ዘዳግም 3 – NASV & PCB

New Amharic Standard Version

ዘዳግም 3:1-29

የባሳን ንጉሥ የዐግ መሸነፍ

1ከዚያም፣ ተመልሰን የባሳንን መንገድ ይዘን ወጣን፤ የባሳን ንጉሥ ዐግም ከመላው ሰራዊቱ ጋር ሆኖ በኤድራይ ጦርነት ሊገጥመን ተነሣ። 2እግዚአብሔር (ያህዌ)፣ “እርሱን፣ መላው ሰራዊቱንና ምድሩን በእጅህ አሳልፌ ስለ ሰጠሁህ፣ አትፍራው፤ ሐሴቦንን ይገዛ በነበረው በአሞራውያን ንጉሥ በሴዎን ላይ ያደረግህበትን በእርሱም ላይ አድርግበት” አለኝ።

3ስለዚህ አምላካችን እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) የባሳንን ንጉሥ ዐግንና ሰራዊቱን ሁሉ እንደዚሁ በእጃችን ላይ ጣላቸው፤ እኛም አንድ እንኳ በሕይወት ሳናስቀር አጠፋናቸው። 4በዚያን ጊዜ ከተሞቹን ሁሉ ያዝን፤ የዐግ ግዛት ከሆነው፣ በባሳን ከሚገኘው ከጠቅላላው የአርጎብ ክልል ስድሳ ከተሞች ውስጥ፣ እኛ ያልያዝነው አንድም ከተማ አልነበረም። 5እነዚህ ከተሞች ሁሉ ከፍ ባሉ ቅጥሮች፣ በመዝጊያዎችና በመወርወሪያዎች የተመሸጉ ነበሩ፤ እንዲሁም ቅጥር የሌላቸው አያሌ መንደሮች ነበሩ። 6በእያንዳንዱ ከተማ ያሉትን ወንዶቹን፣ ሴቶቹንና ልጆቻቸውን ጭምር በማጥፋት፣ በሐሴቦን ንጉሥ በሴዎን ላይ እንዳደረግነው ሁሉ፣ እነዚህንም ፈጽመን ደመሰስናቸው3፥6 የ2፥34 አማራጭ ትርጕም ይመ።7ከብቱን በሙሉና ከየከተሞቻቸው የማረክነውን ሁሉ ግን ለራሳችን አደረግን።

8ስለዚህ በዚያን ጊዜ ከዮርዳኖስ በስተ ምሥራቅ የሚገኘውን፣ ከአርኖን ሸለቆ እስከ አርሞንዔም ተራራ ያለውን ግዛት፣ ከእነዚህ ከሁለቱ የአሞራውያን ነገሥታት ላይ ወሰድንባቸው። 9አርሞንዔምን፣ ሲዶናውያን ሢርዮን ብለው ሲጠሩት፣ አሞራውያን ግን ሳኔር ይሉታል። 10በከፍታው ቦታ ላይ የሚገኙትን ከተሞች በሙሉ፣ ገለዓድን እንዳለ፣ እስከ ሰልካና እስከ ኤድራይ ያለውን ባሳንን ሁሉ እንዲሁም በባሳን ውስጥ የሚገኙትን የዐግ ግዛት ከተሞች በእጃችን አደረግን። 11ከራፋይማውያን ወገን የተረፈ የባሳን ንጉሥ ዐግ ብቻ ነበር። ዐልጋው3፥11 ወይም፣ ድንጋይ ተጠርቦ የተዘጋይ የሬሳ ሣጥን ከብረት የተሠራ ቁመቱም ዘጠኝ ክንድ፣ ስፋቱ ደግሞ አራት ክንድ3፥11 ቁመቱ 4 ሜትር ስፋቱ 1.8 ሜትር ያህል ነው። ነበር። ይህም እስካሁን በአሞናውያን ከተማ በረባት ይገኛል።

