ዘዳግም 32 – NASV & KLB

New Amharic Standard Version

ዘዳግም 32:1-52

1ሰማያት ሆይ፤ አድምጡ፤ እኔም እናገራለሁ፤

ምድር ሆይ፤ አንቺም የአፌን ቃል ስሚ።

2ትምህርቴ እንደ ዝናብ ትውረድ፤

ቃሌም እንደ ጤዛ ይንጠባጠብ፤

በቡቃያ ሣር ላይ እንደ ካፊያ፣

ለጋ ተክልም ላይ እንደ ከባድ ዝናብ ይውረድ።

3እኔ የእግዚአብሔርን (ያህዌ) ስም ዐውጃለሁ፤

የአምላካችንን (ኤሎሂም) ታላቅነት አወድሱ!

4እርሱ ዐለት፣ ሥራውም ፍጹም ነው፤

መንገዱም ሁሉ ትክክል ነው፤

የማይሳሳት ታማኝ አምላክ፣

ቀጥተኛና ጻድቅ አምላክም እርሱ ነው።

5በእርሱ ላይ ክፋት ፈጽመዋል፤ ከነውራቸው የተነሣ ከእንግዲህ ልጆቹ አይደሉም፤

ወልጋዳና ጠማማ ትውልዶች ናቸው32፥5 ወይም የተጣመሙት እነርሱ እንጂ የእርሱ ልጆች አይደሉም

6አንተ ተላላና ጥበብ የጐደለህ ሕዝብ፣

ለእግዚአብሔር (ለያህዌ) የምትመልስለት በዚህ መንገድ ነውን?

አባትህ ፈጣሪህ32፥6 ወይም ያወጣህ አባትህ።

የሠራህና ያበጀህ እርሱ አይደለምን?

7የጥንቱን ዘመን አስታውስ፤

አባትህን ጠይቅ፤ ይነግርሃልም፤

ሽማግሌዎችህንም ጠይቅ፤ ያስረዱሃል።

8ልዑል ለአሕዛብ ርስታቸውን በሰጠ ጊዜ፣

የሰውንም ዘር በለያየ ጊዜ፣

በእስራኤል ልጆች32፥8 የማሶሬቱ ቅጅ፣ የሙት ባሕር ጥቅልል እንዲሁም የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም፣ የእግዚአብሔር ልጆች ይላሉ። ቍጥር ልክ፣

