ዘዳግም 10 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዘዳግም 10:1-22

በድጋሚ የተሰጡ የመጀመሪያዎቹ ዐይነት ጽላቶች

1በዚያን ጊዜ እግዚአብሔር (ያህዌ) እንዲህ አለኝ፤ “እንደ መጀመሪያዎቹ ያሉ ሁለት የድንጋይ ጽላቶች ቀርጸህ ወደ እኔ ወደ ተራራው ላይ ውጣ፤ ታቦትም ከዕንጨት ሥራ። 2እኔም አንተ በሰበርሃቸው በፊተኞቹ ጽላቶች ላይ የነበሩትን ቃላት በእነዚህኞቹ ጽላቶች ላይ እጽፋቸዋለሁ፤ አንተም በታቦቱ ውስጥ ታኖራቸዋለህ።”

3ስለዚህ ከግራር ዕንጨት ታቦት ሠራሁ፤ እንደ ፊተኞቹ ያሉ ሁለት የድንጋይ ጽላቶች ቀረጽሁ፤ ሁለቱንም ጽላቶች በእጆቼ ይዤ ወደ ተራራው ወጣሁ። 4እግዚአብሔር (ያህዌ) በስብሰባው ቀን፣ በእሳት ውስጥ ሆኖ ለእናንተ የተናገራቸውንና ቀድሞ ጽፏቸው የነበሩትን ዐሥሩን ትእዛዞች በእነዚህ ጽላቶች ላይ ጻፋቸው። እግዚአብሔርም (ያህዌ) እነርሱን ለእኔ ሰጠኝ። 5ከዚያም ከተራራው ተመልሼ ወረድሁ፤ እግዚአብሔር (ያህዌ) ባዘዘኝ መሠረት በሠራሁት ታቦትም ውስጥ፣ ጽላቶቹን አስቀመጥኋቸው፤ አሁንም እዚያ ናቸው።

6እስራኤላውያን ከብኤሮት ብኔያዕቃን፣ የያዕቃን ልጆች ከቈፈሯቸው የውሃ ጕድጓዶች ተነሥተው ወደ ሞሴራ ተጓዙ፤ አሮንም በዚያ ቦታ ሞቶ ተቀበረ፤ ልጁ አልዓዛር በእርሱ ምትክ ካህን ሆነ። 7ከዚያም ተነሥተው ጕድጎዳ ወደ ተባለ ስፍራ፣ ቀጥሎም የውሃ ፈሳሾች ወዳሉባት ዮጥባታ ወደምትባል ምድር ተጓዙ። 8በዚያን ጊዜ፣ ዛሬም እንደሚያደርገው ያገለግል ዘንድ፣ በእግዚአብሔርም (ያህዌ) ፊት እንዲቆምና በስሙ እንዲባርክ የእግዚአብሔርንም (ያህዌ) የኪዳኑን ታቦት እንዲሸከም እግዚአብሔር (ያህዌ) የሌዊን ነገድ ለየ። 9ሌዋዊ በወንድሞቹ መካከል ድርሻም ሆነ ርስት የሌለው ከዚህ የተነሣ ነው፤ አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) በነገረው መሠረት ርስቱ እግዚአብሔር (ያህዌ) ነው።

10እኔም በመጀመሪያው ጊዜ እንዳደረግሁት፣ በተራራው ላይ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ቈየሁ፤ በዚህ ጊዜም እግዚአብሔር (ያህዌ) እንደ ገና ሰማኝ፤ እግዚአብሔር (ያህዌ) አንተን ሊያጠፋ አልፈቀደም። 11ስለዚህም እግዚአብሔር (ያህዌ)፣ “ሂድ፤ ለአባቶቻቸው ለመስጠት ወደ ማልሁላቸው ምድር ገብተው እንዲወርሱ ሕዝቡን ምራ” አለኝ።

እግዚአብሔርን (ያህዌ) ፍራ

12አሁንም እስራኤል ሆይ፤ አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ከአንተ የሚፈልገው ምንድን ነው? አምላክህን እግዚአብሔርን (ኤሎሂም ያህዌ) እንድትፈራው፣ በመንገዶቹ ሁሉ እንድትሄድ፣ እንድትወድደው፣ በፍጹም ልብህ፣ በፍጹም ነፍስህ እንድታገለግለው፣ 13መልካም እንዲሆንልህና ዛሬ እኔ የምሰጥህን ትእዛዞችና ሥርዐቶች እንድትጠብቅ አይደለምን?

