ዘዳግም 10 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

ዘዳግም 10:1-22

በድጋሚ የተሰጡ የመጀመሪያዎቹ ዐይነት ጽላቶች

1በዚያን ጊዜ እግዚአብሔር (ያህዌ) እንዲህ አለኝ፤ “እንደ መጀመሪያዎቹ ያሉ ሁለት የድንጋይ ጽላቶች ቀርጸህ ወደ እኔ ወደ ተራራው ላይ ውጣ፤ ታቦትም ከዕንጨት ሥራ። 2እኔም አንተ በሰበርሃቸው በፊተኞቹ ጽላቶች ላይ የነበሩትን ቃላት በእነዚህኞቹ ጽላቶች ላይ እጽፋቸዋለሁ፤ አንተም በታቦቱ ውስጥ ታኖራቸዋለህ።”

3ስለዚህ ከግራር ዕንጨት ታቦት ሠራሁ፤ እንደ ፊተኞቹ ያሉ ሁለት የድንጋይ ጽላቶች ቀረጽሁ፤ ሁለቱንም ጽላቶች በእጆቼ ይዤ ወደ ተራራው ወጣሁ። 4እግዚአብሔር (ያህዌ) በስብሰባው ቀን፣ በእሳት ውስጥ ሆኖ ለእናንተ የተናገራቸውንና ቀድሞ ጽፏቸው የነበሩትን ዐሥሩን ትእዛዞች በእነዚህ ጽላቶች ላይ ጻፋቸው። እግዚአብሔርም (ያህዌ) እነርሱን ለእኔ ሰጠኝ። 5ከዚያም ከተራራው ተመልሼ ወረድሁ፤ እግዚአብሔር (ያህዌ) ባዘዘኝ መሠረት በሠራሁት ታቦትም ውስጥ፣ ጽላቶቹን አስቀመጥኋቸው፤ አሁንም እዚያ ናቸው።

6እስራኤላውያን ከብኤሮት ብኔያዕቃን፣ የያዕቃን ልጆች ከቈፈሯቸው የውሃ ጕድጓዶች ተነሥተው ወደ ሞሴራ ተጓዙ፤ አሮንም በዚያ ቦታ ሞቶ ተቀበረ፤ ልጁ አልዓዛር በእርሱ ምትክ ካህን ሆነ። 7ከዚያም ተነሥተው ጕድጎዳ ወደ ተባለ ስፍራ፣ ቀጥሎም የውሃ ፈሳሾች ወዳሉባት ዮጥባታ ወደምትባል ምድር ተጓዙ። 8በዚያን ጊዜ፣ ዛሬም እንደሚያደርገው ያገለግል ዘንድ፣ በእግዚአብሔርም (ያህዌ) ፊት እንዲቆምና በስሙ እንዲባርክ የእግዚአብሔርንም (ያህዌ) የኪዳኑን ታቦት እንዲሸከም እግዚአብሔር (ያህዌ) የሌዊን ነገድ ለየ። 9ሌዋዊ በወንድሞቹ መካከል ድርሻም ሆነ ርስት የሌለው ከዚህ የተነሣ ነው፤ አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) በነገረው መሠረት ርስቱ እግዚአብሔር (ያህዌ) ነው።

10እኔም በመጀመሪያው ጊዜ እንዳደረግሁት፣ በተራራው ላይ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ቈየሁ፤ በዚህ ጊዜም እግዚአብሔር (ያህዌ) እንደ ገና ሰማኝ፤ እግዚአብሔር (ያህዌ) አንተን ሊያጠፋ አልፈቀደም። 11ስለዚህም እግዚአብሔር (ያህዌ)፣ “ሂድ፤ ለአባቶቻቸው ለመስጠት ወደ ማልሁላቸው ምድር ገብተው እንዲወርሱ ሕዝቡን ምራ” አለኝ።

እግዚአብሔርን (ያህዌ) ፍራ

12አሁንም እስራኤል ሆይ፤ አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ከአንተ የሚፈልገው ምንድን ነው? አምላክህን እግዚአብሔርን (ኤሎሂም ያህዌ) እንድትፈራው፣ በመንገዶቹ ሁሉ እንድትሄድ፣ እንድትወድደው፣ በፍጹም ልብህ፣ በፍጹም ነፍስህ እንድታገለግለው፣ 13መልካም እንዲሆንልህና ዛሬ እኔ የምሰጥህን ትእዛዞችና ሥርዐቶች እንድትጠብቅ አይደለምን?

