ዘዳግም 32 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

ዘዳግም 32:1-52

1ሰማያት ሆይ፤ አድምጡ፤ እኔም እናገራለሁ፤

ምድር ሆይ፤ አንቺም የአፌን ቃል ስሚ።

2ትምህርቴ እንደ ዝናብ ትውረድ፤

ቃሌም እንደ ጤዛ ይንጠባጠብ፤

በቡቃያ ሣር ላይ እንደ ካፊያ፣

ለጋ ተክልም ላይ እንደ ከባድ ዝናብ ይውረድ።

3እኔ የእግዚአብሔርን (ያህዌ) ስም ዐውጃለሁ፤

የአምላካችንን (ኤሎሂም) ታላቅነት አወድሱ!

4እርሱ ዐለት፣ ሥራውም ፍጹም ነው፤

መንገዱም ሁሉ ትክክል ነው፤

የማይሳሳት ታማኝ አምላክ፣

ቀጥተኛና ጻድቅ አምላክም እርሱ ነው።

5በእርሱ ላይ ክፋት ፈጽመዋል፤ ከነውራቸው የተነሣ ከእንግዲህ ልጆቹ አይደሉም፤

ወልጋዳና ጠማማ ትውልዶች ናቸው32፥5 ወይም የተጣመሙት እነርሱ እንጂ የእርሱ ልጆች አይደሉም

6አንተ ተላላና ጥበብ የጐደለህ ሕዝብ፣

ለእግዚአብሔር (ለያህዌ) የምትመልስለት በዚህ መንገድ ነውን?

አባትህ ፈጣሪህ32፥6 ወይም ያወጣህ አባትህ።

የሠራህና ያበጀህ እርሱ አይደለምን?

7የጥንቱን ዘመን አስታውስ፤

አባትህን ጠይቅ፤ ይነግርሃልም፤

ሽማግሌዎችህንም ጠይቅ፤ ያስረዱሃል።

8ልዑል ለአሕዛብ ርስታቸውን በሰጠ ጊዜ፣

የሰውንም ዘር በለያየ ጊዜ፣

በእስራኤል ልጆች32፥8 የማሶሬቱ ቅጅ፣ የሙት ባሕር ጥቅልል እንዲሁም የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም፣ የእግዚአብሔር ልጆች ይላሉ። ቍጥር ልክ፣