14ሰማያት፣ ሰማየ ሰማያት፣ ምድርና በእርሷም ያለው ሁሉ የአምላክህ የእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ነው። 15ነገር ግን እግዚአብሔር (ያህዌ) አባቶችህን ስላፈቀረ፣ ወደዳቸው፤ ዛሬም እንደ ሆነው የእነርሱ ዘር የሆናችሁትን እናንተን ከአሕዛብ ሁሉ ለይቶ መረጣችሁ። 16ስለዚህ የልባችሁን ሸለፈት ግረዙት፤ ከእንግዲህም ወዲያ ዐንገተ ደንዳና አትሁኑ። 17አምላካችሁ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) የአማልክት አምላክ (ኤሎሂም)፣ የጌቶች ጌታ (አዶናይ) ታላቅ አምላክ (ኤሎሂም)፣ ኀያልና የሚያስፈራ፣ አድልዎ የማያደርግ፣ መማለጃም የማይቀበል ነውና። 18እርሱ አባት ለሌላቸውና ለመበለቶች ይፈርዳል፤ መጻተኛውንም ምግብና ልብስ በመስጠት ይወድዳል። 19ስለዚህ እናንተም በግብፅ ምድር መጻተኞች ነበራችሁና መጻተኛን ውደዱ። 20አምላክህን እግዚአብሔርን (ኤሎሂም ያህዌ) ፍራ፤ አምልከውም፤ ከእርሱም ጋር ተጣበቅ፤ በስሙም ማል። 21እርሱ ውዳሴህ ነው፤ በገዛ ዐይኖችህ ያየሃቸውን፣ እነዚያን ታላላቅና አስፈሪ ነገሮች ያደረገልህ አምላክህ (ኤሎሂም) ነው። 22አባቶችህ ወደ ግብፅ ሲወርዱ ሰባ ነበሩ፤ አሁን ግን አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) እንደ ሰማይ ከዋክብት አብዝቶሃል።

Thai New Contemporary Bible

เฉลยธรรมบัญญัติ 10:1-22

แผ่นศิลาชุดที่สอง

1ครั้งนั้นองค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสสั่งข้าพเจ้าว่า “จงสกัดศิลาสองแผ่นเหมือนชุดแรกและทำหีบไม้สำหรับเก็บรักษา แล้วกลับขึ้นมาหาเราบนภูเขา 2เราจะจารึกข้อความเหมือนกับศิลาชุดแรกซึ่งเจ้าทำแตกไปแล้วนั้น และให้เจ้าเก็บรักษาแผ่นศิลาชุดใหม่นี้ไว้ในหีบ”

3ข้าพเจ้าจึงใช้ไม้กระถินเทศทำหีบและสกัดศิลาสองแผ่นเหมือนชุดแรก และข้าพเจ้าถือศิลาสองแผ่นขึ้นไปเข้าเฝ้าพระเจ้าบนภูเขา 4องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงจารึกข้อความเดียวกันกับครั้งก่อน คือบัญญัติสิบประการซึ่งทรงประกาศแก่ท่านจากเปลวไฟบนภูเขาในวันชุมนุมนั้น และองค์พระผู้เป็นเจ้าประทานศิลานั้นแก่ข้าพเจ้า 5ข้าพเจ้าก็ลงมาจากภูเขา แล้วเก็บแผ่นศิลาไว้ในหีบที่ข้าพเจ้าทำขึ้น ตามที่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงบัญชาข้าพเจ้าไว้ ซึ่งศิลานั้นยังคงอยู่ในหีบนั้นตราบจนบัดนี้

6(ชนอิสราเอลเดินทางจากบ่อน้ำของชาวยาอาคานมายังโมเสราห์ ที่ซึ่งอาโรนสิ้นชีวิตลงและถูกฝังไว้ เอเลอาซาร์บุตรของเขาดำรงตำแหน่งปุโรหิตสืบต่อมา 7จากที่นั่นพวกเขาเดินทางต่อมาถึงกุดโกดาห์และต่อมาถึงโยทบาธาห์ซึ่งเป็นดินแดนแห่งธารน้ำ 8ครั้งนั้นองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงคัดเลือกเผ่าเลวีให้หามหีบพันธสัญญาขององค์พระผู้เป็นเจ้าให้เข้าเฝ้ารับใช้ต่อหน้าองค์พระผู้เป็นเจ้าและกล่าวอวยพรในพระนามของพระองค์ดังที่พวกเขายังทำอยู่ตราบจนทุกวันนี้ 9ฉะนั้นเผ่าเลวีจึงไม่ได้รับส่วนแบ่งที่ดินเป็นกรรมสิทธิ์ในหมู่พี่น้อง องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงเป็นกรรมสิทธิ์ของเขาตามที่พระยาห์เวห์พระเจ้าของท่านรับสั่งกับเขา)