14ሰማያት፣ ሰማየ ሰማያት፣ ምድርና በእርሷም ያለው ሁሉ የአምላክህ የእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ነው። 15ነገር ግን እግዚአብሔር (ያህዌ) አባቶችህን ስላፈቀረ፣ ወደዳቸው፤ ዛሬም እንደ ሆነው የእነርሱ ዘር የሆናችሁትን እናንተን ከአሕዛብ ሁሉ ለይቶ መረጣችሁ። 16ስለዚህ የልባችሁን ሸለፈት ግረዙት፤ ከእንግዲህም ወዲያ ዐንገተ ደንዳና አትሁኑ። 17አምላካችሁ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) የአማልክት አምላክ (ኤሎሂም)፣ የጌቶች ጌታ (አዶናይ) ታላቅ አምላክ (ኤሎሂም)፣ ኀያልና የሚያስፈራ፣ አድልዎ የማያደርግ፣ መማለጃም የማይቀበል ነውና። 18እርሱ አባት ለሌላቸውና ለመበለቶች ይፈርዳል፤ መጻተኛውንም ምግብና ልብስ በመስጠት ይወድዳል። 19ስለዚህ እናንተም በግብፅ ምድር መጻተኞች ነበራችሁና መጻተኛን ውደዱ። 20አምላክህን እግዚአብሔርን (ኤሎሂም ያህዌ) ፍራ፤ አምልከውም፤ ከእርሱም ጋር ተጣበቅ፤ በስሙም ማል። 21እርሱ ውዳሴህ ነው፤ በገዛ ዐይኖችህ ያየሃቸውን፣ እነዚያን ታላላቅና አስፈሪ ነገሮች ያደረገልህ አምላክህ (ኤሎሂም) ነው። 22አባቶችህ ወደ ግብፅ ሲወርዱ ሰባ ነበሩ፤ አሁን ግን አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) እንደ ሰማይ ከዋክብት አብዝቶሃል።

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

申命记 10:1-22

摩西重新接受诫命

1“当时耶和华对我说,‘你要凿两块石版,与前两块一样,也要做一个木柜,然后上山来见我。 2我要把你摔碎的那两块石版上的话重新写在你凿的石版上。你要把它们放在柜子里。’ 3于是,我用皂荚木做了一个柜子,又凿了两块石版,与前两块石版一样,然后带着石版上了山。 4耶和华把你们在山脚下聚会时祂在山上的火焰中向你们颁布的十条诫命,重新刻在石版上,并把石版交给我。 5我下山后,遵照耶和华的吩咐把石版放在我做的柜子里。现在石版仍放在那里。

6“我们从亚干人的井10:6 亚干人的井”或译“比罗比尼·亚干”或“比尼亚干井”。出发,来到摩西拉亚伦死在那里,并葬在那里,他儿子以利亚撒接替他做大祭司。 7我们从那里走到谷歌大,又走到溪流之乡约巴他8那时,耶和华把利未支派分别出来,派他们抬祂的约柜,站立在祂面前事奉祂,奉祂的名祝福,至今未变。 9因此,利未人在众支派中没有分到土地作产业,耶和华是他们的产业,这是你们的上帝耶和华对他们的应许。

10“和前一次一样,我又在山上待了四十昼夜,耶和华又听了我的祈求,答应不毁灭你们。 11耶和华对我说,‘起来,带他们走吧,去占领我起誓赐给他们祖先的土地。’

耶和华的要求

12以色列人啊,你们的上帝耶和华对你们有何要求?无非要你们敬畏祂,遵行祂的旨意,爱祂,全心全意地事奉祂, 13遵守祂的诫命和律例。我今天把这些诫命和律例赐给你们,是为了你们的益处。 14看啊,诸天、大地和万物都属于你们的上帝耶和华。 15但耶和华只喜爱你们的祖先,从万族中拣选了他们的后裔——你们,正如今日的情形。 16所以,你们要洗心革面,不可再顽固不化。 17你们的上帝耶和华是万神之神、万主之主,是伟大、全能、可畏的上帝。祂不徇情面,不受贿赂; 18祂为孤儿寡妇主持公道,关爱寄居者,供给他们衣食。 19所以,你们要爱寄居者,因为你们也曾寄居埃及20你们要敬畏你们的上帝耶和华,事奉祂,倚靠祂,凭祂的名起誓。 21你们要赞美祂,祂是你们的上帝,你们亲眼目睹了祂为你们做的伟大而可畏的事。 22当年你们祖先下埃及时,只有七十人,现在你们的上帝耶和华使你们多如天上的星辰。