እስራኤላውያን ምድሪቱን መከፋፈላቸው

12በዚያን ጊዜ ከያዝነው ምድር ላይ በአርኖን ሸለቆ አጠገብ ካለችው ከአሮዔር አንሥቶ በስተ ሰሜን ያለውን ግዛት፣ በተጨማሪም ኰረብታማውን የገለዓድ አገር እኩሌታ ከነከተሞቹ ለሮቤላውያንና ለጋዳውያን ሰጠኋቸው። 13ቀሪውን የገለዓድ ምድርና የዐግ ግዛት የሆነውን ባሳንን በሙሉ ለምናሴ ነገድ እኩሌታ ሰጠሁ። በባሳን የሚገኘው መላው የአርጎብ ክልል የራፋይማውያን ምድር በመባል ይታወቅ ነበር። 14ከምናሴ ነገድ የሆነው ኢያዕር፣ እስከ ጌሹራውያንና እስከ ማዕካታውያን ወሰን ድረስ የሚገኘውን መላውን የአርጎብ ምድር ወሰደ፤ ምድሪቱም በስሙ ተጠራች3፥14 ወይም፣ የኢያዕር መኖሪያ ተብላ ተጠራች፤ ከዚሁ የተነሣ ባሳን እስከ ዛሬ ድረስ ሓቦት ኢያዕር ትባላለች። 15ገለዓድንም ለማኪር ሰጠሁት። 16ነገር ግን የሸለቆውን እኩሌታ ወሰን በማድረግ ከገለዓድ አንሥቶ እስከ አርኖን ሸለቆ፣ ከዚያም የአሞናውያን ድንበር እስከ ሆነው እስከ ያቦቅ ወንዝ ያለውን ግዛት ለሮቤላውያንና ለጋዳውያን ሰጠኋቸው። 17የምዕራቡ ወሰን፣ በዓረባ የሚገኘው ዮርዳኖስ ሲሆን፣ ይኸውም ከፈስጋ ተረተሮች በታች፣ ከኪኔሬት አንሥቶ የጨው ባሕር3፥17 ይኸውም የሙት ባሕር ነው። እስከሚባለው እስከ ዓረባ ባሕር ድረስ ነው።

18በዚያን ጊዜ እኔ እንዲህ ብዬ አዘዝኋችሁ፤ “አምላካችሁ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ይህችን ምድር ርስት አድርጎ ለእናንተ ሰጥቷችኋል፤ ይሁን እንጂ የአካል ብቃት ያላቸው ሰዎቻችሁ ሁሉ ለጦርነት ዝግጁ ሆነው ከወንድሞቻችሁ ከእስራኤላውያን ፊት በመቅደም መሻገር አለባቸው። 19ሆኖም ሚስቶቻችሁና ልጆቻችሁ፣ (ብዙ ከብቶች እንዳሏችሁም ስለማውቅ) ከብቶቻችሁም በሰጠኋችሁ ከተሞች ውስጥ ይቈዩ፤ 20ይኸውም፣ እግዚአብሔር (ያህዌ) ለእናንተ እንዳደረገው ሁሉ ወንድሞቻችሁን እስኪያሳርፋቸውና አምላካችሁ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ከዮርዳኖስ ማዶ የሚሰጣቸውን ምድር እነርሱም እንደዚሁ እስኪወርሱ ድረስ ነው፤ ከዚያ በኋላ እያንዳንዳችሁ ወደ ሰጠኋችሁ ርስት ትመለሳላችሁ።”

ሙሴ ዮርዳኖስን እንዳይሻገር መከልከሉ

21በዚያን ጊዜ ኢያሱን እንዲህ ስል አዘዝሁት፤ “አምላካችሁ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) በእነዚህ በሁለቱ ነገሥታት ላይ ያደረገውን ሁሉ በገዛ ዐይንህ አይተሃል፤ አሁንም ዐልፈህ በምትሄድባቸው መንግሥታት ላይ ሁሉ እግዚአብሔር ይህንኑ ይደግመዋል። 22አምላካችሁ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ራሱ ይዋጋላችኋልና አትፍሯቸው።”

