ዘዳግም 29 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ዘዳግም 29:1-29

የቃል ኪዳኑ መታደስ

1እግዚአብሔር (ያህዌ) በኮሬብ ከገባው ቃል ኪዳን በተጨማሪ በሞዓብ ምድር ከእስራኤላውያን ጋር እንዲያደርግ ሙሴን ያዘዘው የኪዳኑ ቃሎች እነዚህ ናቸው።

2ሙሴ እስራኤላውያንን ሁሉ ጠርቶ እንዲህ አላቸው፦ እግዚአብሔር (ያህዌ) በግብፅ፣ በፈርዖን፣ በሹማምቱ ሁሉና በመላ አገሩ ላይ ያደረገውን ሁሉ ዐይኖቻችሁ አይተዋል። 3እነዚያን ከባድ ፈተናዎች፣ ታምራዊ ምልክቶችና ታላላቅ ድንቆች በገዛ ዐይኖቻችሁ አይታችኋል። 4ነገር ግን እስከ ዛሬ ድረስ እግዚአብሔር (ያህዌ) የሚያስተውል አእምሮ ወይም የሚያይ ዐይን ወይም የሚሰማ ጆሮ አልሰጣችሁም። 5በምድረ በዳ በመራኋችሁ በእነዚያ አርባ ዓመታት ውስጥ ልብሳችሁ አላረጀም፤ የእግራችሁም ጫማ አላለቀም። 6ቂጣ አልበላችሁም፤ የወይን ጠጅ ወይም ሌላ የሚያሰክር መጠጥ አልጠጣችሁም፤ ይህን ያደረግሁት እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ (ያህዌ ኤሎሂም) እንደ ሆንሁ ታውቁ ዘንድ ነው።

7ወደዚህ ስፍራ በደረሳችሁ ጊዜ፣ የሐሴቦን ንጉሥ ሴዎንና የባሳን ንጉሥ ዐግ ሊወጉን መጡ፤ ሆኖም ድል አደረግናቸው። 8ምድራቸውንም ወስደን ለሮቤላውያን፣ ለጋዳውያንና ለምናሴ ነገድ እኩሌታ ርስት አድርገን ሰጠን።

9እንግዲህ የምታደርጉት ሁሉ እንዲከናወንላችሁ፣ የዚህን ኪዳን ቃሎች በጥንቃቄ ተከተሉ። 10እናንተ ሁላችሁ መሪዎቻችሁና አለቆቻችሁ፣ ሽማግሌዎቻችሁና ሹሞቻችሁ እንዲሁም ሌሎች የእስራኤል ሰዎች ሁሉ ዛሬ በአምላካችሁ በእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ፊት ቆማችኋል፤ 11ልጆቻችሁና ሚስቶቻችሁ ዕንጨትህን እየፈለጡ፣ ውሃህንም እየቀዱ በሰፈርህ የሚኖሩ መጻተኞችም አብረውህ ቆመዋል። 12እዚህ የቆምኸው እግዚአብሔር (ያህዌ) ዛሬ ከአንተ ጋር ወደሚያደርገውና በመሐላ ወደሚያጸናው ኪዳን ከአምላክህ ከእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ጋር ትገባ ዘንድ፣ 13ለአንተ በሰጠው ተስፋና ለአባቶችህ ለአብርሃም፣ ለይስሐቅና ለያዕቆብ በማለላቸው መሠረት እርሱ አምላክህ (ኤሎሂም) ይሆን ዘንድ፣ አንተም ሕዝቡ መሆንህን በዛሬው ዕለት ለማረጋገጥ ነው። 14እኔም ይህን የመሐላ ኪዳን የማደርገው ከእናንተ ጋር ብቻ አይደለም፤ 15አብራችሁን በአምላካችን በእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ፊት እዚህ ከቆማችሁት ጋር ብቻ ሳይሆን፣ ዛሬ እዚህ ከሌሉትም ጋር ነው።