የአሕዛብን ርስት ድንበር ለየ፤

9የእግዚአብሔር (ያህዌ) ድርሻ የገዛ ሕዝቡ፣

ያዕቆብ የተለየ ርስቱ ነውና።

10እርሱን በምድረ በዳ፣

ባዶና ጭው ባለ በረሓ ውስጥ አገኘው፤

ጋሻ ሆነው፤ ተጠነቀቀለትም፤

እንደ ዐይኑ ብሌን ጠበቀው።

11ንስር ጐጆዋን በትና፣

በጫጩቶቿም ላይ እንደምትረብብ፣

እነርሱን ለመያዝ ክንፎቿን እንደምትዘረጋ፣

በክንፎቿም እንደምትሸከማቸው፣

12እግዚአብሔር (ያህዌ) ብቻ መራው፤

ምንም ባዕድ አምላክ አብሮት አልነበረም።

13በምድር ከፍታ ላይ አወጣው፤

የዕርሻንም ፍሬ መገበው፤

ከዐለት ድንጋይ ማር አበላው፤

ከባልጩትም ድንጋይ ዘይት መገበው።

14የላሙንና የበጉን መንጋ ቅቤና ወተት፣

የሰቡትን በጎችና ፍየሎች፣

የባሳንን ምርጥ አውራ በግ፣

መልካም የሆነውንም ስንዴ፣

ማለፊያውንም የወይን ጠጅ።

15ይሹሩን32፥15 ይሹሩን ማለት ቅን ወይም ትክክለኛ ማለት ሲሆን፣ ይኸውም እስራኤልን የሚያሳይ ነው። ወፈረ፤ ረገጠ፤

ጠገበ፤ ሰውነቱ ደነደነ፤ ለሰለሰ፤

የፈጠረውንም አምላክ (ኤሎሂም) ተወ፤

መጠጊያ ዐለት የሆነውን አዳኙንም ናቀ።

16በባዕዳን አማልክታቸው አስቀኑት፤

በአጸያፊ ጣዖቶቻቸውም አስቈጡት።

17አምላክ ላልሆኑ አጋንንት፦

ላላወቋቸው አማልክት፣

ከጊዜ በኋላ ለተነሡ አማልክት፣

አባቶቻችሁ ላልፈሯቸው አማልክት ሠዉ።

18አባት የሆነህን ዐለት ከዳኸው፤

የወለደህን አምላክ ረሳኸው።

19እግዚአብሔር (ያህዌ) ይህን አይቶ ናቃቸው፤

በወንድና በሴት ልጆቹ ተቈጥቷልና።

20እርሱም፣ “ፊቴን ከእነርሱ እሰውራለሁ፤

መጨረሻቸው ምን እንደሚሆንም አያለሁ” አለ፤

ጠማማ ትውልድ፣

የማይታመኑም ልጆች ናቸውና።

21አምላክ ባልሆነው አስቀኑኝ፤

በከንቱ ጣዖቶቻቸው አስቈጡኝ።

እኔም ሕዝብ ባልሆነው አስቀናቸዋለሁ።

በማያስተውልም ሕዝብ አስቈጣቸዋለሁ።

22በቍጣዬ እሳት ተቀጣጥሏልና፤

እርሱ እስከ ሲኦል ዘልቆ ይነድዳል።

ምድርን እስከ ሰብሏ ይበላል፤

የተራሮችንም መሠረት ያቀጣጥላል።

23“በመዓት ላይ መዓት አመጣባቸዋለሁ።

ፍላጻዬንም በእነርሱ ላይ እጨርሳለሁ።

24የሚያጠፋ ራብ፣ በልቶ የሚጨርስ ቸነፈርና ከባድ

መቅሠፍት እሰድድባቸዋለሁ፤

የአራዊትን ሹል ጥርስ፣ በምድር የሚሳብ የእባብ መርዝም

እሰድድባቸዋለሁ።

25ሰይፍ መንገድ ላይ ያስቀራቸዋል፤

ቤታቸውም ውስጥ ድንጋጤ ይነግሣል፤

ጕልማሳውና ልጃገረዷ፣

ሕፃኑና ሽማግሌው ይጠፋሉ።

26እበትናቸዋለሁ፤ ከሰዎችም መካከል መታሰቢያቸውን

አጠፋለሁ አልሁ፤

27ነገር ግን ጠላቶቻቸው እንዳይታበዩ፣

‘ድል ያደረገችው እጃችን እንጂ፣

እግዚአብሔር (ያህዌ) ይህን ሁሉ አላደረገም’ እንዳይሉ፣

የጠላትን መነሣሣት ሠጋሁ።”

28አእምሮ የጐደላቸው፣

ማስተዋልም የሌላቸው ናቸው።

29አስተዋዮች ቢሆኑ ኖሮ ይህን በተገነዘቡ፣

መጨረሻቸውም ምን እንደሚሆን ባስተዋሉ ነበር።

30መጠጊያ ዐለታቸው ካልሸጣቸው፣

እግዚአብሔር (ያህዌ) ካልተዋቸው በቀር፣

አንድ ሰው እንዴት ሺሑን ያሳድዳል?

ሁለቱስ እንዴት ዐሥር ሺሑን እንዲሸሹ ያደርጋሉ?

31የእነርሱ መጠጊያ ዐለት እንደ እኛ መጠጊያ

ዐለት አይደለምና፤ ጠላቶቻችንም እንኳ ይህን አይክዱም።

32ወይናቸው ከሰዶም ወይን፣

ከገሞራም ዕርሻ ይመጣል፤

የወይናቸው ፍሬ በመርዝ፣

ዘለላቸውም በምሬት የተሞላ ነው።

33ወይናቸው የእባብ መርዝ፣

የመራዥ እባብም መርዝ ነው።

34“ይህ በእኔ ዘንድ ተጠብቆ ያለ፣

በመዝገቤስ የታተመ አይደለምን?