23በዚያን ጊዜ እግዚአብሔርን (ያህዌ) እንዲህ ብዬ ለመንሁት፤ 24“ጌታ እግዚአብሔር (አዶናይ ያህዌ) ሆይ፤ ታላቅነትህንና ብርቱ ክንድህን ለእኔ ለባሪያህ እነሆ ማሳየት ጀምረሃል፤ ለመሆኑ በሰማይም ሆነ በምድር፣ አንተ የምታደርጋቸውን ሥራዎችና ታላላቅ ድርጊቶች መፈጸም የሚችል አምላክ ማነው? 25አሁንም ከዮርዳኖስ ማዶ ያለችውን ያችን መልካሚቱን ምድር፣ ውብ የሆነችውን ኰረብታማ አገርና ሊባኖስን እንዳይ ፍቀድልኝ።”

26እግዚአብሔር (ያህዌ) ግን በእናንተ ሰበብ ተቈጥቶኝ ነበርና አልሰማኝም፤ እግዚአብሔር (ያህዌ) እንዲህ አለኝ፤ “ይበቃል፤ ከእንግዲህ ወዲያ ስለዚህ ነገር አታንሣብኝ። 27ወደ ፈስጋ ተራራ ጫፍ ውጣ፤ ወደ ምዕራብና ወደ ሰሜን፣ ወደ ደቡብና ወደ ምሥራቅም ተመልከት። አንተ ዮርዳኖስን ስለማትሻገር፣ ምድሪቱን በዐይንህ ብቻ እያት። 28ነገር ግን ሕዝቡን መርቶ በማሻገር የምታያትን ምድር እንዲወርሱ የሚያደርጋቸው ስለሆነ፣ ኢያሱን ላከው፤ አደፋፍረው፤ አበረታታውም።” 29ስለዚህ እኛ በቤተ ፌጎር አጠገብ ባለው ሸለቆ ውስጥ ቈየን።

Persian Contemporary Bible

تثنيه 3:1‏-29

شكست عوج پادشاه

(اعداد 21‏:31‏-35)

1‏-2سپس به جانب سرزمين باشان روی آورديم. عوج، پادشاه باشان لشكر خود را بسيج نموده، در اَدَرعی به ما حمله كرد. ولی خداوند به من فرمود كه از او نترسم. خداوند به من گفت: «تمام سرزمين عوج و مردمش در اختيار شما هستند. با ايشان همان كنيد كه با سيحون، پادشاه اموری‌ها در حشبون كرديد.» 3بنابراين خداوند، خدای ما عوج پادشاه و همهٔ مردمش را به ما تسليم نمود و ما همهٔ آنها را كشتيم. 4تمامی شصت شهرش يعنی سراسر ناحيهٔ ارجوب باشان را به تصرف خود درآورديم. 5اين شهرها با ديوارهای بلند و دروازه‌های پشتبنددار محافظت می‌شد. علاوه بر اين شهرها، تعداد زيادی آبادی بی‌حصار نيز بودند كه به تصرف ما درآمدند. 6ما سرزمين باشان را مثل قلمرو سيحون پادشاه واقع در حشبون، كاملاً نابود كرديم و تمام اهالی آن را چه مرد، چه زن و چه كودک، از بين برديم؛ 7ولی گله‌ها و غنايم جنگی را برای خود نگه‌داشتيم.

8پس ما بر تمام سرزمين دو پادشاه اموری واقع در شرق رود اردن، يعنی بر كليه اراضی از دره ارنون تا كوه حرمون، مسلط شديم. 9(صيدونی‌ها كوه حرمون را سريون و اموری‌ها آن را سنير می‌خوانند.) 10ما كليهٔ شهرهای واقع در آن جلگه و تمامی سرزمين جلعاد و باشان را تا شهرهای سلخه و ادرعی تصرف كرديم.

11ناگفته نماند كه عوج، پادشاه باشان آخرين بازماندهٔ رفائی‌های غول‌پيكر بود. تختخواب آهنی او كه در شهر رَبَت، يكی از شهرهای عمونی‌ها نگهداری می‌شود حدود چهار متر طول و دو متر عرض دارد.

