but to this day no-one knows where his grave is. 7Moses was a hundred and twenty years old when he died, yet his eyes were not weak nor his strength gone. 8The Israelites grieved for Moses in the plains of Moab thirty days, until the time of weeping and mourning was over.

9Now Joshua son of Nun was filled with the spirit34:9 Or Spirit of wisdom because Moses had laid his hands on him. So the Israelites listened to him and did what the Lord had commanded Moses.

10Since then, no prophet has risen in Israel like Moses, whom the Lord knew face to face, 11who did all those signs and wonders the Lord sent him to do in Egypt – to Pharaoh and to all his officials and to his whole land. 12For no-one has ever shown the mighty power or performed the awesome deeds that Moses did in the sight of all Israel.