35በቀል የእኔ ነው፤ እኔ ብድራትን እመልሳለሁ፤

ጊዜው ሲደርስ እግራቸው ይሰናከላል፤

የመጥፊያቸው ቀን ቀርቧል፤

የሚመጣባቸውም ፍርድ ፈጥኖባቸዋል።”

36ኀይላቸው መድከሙን፣

ባሪያም ሆነ ነጻ ሰው አለመቅረቱን በሚያይበት ጊዜ፣

እግዚአብሔር (ያህዌ) ለሕዝቡ ይፈርዳል፤

ለአገልጋዮቹም ይራራል።

37እንዲህም ይላል፤ “መጠጊያ ዐለት የሆኗቸው፣

እነዚያ አማልክታቸው የት አሉ?

38የመሥዋዕታቸውን ሥብ የበሉ፣

የመጠጥ ቍርባናቸውንም የወይን ጠጅ የጠጡ አማልክት ወዴት ናቸው?

እስቲ ይነሡና ይርዷችሁ!

እስቲ መጠለያ ይስጧችሁ!

39“እኔ ራሴ እርሱ እንደ ሆንሁ እዩ፤

ከእኔም በቀር ሌላ አምላክ የለም፤

እገድላለሁ፤ አድናለሁም፤

አቈስላለሁ፤ እፈውሳለሁም፤

ከእጄም የሚያስጥል ማንም የለም።

40እጄን ወደ ሰማይ አነሣለሁ፤

ለዘላለምም ሕያው እንደ ሆንሁ እናገራለሁ፤

41የሚያብረቀርቅ ሰይፌን ስዬ፣

እጄ ለፍርድ ስትይዘው፣

ባላጋራዎቼን እበቀላቸዋለሁ፤

የሚጠሉኝንም እንደ ሥራቸው እከፍላቸዋለሁ።

42ሰይፌ ሥጋ በሚበላበት ጊዜ፣

ፍላጾቼ በደም እንዲሰክሩ አደርጋለሁ፤

ደሙ የታረዱትና የምርኮኞች፣

የጠላት አለቆችም ራስ ደም ነው።”

43አሕዛብ ሆይ፤ ከሕዝቡ ጋር ደስ ይበላችሁ32፥43 ወይም፣ ሕዝቦች ሆይ፤ ደስ ይበላችሁ።32፥43 የማሶሬቱ ቅጅ፣ የሙት ባሕር ጥቅልል እንዲሁም የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም፣ ሕዝቦች ሆይ፤ መላእክት ሁሉ ለእርሱ ይስገዱ ይላሉ።

እርሱ የአገልጋዮቹን ደም ይመልሳል፤

ጠላቶቹንም ይበቀላል።

ምድሪቱንና ሕዝቡን ይቤዣቸዋልና።

44ሙሴም ከነዌ ልጅ ከኢያሱ ጋር መጥቶ የዚህን መዝሙር ቃሎች በሕዝቡ ጆሮ ተናገረ። 45ሙሴም እነዚህን ቃሎች ሁሉ ለመላው እስራኤል ተናግሮ ከጨረሰ በኋላ፣ 46እንዲህ አላቸው፤ የዚህን ሕግ ቃሎች ሁሉ በጥንቃቄ ይጠብቁ ዘንድ ልጆቻችሁን እንድታዝዟቸው፣ እኔ ዛሬ በግልጥ የምነግራችሁን ቃሎች ሁሉ በልባችሁ አኑሩ። 47ቃሎቹ ለእናንተ ሕይወታችሁ እንጂ እንዲሁ ባዶ ቃሎች አይደሉም፤ በእነርሱ ዮርዳኖስን ተሻግራችሁ፣ በምትወርሷትም ምድር ረዥም ዘመን ትኖራላችሁ።

ሙሴ በናባው ተራራ ላይ መሞቱ

48በዚያችም ዕለት እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤ 49“ከኢያሪኮ ማዶ ባለው የሞዓብ ምድር፣ ከዓባሪም ተራሮች አንዱ ወደ ሆነው ወደ ናባው ተራራ ወጥተህ ለእስራኤላውያን ርስት አድርጌ የምሰጣትን የከነዓንን ምድር አሻግረህ ተመልከት። 50ወንድምህ አሮን በሖር ተራራ ላይ እንደ ሞተና ወደ ወገኖቹ እንደ ተሰበሰበ ሁሉ፣ አንተም በወጣህበት በዚያ ተራራ ላይ ሙት፤ ወደ ወገኖችህም ተሰብሰብ። 51ይህ የሚሆንበት ምክንያት ሁለታችሁም በጺን ምድረ በዳ፣ በቃዴስ በመሪባ ውሃ አጠገብ በእኔ ላይ መታመናችሁን በእስራኤላውያን ፊት ስላጐደላችሁና ቅድስናዬንም በእስራኤላውያን መካከል ስላላከበራችሁ ነው። 52ስለዚህ ምድሪቱን ከሩቅ ሆነህ ታያታለህ እንጂ፣ ለእስራኤል ሕዝብ ወደምሰጣት ምድር አትገባም።”

Korean Living Bible

신명기 32:1-52

1“하늘이여, 땅이여,

내 말을 들어라!