የአሕዛብን ርስት ድንበር ለየ፤

9የእግዚአብሔር (ያህዌ) ድርሻ የገዛ ሕዝቡ፣

ያዕቆብ የተለየ ርስቱ ነውና።

10እርሱን በምድረ በዳ፣

ባዶና ጭው ባለ በረሓ ውስጥ አገኘው፤

ጋሻ ሆነው፤ ተጠነቀቀለትም፤

እንደ ዐይኑ ብሌን ጠበቀው።

11ንስር ጐጆዋን በትና፣

በጫጩቶቿም ላይ እንደምትረብብ፣

እነርሱን ለመያዝ ክንፎቿን እንደምትዘረጋ፣

በክንፎቿም እንደምትሸከማቸው፣

12እግዚአብሔር (ያህዌ) ብቻ መራው፤

ምንም ባዕድ አምላክ አብሮት አልነበረም።

13በምድር ከፍታ ላይ አወጣው፤

የዕርሻንም ፍሬ መገበው፤

ከዐለት ድንጋይ ማር አበላው፤

ከባልጩትም ድንጋይ ዘይት መገበው።

14የላሙንና የበጉን መንጋ ቅቤና ወተት፣

የሰቡትን በጎችና ፍየሎች፣

የባሳንን ምርጥ አውራ በግ፣

መልካም የሆነውንም ስንዴ፣

ማለፊያውንም የወይን ጠጅ።

15ይሹሩን32፥15 ይሹሩን ማለት ቅን ወይም ትክክለኛ ማለት ሲሆን፣ ይኸውም እስራኤልን የሚያሳይ ነው። ወፈረ፤ ረገጠ፤

ጠገበ፤ ሰውነቱ ደነደነ፤ ለሰለሰ፤

የፈጠረውንም አምላክ (ኤሎሂም) ተወ፤

መጠጊያ ዐለት የሆነውን አዳኙንም ናቀ።

16በባዕዳን አማልክታቸው አስቀኑት፤

በአጸያፊ ጣዖቶቻቸውም አስቈጡት።

17አምላክ ላልሆኑ አጋንንት፦

ላላወቋቸው አማልክት፣

ከጊዜ በኋላ ለተነሡ አማልክት፣

አባቶቻችሁ ላልፈሯቸው አማልክት ሠዉ።

18አባት የሆነህን ዐለት ከዳኸው፤

የወለደህን አምላክ ረሳኸው።

19እግዚአብሔር (ያህዌ) ይህን አይቶ ናቃቸው፤

በወንድና በሴት ልጆቹ ተቈጥቷልና።

20እርሱም፣ “ፊቴን ከእነርሱ እሰውራለሁ፤

መጨረሻቸው ምን እንደሚሆንም አያለሁ” አለ፤

ጠማማ ትውልድ፣

የማይታመኑም ልጆች ናቸውና።

21አምላክ ባልሆነው አስቀኑኝ፤

በከንቱ ጣዖቶቻቸው አስቈጡኝ።

እኔም ሕዝብ ባልሆነው አስቀናቸዋለሁ።

በማያስተውልም ሕዝብ አስቈጣቸዋለሁ።

22በቍጣዬ እሳት ተቀጣጥሏልና፤

እርሱ እስከ ሲኦል ዘልቆ ይነድዳል።

ምድርን እስከ ሰብሏ ይበላል፤

የተራሮችንም መሠረት ያቀጣጥላል።

23“በመዓት ላይ መዓት አመጣባቸዋለሁ።

ፍላጻዬንም በእነርሱ ላይ እጨርሳለሁ።

24የሚያጠፋ ራብ፣ በልቶ የሚጨርስ ቸነፈርና ከባድ

መቅሠፍት እሰድድባቸዋለሁ፤

የአራዊትን ሹል ጥርስ፣ በምድር የሚሳብ የእባብ መርዝም

እሰድድባቸዋለሁ።

25ሰይፍ መንገድ ላይ ያስቀራቸዋል፤

ቤታቸውም ውስጥ ድንጋጤ ይነግሣል፤

ጕልማሳውና ልጃገረዷ፣

ሕፃኑና ሽማግሌው ይጠፋሉ።

26እበትናቸዋለሁ፤ ከሰዎችም መካከል መታሰቢያቸውን

አጠፋለሁ አልሁ፤

27ነገር ግን ጠላቶቻቸው እንዳይታበዩ፣

‘ድል ያደረገችው እጃችን እንጂ፣

እግዚአብሔር (ያህዌ) ይህን ሁሉ አላደረገም’ እንዳይሉ፣

የጠላትን መነሣሣት ሠጋሁ።”

28አእምሮ የጐደላቸው፣

ማስተዋልም የሌላቸው ናቸው።

29አስተዋዮች ቢሆኑ ኖሮ ይህን በተገነዘቡ፣

መጨረሻቸውም ምን እንደሚሆን ባስተዋሉ ነበር።

30መጠጊያ ዐለታቸው ካልሸጣቸው፣

እግዚአብሔር (ያህዌ) ካልተዋቸው በቀር፣

አንድ ሰው እንዴት ሺሑን ያሳድዳል?

ሁለቱስ እንዴት ዐሥር ሺሑን እንዲሸሹ ያደርጋሉ?