قبيله‌های شرق رود اردن

(اعداد 32‏:1‏-42)

12در آن موقع، من سرزمين تسخير شده را به قبيله‌های رئوبين، جاد و نصف قبيلهٔ مَنَسی دادم. به قبيله‌های رئوبين و جاد ناحيهٔ شمال عروعير را كه در كنار رود ارنون است به اضافهٔ نصف كوهستان جلعاد را با شهرهايش دادم، 13و به نصف قبيلهٔ منسی باقيماندهٔ سرزمين جلعاد و تمام سرزمين باشان را كه قلمرو قبلی عوج پادشاه بود واگذار كردم. (منطقهٔ ارجوب در باشان را سرزمين رفائی‌ها نيز می‌نامند.) 14طايفهٔ يائير از قبيلهٔ منسی تمامی منطقهٔ ارجوب (باشان) را تا مرزهای جشوری‌ها و معكی‌ها گرفتند و آن سرزمين را به اسم خودشان نامگذاری كرده، آنجا را همچنانكه امروز هم مشهور است حَووُت يائير (يعنی «دهستانهای يائير») ناميدند. 15بعد جلعاد را به طايفهٔ ماخير دادم. 16قبيله‌های رئوبين و جاد منطقه‌ای را كه از رود يبوق در جلعاد (كه سرحد عمونی‌ها بود) شروع می‌شد و تا وسط جلگهٔ رود ارنون امتداد می‌يافت، گرفتند. 17مرز غربی ايشان رود اردن بود كه از درياچهٔ جليل تا دريای مرده و كوه پيسگاه ادامه می‌يافت.

18آنگاه من به قبيله‌های رئوبين و جاد و نصف قبيلهٔ منسی يادآوری كردم كه اگرچه خداوند آن سرزمين را به ايشان داده است با اين حال حق سكونت در آنجا را نخواهند داشت تا زمانی كه مردان مسلحشان در پيشاپيش بقيه قبيله‌ها، آنها را به آن سوس رود اردن يعنی به سرزمينی كه خدا به ايشان وعده داده، برسانند.

19به ايشان گفتم: «ولی زنان و فرزندانتان می‌توانند اينجا در اين شهرهايی كه خداوند به شما داده است سكونت كرده، از گله‌هايتان (كه می‌دانم تعدادشان زياد است) مواظبت كنند. 20شما به برادران خود كمک كنيد تا خداوند به آنها نيز پيروزی بدهد. وقتی آنها سرزمينی را كه خداوند، خدايتان در آن طرف رود اردن به ايشان داده است تصرف كردند، آنگاه شما می‌توانيد به سرزمين خود بازگرديد.»

21بعد به يوشع گفتم: «تو با چشمانت ديدی كه خداوند، خدايت با آن دو پادشاه چگونه عمل نمود. او با تمامی ممالک آن طرف رود اردن نيز همين كار را خواهد كرد. 22از مردم آنجا نترسيد، چون خداوند، خدايتان برای شما خواهد جنگيد.»

خدا به موسی اجازهٔ ورود به سرزمين موعود را نمی‌دهد

23‏-25آنگاه از خداوند چنين درخواست نمودم: «ای خداوند، التماس می‌كنم اجازه فرمايی از اين رود گذشته، وارد سرزمين موعود بشوم، به سرزمين حاصلخيز آن طرف رود اردن با رشته کوههای آن و به سرزمين لبنان. آرزومندم نتيجه بزرگی و قدرتی را كه به ما نشان داده‌ای ببينم. كدام خدايی در تمام آسمان و زمين قادر است آنچه را كه تو برای ما كرده‌ای بكند؟»

26ولی خداوند به سبب گناهان شما بر من غضبناک بود و به من اجازهٔ عبور نداد. او فرمود: «ديگر از اين موضوع سخنی بر زبان نياور. 27به بالای كوه پيسگاه برو. از آنجا می‌توانی به هر سو نظر اندازی و سرزمين موعود را از دور ببينی؛ ولی از رود اردن عبور نخواهی كرد. 28يوشع را به جانشينی خود بگمار و او را تقويت و تشويق كن، زيرا او قوم را برای فتح سرزمينی كه تو از قلهٔ كوه خواهی ديد، به آن طرف رودخانه هدايت خواهد كرد.»

29بنابراين ما در درهٔ نزديک بيت‌فغور مانديم.