2내 교훈은 비처럼 내리고

이슬처럼 맺히며

연한 풀밭 위에 내리는 보슬비요

채소에 내리는 단비라네.

3내가 여호와의 이름을 선포하리니

너희는 우리 하나님의

위대하심을 찬양하라!

4그는 반석이시요

그의 일은 완전하며

그가 하는 모든 일이 공정하니

그는 진실하고 정직한 분이시다.

5“이스라엘이 부패하여 악을 행하니

이제 하나님의 자녀가 아니요,

고집스럽고 비뚤어진 민족이구나.

6어리석고 미련한 백성들아,

이것이 여호와께

보답하는 길이냐?

그는 너희 아버지요

창조주가 아니시냐?

그가 너희를

강한 민족으로 세우셨다.

7“지난날을 회상해 보아라!

과거의 모든 역사를

생각해 보아라!

너희 32:7 원문에는 ‘아비’부모들과

나이 많은 어른들에게

물어 보아라!

그들이 너희에게

설명해 줄 것이다.

8하나님이 모든 민족들에게

땅을 나누어 주실 때,

모든 인종을 구분하실 때에,

각 민족들의 경계를 정하셨다.

9여호와께서

이스라엘을 택하셨으니

야곱의 후손이

그의 백성이 되었네.

10“여호와께서 사막 같은 땅에서,

짐승이 울부짖는 광야에서,

그들을 자기 눈동자처럼

보호하고 지켜 주셨으니

11독수리가 그 보금자리를 흔들어

새끼가 떨어지면

날개를 펴서

새끼를 받아 올리듯 하셨네.

12여호와께서 자기 백성을

혼자 인도하셨고

그들을 도와준 다른 신이 없었다.

13“여호와께서 기름진 고원을

그들에게 주셔서

그들이

밭의 농산물을 먹게 하시고

바위에서 꿀을 빨게 하시며

단단한 바위에서

기름을 얻게 하셨다.

14그가 우유와 고기를 주시고

살진 양과 염소와

좋은 밀을 먹게 하시며

맛있는 포도주를 마시게 하셨네.

1532:15 히 ‘여수룬’이스라엘이 살찌고

비대하며 윤택해지자

자기를 창조하신

하나님을 저버리고,

자기들의 반석 되신

구원자를 멸시하였다.

16그들이 이방 신을 섬기므로

여호와께서 질투하시고,

그들이 악을 행하므로

여호와께서 분노하셨다.

17그들이 하나님이 아닌

마귀에게 제사하였으니

그들이 알지 못한 신,

최근에 나타난 신,

그들의 조상들이

두려워하지 않은 신이었다.

18그들은 자기들을 낳은

반석 되신 하나님을 잊어버렸다.

19“여호와께서 이것을 보시고

그들을 미워하셨으니

그의 자녀들이

그를 노하게 하셨음이라.

20여호와께서 이런 말씀을 하셨다.

‘내가 그들을 외면하고

그들의 종말을 지켜 볼 것이니

그들은 악하고

신실하지 못한 백성임이라.

21그들이 신이 아닌 것으로

나를 질투하게 하고,

무가치한 우상으로

나를 분노하게 하였으니

32:21 또는 ‘나도 백성이 되지 아니한 자로’나도 내 백성이 아닌 사람들에게

애정을 주어

그들을 질투하게 하고

어리석은 민족으로

그들을 분노하게 하리라.

22내 분노가 불같이 일어나

32:22 또는 ‘음부’땅 속 깊은 곳까지 태우며

땅에 있는 모든 것을 삼키고

산들의 터를 소멸하리라.

23내가 그들에게

끝없는 재앙을 내리고

그들에게 내 화살을

마구 쏠 것이다.