31የእነርሱ መጠጊያ ዐለት እንደ እኛ መጠጊያ

ዐለት አይደለምና፤ ጠላቶቻችንም እንኳ ይህን አይክዱም።

32ወይናቸው ከሰዶም ወይን፣

ከገሞራም ዕርሻ ይመጣል፤

የወይናቸው ፍሬ በመርዝ፣

ዘለላቸውም በምሬት የተሞላ ነው።

33ወይናቸው የእባብ መርዝ፣

የመራዥ እባብም መርዝ ነው።

34“ይህ በእኔ ዘንድ ተጠብቆ ያለ፣

በመዝገቤስ የታተመ አይደለምን?

35በቀል የእኔ ነው፤ እኔ ብድራትን እመልሳለሁ፤

ጊዜው ሲደርስ እግራቸው ይሰናከላል፤

የመጥፊያቸው ቀን ቀርቧል፤

የሚመጣባቸውም ፍርድ ፈጥኖባቸዋል።”

36ኀይላቸው መድከሙን፣

ባሪያም ሆነ ነጻ ሰው አለመቅረቱን በሚያይበት ጊዜ፣

እግዚአብሔር (ያህዌ) ለሕዝቡ ይፈርዳል፤

ለአገልጋዮቹም ይራራል።

37እንዲህም ይላል፤ “መጠጊያ ዐለት የሆኗቸው፣

እነዚያ አማልክታቸው የት አሉ?

38የመሥዋዕታቸውን ሥብ የበሉ፣

የመጠጥ ቍርባናቸውንም የወይን ጠጅ የጠጡ አማልክት ወዴት ናቸው?

እስቲ ይነሡና ይርዷችሁ!

እስቲ መጠለያ ይስጧችሁ!

39“እኔ ራሴ እርሱ እንደ ሆንሁ እዩ፤

ከእኔም በቀር ሌላ አምላክ የለም፤

እገድላለሁ፤ አድናለሁም፤

አቈስላለሁ፤ እፈውሳለሁም፤

ከእጄም የሚያስጥል ማንም የለም።

40እጄን ወደ ሰማይ አነሣለሁ፤

ለዘላለምም ሕያው እንደ ሆንሁ እናገራለሁ፤

41የሚያብረቀርቅ ሰይፌን ስዬ፣

እጄ ለፍርድ ስትይዘው፣

ባላጋራዎቼን እበቀላቸዋለሁ፤

የሚጠሉኝንም እንደ ሥራቸው እከፍላቸዋለሁ።

42ሰይፌ ሥጋ በሚበላበት ጊዜ፣

ፍላጾቼ በደም እንዲሰክሩ አደርጋለሁ፤

ደሙ የታረዱትና የምርኮኞች፣

የጠላት አለቆችም ራስ ደም ነው።”

43አሕዛብ ሆይ፤ ከሕዝቡ ጋር ደስ ይበላችሁ32፥43 ወይም፣ ሕዝቦች ሆይ፤ ደስ ይበላችሁ።32፥43 የማሶሬቱ ቅጅ፣ የሙት ባሕር ጥቅልል እንዲሁም የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም፣ ሕዝቦች ሆይ፤ መላእክት ሁሉ ለእርሱ ይስገዱ ይላሉ።

እርሱ የአገልጋዮቹን ደም ይመልሳል፤

ጠላቶቹንም ይበቀላል።

ምድሪቱንና ሕዝቡን ይቤዣቸዋልና።

44ሙሴም ከነዌ ልጅ ከኢያሱ ጋር መጥቶ የዚህን መዝሙር ቃሎች በሕዝቡ ጆሮ ተናገረ። 45ሙሴም እነዚህን ቃሎች ሁሉ ለመላው እስራኤል ተናግሮ ከጨረሰ በኋላ፣ 46እንዲህ አላቸው፤ የዚህን ሕግ ቃሎች ሁሉ በጥንቃቄ ይጠብቁ ዘንድ ልጆቻችሁን እንድታዝዟቸው፣ እኔ ዛሬ በግልጥ የምነግራችሁን ቃሎች ሁሉ በልባችሁ አኑሩ። 47ቃሎቹ ለእናንተ ሕይወታችሁ እንጂ እንዲሁ ባዶ ቃሎች አይደሉም፤ በእነርሱ ዮርዳኖስን ተሻግራችሁ፣ በምትወርሷትም ምድር ረዥም ዘመን ትኖራላችሁ።