16በግብፅ ምድር እንዴት እንደ ኖርንና ወደዚህ ስንመጣም በየአገሮቹ ውስጥ እንዴት እንዳለፍን ራሳችሁ ታውቃላችሁ። 17በመካከላቸውም አስጸያፊ ምስሎቻቸውንና የዕንጨትና የድንጋይ፣ የብርና የወርቅ ጣዖቶቻቸውን አይታችኋል። 18የእነዚህን ሕዝቦች አማልክት ለማምለክ ልቡን ከአምላካችን ከእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) የሚመልስ ወንድም ሆነ ሴት ጐሣም ሆነ ነገድ ዛሬ ከመካከላችሁ አለመገኘቱን አረጋግጡ፤ ከመካከልህ እንዲህ ያለውን መራራ መርዝ የሚያወጣ ሥር እንዳይኖር ተጠንቀቁ።

19እንዲህ ያለው ሰው የዚህን መሐላ ቃል በሚሰማበት ጊዜ፣ በልቡ ራሱን በመባረክ፣ “እንደ ልቤ ሐሳብ ብኖርም እንኳ ሰላም አለኝ” ብሎ ያስባል። ይህም በለምለሙም ሆነ በደረቁ መሬት ላይ ጥፋትን ያመጣል29፥19 ወይም፣ ለመርካት ስካርን ይጨምራል20እግዚአብሔር (ያህዌ) ለዚያ ሰው ፈጽሞ ይቅርታ አያደርግለትም፤ ቍጣውና ቅናቱ በእርሱ ላይ ይነድድበታል። በዚህ መጽሐፍ የተጻፈው ርግማን ሁሉ ይወርድበታል፤ እግዚአብሔርም (ያህዌ) ስሙን ከሰማይ በታች ይደመስሰዋል። 21በዚህ የሕግ መጽሐፍ በተጻፈው የኪዳኑ ርግማን መሠረት፣ እግዚአብሔር (ያህዌ) እርሱን ከእስራኤል ነገዶች ሁሉ ለጥፋት ይለየዋል።

22የሚቀጥለው ትውልድ ከእናንተ በኋላ የሚተኩት ልጆቻችሁና ከሩቅ አገር የሚመጡ እንግዶች በምድሪቱ የደረሰውን ታላቅ መቅሠፍትና እግዚአብሔር (ያህዌ) ያመጣባቸውን በሽታዎች ያያሉ። 23ምድሪቱ በሙሉ የተቃጠለ ጨውና ዲን ዐመድ ትሆናለች። አንዳች ነገር አይተከልባትም፤ ምንም ነገር አያቈጠቍጥባትም፤ የሚያድግ ተክል አይገኝባትም። የሚደርስባት ውድመት እግዚአብሔር (ያህዌ) በታላቅ ቍጣ እንደ ገለባበጣቸው እንደ ሰዶምና ገሞራ፣ እንደ አዳማና ሲባዮ ጥፋት ይሆናል። 24አሕዛብም ሁሉ፣ “እግዚአብሔር (ያህዌ) በዚህች ምድር ላይ ይህን ለምን አደረገባት? ይህ አስፈሪና የሚነድድ ቍጣስ ለምን መጣባት?” ብለው ይጠይቃሉ።

25መልሱም፣ “የአባቶቻቸው አምላክ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ከግብፅ ምድር ባወጣቸው ጊዜ፣ ከእነርሱ ጋር የገባውን ኪዳን ሕዝቡ ስለ ተዉ ነው። 26ወጥተውም የማያውቋቸውን፣ እርሱም ያላዘዛቸውን ሌሎችን አማልክት አመለኩ፤ ሰገዱላቸውም። 27ስለዚህ በዚህ መጽሐፍ የተጻፈውን ርግማን ሁሉ እስኪያመጣባት ድረስ፣ የእግዚአብሔር (ያህዌ) ቍጣ በዚህች ምድር ላይ ነደደ። 28በአስፈሪ ቍጣና በታላቅ መዓት እግዚአብሔር (ያህዌ) ከምድራቸው ነቀላቸው፤ አሁን እንደ ሆነውም ወደ ሌላ ምድር ጣላቸው” የሚል ይሆናል።