24내가 그들에게 심한 기근과

무서운 전염병을 보내고

사나운 들짐승과 독사로

그들을 해하리라.

25밖에서는 칼날에 죽고

집 안에서는

겁에 질려 쓰러질 것이니

젊은 남녀와 젖먹이와

백발 노인이 다 멸망하리라.

26내가 그들을 완전히 없애 버려

아무도 그들을

기억하지 못하게 하려고 하였으나

27그들의 원수들이 오해하여

나 여호와가 이렇게 한 것이 아니라

자기들이 내 백성을 멸망시켰다고

자랑하며 우쭐댈까 두렵구나.’

28“이스라엘은

어리석고 지혜가 없는 민족이다.

29그들이 지혜가 있어서

패망할 것을 알고

자기들의 종말이

어떻게 될 것인지 알았더라면!

30그들의 반석 되시는 하나님이

그들을 버리지 않고

여호와께서 그들을

내주지 않는다면

어떻게 한 사람의 적이

천 명을 추격하고

두 사람의 적이

만 명을 도망치게 할 수 있겠는가?

31원수들의 신이

우리 하나님과 같지 않으니

그들도 이 사실을 인정하는구나.

32그들은 소돔과 고모라 사람들처럼

부패하여

32:32 또는 ‘그들의 포도는’그 행위가 쓰고 독한 열매를 맺는

포도나무 같으며,

33독사의 독으로 만든 독주와 같다.

34“ ‘이것이 내 창고에 쌓여

밀봉되어 있지 않은가?

35원수 갚는 것은 나의 일이다.

내가 갚아 주겠다.

환난 날이 가깝고

멸망의 때가 속히 오리라.’

36“여호와께서 자기 백성을

심판하실 것이며

자기 종들이 무력해지고

종이나 자유인이나

남은 자가 없을 때

그들을 불쌍히 여기실 것이다.

37“여호와께서

이런 말씀을 하시리라.

‘그들의 신들이 어디 있으며,

그들이 피난처로 생각하던

반석이 어디 있느냐?

38그들이 제사지낸 기름을 먹고

포도주를 마시던 신들아,

너희는 지금 어디 있느냐?

일어나서 그들을 도와라.

39나만 하나님인 것을

알지 못하느냐?

나 외에는 참된 신이 없다.

내가 죽이기도 하고 살리기도 하며

상하게도 하고 고치기도 하는데

내가 하는 일을

누가 막을 수 있겠는가?

40내가 하늘을 향해 손을 들고

분명히 말하지만

41내가 심판의 칼을 갈아

내 원수들과

나를 미워하는 자에게 복수하리라.

42내 화살이

그들의 피로 물들 것이며

내 칼이 그들을 죽일 것이니

피를 흘릴 자는

피살자와 포로들과 적장들이다.’

43“만민들아,

여호와의 백성과 함께 기뻐하라.

여호와께서

자기 종들의 원수들을 죽이시고

그들에게 보복하여

32:43 또는 ‘자기땅과백성을위하여속죄하시리로다’자기 땅과 백성을

깨끗하게 하시리라.”

44-45모세는 눈의 아들 여호수아와 함께 이 모든 노래를 낭송한 다음에

46백성들에게 이렇게 말하였다. “여러분은 오늘 내가 전한 이 모든 말씀을 마음에 잘 간직하고 여러분의 자녀들에게도 가르쳐 지키게 하십시오.

47이것은 헛된 말이 아니라 바로 여러분의 생명입니다. 여러분이 이 말씀을 지켜야 요단강을 건너가 살 그 땅에서 오래오래 살게 될 것입니다.”

모세의 죽음에 대한 예고

48바로 그 날 여호와께서 모세에게 말씀하셨다.

49“너는 여리고 맞은편 모압 땅에 있는 아바림 산맥의 느보산에 올라가서 내가 이스라엘 백성에게 줄 가나안 땅을 바라보아라.

50너의 형 아론이 호르산에서 죽었던 것처럼 너는 그 산에서 죽게 될 것이다.

51이것은 너희가 진 광야에 있는 가데스의 므리바 샘에서 범죄하여 이스라엘 백성에게 나의 거룩함을 나타내지 않았기 때문이다.

52너는 내가 이스라엘 백성에게 줄 그 땅을 멀리서 바라보기만 하고 들어가지는 못할 것이다.”