ሙሴ በናባው ተራራ ላይ መሞቱ

48በዚያችም ዕለት እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤ 49“ከኢያሪኮ ማዶ ባለው የሞዓብ ምድር፣ ከዓባሪም ተራሮች አንዱ ወደ ሆነው ወደ ናባው ተራራ ወጥተህ ለእስራኤላውያን ርስት አድርጌ የምሰጣትን የከነዓንን ምድር አሻግረህ ተመልከት። 50ወንድምህ አሮን በሖር ተራራ ላይ እንደ ሞተና ወደ ወገኖቹ እንደ ተሰበሰበ ሁሉ፣ አንተም በወጣህበት በዚያ ተራራ ላይ ሙት፤ ወደ ወገኖችህም ተሰብሰብ። 51ይህ የሚሆንበት ምክንያት ሁለታችሁም በጺን ምድረ በዳ፣ በቃዴስ በመሪባ ውሃ አጠገብ በእኔ ላይ መታመናችሁን በእስራኤላውያን ፊት ስላጐደላችሁና ቅድስናዬንም በእስራኤላውያን መካከል ስላላከበራችሁ ነው። 52ስለዚህ ምድሪቱን ከሩቅ ሆነህ ታያታለህ እንጂ፣ ለእስራኤል ሕዝብ ወደምሰጣት ምድር አትገባም።”