10ส่วนข้าพเจ้าได้อยู่บนภูเขาสี่สิบวันสี่สิบคืนเหมือนคราวแรก ครั้งนี้องค์พระผู้เป็นเจ้าก็ทรงรับฟังข้าพเจ้าอีกเช่นกัน พระองค์ไม่ได้ทรงประสงค์จะทำลายท่าน 11องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับข้าพเจ้าว่า “ลุกขึ้นเถิด นำประชากรไปตามทางของเขา เพื่อเขาจะได้เข้าครอบครองดินแดนที่เราปฏิญาณไว้กับบรรพบุรุษของเขาว่าจะยกให้เขา”

จงยำเกรงองค์พระผู้เป็นเจ้า

12บัดนี้อิสราเอลเอ๋ย พระยาห์เวห์พระเจ้าของท่านไม่ได้ทรงประสงค์สิ่งอื่นใด นอกเสียจากให้ท่านยำเกรงพระยาห์เวห์พระเจ้าของท่าน ให้ดำเนินในวิถีทั้งปวงของพระองค์ รักพระองค์ ปรนนิบัติพระยาห์เวห์พระเจ้าของท่านด้วยสุดจิตสุดใจ 13และยึดถือปฏิบัติตามพระบัญชาและกฎหมายขององค์พระผู้เป็นเจ้าซึ่งข้าพเจ้าแจ้งท่านในวันนี้ เพื่อประโยชน์สุขของท่านเอง

14พระยาห์เวห์พระเจ้าของท่านทรงเป็นเจ้าของฟ้าสวรรค์ ทั้งฟ้าสวรรค์อันสูงสุดและโลกกับสรรพสิ่งในนั้นด้วย 15แต่ถึงอย่างนั้นองค์พระผู้เป็นเจ้ายังทรงรักและโปรดปรานบรรพบุรุษของท่าน จึงได้เลือกสรรท่านทั้งหลายผู้เป็นวงศ์วานให้อยู่เหนือชนชาติอื่นทั้งปวงดังเช่นทุกวันนี้ 16ฉะนั้นจงเข้าสุหนัตใจของท่าน อย่าดื้อรั้นหัวแข็งอีกต่อไป 17เพราะพระยาห์เวห์พระเจ้าของท่านทรงเป็นองค์พระผู้เป็นเจ้าเหนือพระทั้งปวง ทรงเป็นจอมเจ้านายเหนือเจ้านายทั้งหลาย ทรงเป็นพระเจ้าผู้ยิ่งใหญ่ ทรงฤทธิ์และน่าเกรงขาม ผู้ทรงปราศจากอคติและไม่ทรงเห็นแก่อามิสสินจ้าง 18พระองค์ทรงดูแลปกป้องลูกกำพร้าพ่อและหญิงม่าย ทรงรักคนต่างด้าว ประทานอาหารและเครื่องนุ่งห่มแก่พวกเขา 19ดังนั้นพวกท่านจงรักคนต่างด้าว เพราะพวกท่านเองเคยเป็นคนต่างด้าวในอียิปต์ 20จงยำเกรงพระยาห์เวห์พระเจ้าของท่านและปรนนิบัติพระองค์ จงยึดมั่นในพระองค์และปฏิญาณโดยอ้างพระนามของพระองค์ 21จงสรรเสริญพระองค์ผู้ทรงเป็นพระเจ้าของท่าน ผู้ทรงสำแดงปาฏิหาริย์อันยิ่งใหญ่และน่าครั่นคร้ามเพื่อท่าน ซึ่งท่านเองได้เห็นกับตาแล้ว 22เมื่อบรรพบุรุษของท่านลงไปอียิปต์นั้นมีเพียงเจ็ดสิบคน แต่เดี๋ยวนี้พระยาห์เวห์พระเจ้าของท่านทรงให้ท่านมีจำนวนมากมายดุจดวงดาวในท้องฟ้า