29ምስጢር የሆነው ለአምላካችን ለእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ነው፤ የተገለጠው ግን የዚህን ሕግ ቃል ሁሉ እንከተል ዘንድ ለዘላለም የእኛና የልጆቻችን ነው።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

申命記 29:1-29

在摩押立約

1耶和華除了與以色列人在何烈山立約外,還在摩押吩咐摩西以色列人立以下的約。

2摩西召來所有以色列人,對他們說:「你們曾親眼見過耶和華在埃及怎樣對付法老及其臣僕和國民, 3怎樣降下巨大的災難,行偉大的神蹟奇事。 4但耶和華至今還沒有賜給你們能明白的心、能看見的眼、能聽清的耳。 5四十年來,我領你們走過曠野,你們身上的衣服沒有穿破,腳上的鞋子沒有穿壞; 6你們沒有吃餅,也沒有喝淡酒和烈酒。這是為了讓你們知道耶和華是你們的上帝。 7我們來到這裡的時候,希實本西宏巴珊都來攻擊我們,我們擊敗了他們, 8並將佔領的土地分給呂便支派、迦得支派和瑪拿西半個支派作產業。 9所以,你們要謹遵這約上的話,以便你們可以凡事順利。

10「今天,你們全都站在你們的上帝耶和華面前,包括你們的族長、長老、官員、所有以色列男子、 11你們的孩子、妻子和寄居在你們中間為你們砍柴挑水的外族人, 12為要接受你們的上帝耶和華與你們立的誓約。 13這樣,祂今天將宣告你們是祂的子民、祂是你們的上帝,正如祂對你們的應許和對你們祖先亞伯拉罕、撒和各的誓言。 14耶和華的這誓約不僅是與你們立的, 15也是與今天一同站在我們的上帝耶和華面前的人,以及今天不在這裡的人29·15 今天不在這裡的人」或譯「我們將來的子孫」。立的。

16「你們知道我們如何在埃及生活,也知道我們如何穿越列國來到這裡。 17你們也見過他們用木、石、金、銀造的可憎神像。 18你們中間,不論男人或女人,家族或支派,切不可有人背棄我們的上帝耶和華,去祭拜列國的神明,免得你們中間有殘根長出苦毒的果實, 19免得有人聽了這誓言後,心存僥倖地說,『即使我一意孤行,連累他人,也必平安無事。』 20耶和華絕不會赦免這樣的人,祂必向這樣的人發烈怒,使記在這書上的一切咒詛臨到他身上,從世上抹去他的名字。 21耶和華必把他從以色列各支派中隔離出來,使他按律法書上約中的一切咒詛受懲罰。

22「你們的子孫後代和從遠方來的外族人,必看見耶和華降在這地方的災禍和疾病。 23遍地將是硫磺和鹽,無法耕種,寸草不生,如同耶和華盛怒之下毀滅的所多瑪蛾摩拉押瑪洗扁24萬國必問,『耶和華為什麼要這樣對待這地方?祂為什麼大發烈怒?』 25必有人回答說,『因為這地方的人背棄了他們祖先的上帝耶和華領他們出埃及時與他們所立的約, 26去供奉、祭拜他們所不認識、並非耶和華所分派的神明。 27因此,耶和華向這片土地發怒,把這書上的一切咒詛都降在這裡。 28耶和華盛怒之下把他們從這地方連根拔起,扔到別的地方,正如今日的情形。』

29「奧秘的事屬於我們的上帝耶和華,只有顯明的事永遠屬於我們和我們的子孫,以便我們可以遵守這律法上的一切話。」