Japanese Contemporary Bible

申命記 32:1-52

32

モーセの歌

1天よ、地よ、じっと耳をすませ、私のことばに。

2こぬか雨や露のように静かに、

若草をぬらす雨のように心地よく、

山腹を駆ける夕立のように激しく、

私のことばは下る。

3さあ、主の偉大さを告げよう。

主は、この上なくすばらしい方。

4岩のように堅く、なさることはみな完全で正しく、

何事にも公平で忠実な方。

主はいつも潔白な方。

5しかし、イスラエルは堕落し、罪に汚れてしまった。

強情で曲がったことばかりする。

もはや神の民ではない。

6これが主への恩返しか。

愚かな民よ。

神は父親ではなかったか。

あなたの造り主ではなかったか。

あなたを強く育て上げた方ではなかったか。

7昔を思い出せ。

父や老人に聞けば、すべてがはっきりするだろう。

8世界を造られた時、

神は天使を遣わし、国々を監督させた。

9だが、イスラエルは特別だ。

神ご自身のものだからだ。

10獣の遠ぼえの聞こえる寂しい荒野を行く時、

神はまるで自分の目のようにイスラエルを守られた。

11わしが翼を広げ、ひなを乗せて飛ぶように、

神はその国民を、翼に乗せて運ばれる。

12主だけがイスラエルを指導し、

国民が外国の神々を知らずにいた時、

13丘は豊かな実りを約束し、

ゆるやかに起伏する畑は肥えていた。

岩からはちみつが、石地からオリーブ油が採れた。

14ほかにも、乳と肉、バシャンの極上の雄羊と雄やぎ、

最良の小麦、あわ立つぶどう酒と、

何でも欲しいだけあった。

15イスラエルはじきに満腹し、丸々と太った。

ぜいたくに慣れて高慢になり、

自分を造った神を捨て、

救いの岩を軽んじた。

16イスラエルは外国の神々のあとを追い、

神の激しい怒りを燃えさせた。

17あろうことか、外国の神々、

それまで拝んだこともない神々に

いけにえをささげた。

18生みの親である岩をけとばし、

いのちを与えてくれた神を忘れるとは。

19神は憎しみに燃えた。

自分の息子、娘たちに侮辱されたのだ。

20ついに神は言われた。

「強情で不信仰な者ども、

もうわたしは知らない。

どんなことになるか見ているがいい。

21恨みを買ってでも、まやかし物の偶像を拝みたいのか。

ならば報いを与えよう。

あなたを捨て、

無知な異教の諸国民に救いを与えるから、

さんざん恨みごとを言うがいい。

22わたしの怒りの炎は燃え上がり、

地とその産物を焼き尽くし、

山々をなめ尽くす。

23息つくまもなく災いを下し、

次々と矢を放ち、射倒そう。

24飢えと熱病と不治の病で痛めつけてもかまわない。

滅ぼしてしまおう。

野獣が彼らを八つ裂きにし、

毒蛇は獲物を求めて地をはい回る。

25外には敵の剣、内には恐れ。

老人も若者も、乳飲み子さえも逃れられない。

26あげくは、遠い国へ散り散りに追いやる。

そこに彼らがいたことさえ忘れさせるために。

27だが、それでは敵の思うつぼだ。

『われわれがイスラエルを滅ぼした。

主なんかじゃない』と大言壮語させることになる。」

28イスラエルは愚かな国、知恵のない、わからず屋。

29ああ、少しでも知恵があり、ものわかりがよかったら、

自分の末路を見きわめることもできたろうに。

30彼らの岩である主が見捨てず、

滅ぼそうとされなかったら、

一人の敵が千人を追い散らし、

二人が万人を敗走させることもなかったろうに。

31この岩にまさる岩はどこにもない。

敵も、神々への祈りがむなしいことを知っている。

32彼らの行いは、ソドム、ゴモラの人たちと同じで、

苦々しい毒がある。

33彼らの飲むぶどう酒はまむしの毒液だ。

34「だがイスラエルは、わたしの取っておきの国民、

倉に納めた宝だ。

35復讐はわたしの務め、

イスラエルの敵には罰を下す。

判決はすでに下った。」

36神はイスラエルをさばき、

彼らの失敗を優しくかばわれる。

奴隷も自由人も力が衰えていくのを見て、

37こう言われる。

「ほかの神々はどこへ行った。

頼みの岩はどうしたのだ。

38あぶら身やぶどう酒をささげた神々はどうなったのか。

さあ、神々を奮い立たせて助けてもらうがいい。

39どうだ、よくわかったか。

ほんとうの神はわたしだけなのだ。

殺すも生かすも、

傷つけるのも癒やすのも、思いのまま。

わたしの手から救い出せる者はいない。

40-41手を天に差し伸べ、わたしの存在をかけて誓おう。

きらめく剣をとぎすまし、敵に刑罰を下す。

42矢は血に酔いしれ、剣は肉と血をむさぼる。

刺し殺され、捕らわれた者の肉と血を。

敵の頭は血にまみれる。」

43異教の国民よ、神の国民をたたえよ。

神は彼らのかたきを討ち、

御国と民をきよめられたから。

44-45モーセはヨシュアとともにこの歌を歌い終えると、 46人々に命じました。「今日与えた律法をすべて心に留め、子どもたちに教えなさい。 47この律法は、ただ意味もなくことばを並べてあるのではありません。あなたがたのいのちそのものです。この律法を守れば、ヨルダン川の向こうの、これから占領する地で、長く生きることができる。」

48同じ日、主はモーセに告げて語りました。 49「エリコに向かい合った、モアブのアバリム高地にあるネボ山に登りなさい。頂上から、わたしがイスラエル人に与えるカナンの国を見渡すのだ。 50兄のアロンがホル山で死に、先祖の仲間入りをしたように、あなたもその国を見たら、先祖の仲間入りをしなければならない。 51ツィンの荒野のメリバテ・カデシュの泉でしたことの報いだ。あの時あなたは、わたしの神聖さを人々に示さなかった。 52だから、約束の地を目の前にしながら、入って行くことはできない。」