ዘካርያስ 6 – NASV & KLB

New Amharic Standard Version

ዘካርያስ 6:1-15

አራቱ ሠረገሎች

1እንደ ገናም ወደ ላይ ተመለከትሁ፤ እነሆ አራት ሠረገሎች ከሁለት ተራራ መካከል ሲወጡ አየሁ፤ ተራሮቹም የናስ ተራሮች ነበሩ። 2የመጀመሪያው ሠረገላ መጋላ፣ ሁለተኛው ዱሪ፤ 3ሦስተኛው ዐምባላይ፤ አራተኛውም ዝጕርጕር ፈረሶች ነበሯቸው፤ ሁሉም ጠንካሮች ነበሩ። 4እኔም ከእኔ ጋር ይነጋገር የነበረውን መልአክ፣ “ጌታዬ ሆይ፤ እነዚህ ምንድን ናቸው?” አልሁት።

5መልአኩም እንዲህ አለኝ፤ “እነዚህ አራቱ ቆመው ከነበሩበት ከምድር ሁሉ ጌታ ፊት የወጡ የሰማይ መናፍስት6፥5 ወይም ነፋሳት ሊሆን ይችላል። ናቸው። 6የባለ ዱሪ ፈረሶች ወደ ሰሜን፤ የባለ አምባላይ ፈረሶች ወደ ምዕራብ6፥6 ወይም ከኋላቸው ፈረሶች እንደ ማለት ነው። አገር፣ የባለ ዝጕርጕር ፈረሶች ወደ ደቡብ አገር ይወጣል።” 7ጠንካሮቹ ፈረሶች ሲወጡ፣ በምድር ሁሉ ለመመላለስ አቈብቍበው ነበር። እርሱም፣ “ወደ ምድር ሁሉ ሂዱ” አላቸው፤ እነርሱም ወደ ምድር ሁሉ ሄዱ። 8ከዚያም ጮኾ እንዲህ አለኝ፤ “እነሆ፤ ወደ ሰሜን አገር የሚወጡት፣ መንፈሴን በሰሜን ምድር አሳርፈውታል።”

ለኢያሱ የተደረገለት አክሊል

9የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤ 10“ከባቢሎን ከመጡት ምርኮኞች ከሔልዳይና ከጦብያ፣ ከዮዳኤም ወርቅና ብር ውሰድ፤ በዚያው ቀን ወደ ሶፎንያስ ልጅ ወደ ኢዮስያስ ቤት ሂድ። 11ወርቁንና ብሩን ወስደህ አክሊል ሥራ፤ በኢዮሴዴቅ ልጅ በሊቀ ካህኑ በኢያሱ ራስ ላይም አድርገው፤ 12ለእርሱም እግዚአብሔር ጸባኦት እንዲህ ይላል ብለህ ንገረው፤ ‘እነሆ፤ ስሙ ቅርንጫፍ የተባለው ሰው ይህ ነው፤ እርሱም በቦታው ይንሰራፋል፤ የእግዚአብሔርንም ቤተ መቅደስ ይሠራል። 13የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ የሚሠራው እርሱ ነው፤ ክብርን ይጐናጸፋል፤ በዙፋኑ ተቀምጦ ይገዛል፤ በዙፋኑም ላይ ካህን ይሆናል፤ በሁለቱም መካከል ስምምነት ይኖራል።’ 14አክሊሉም ለሔሌምና6፥14 ሲርያክ፤ ዕብራይስጡ ሔሌም ይላል። ለጦብያ፣ ለዮዳኤና ለሶፎንያስ ልጅ ለሔን6፥14 ወይም ርኅሩኁ እንደ ማለት ነው። በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ውስጥ መታሰቢያ ይሆናል። 15እነዚያ በሩቅ ያሉት መጥተው የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ሲሠራ ያግዛሉ፤ እናንተም እግዚአብሔር ጸባኦት እንደ ላከኝ ታውቃላችሁ። ለአምላካችሁ ለእግዚአብሔር በጥንቃቄ ብትታዘዙ ይህ ይሆናል።”

Korean Living Bible

스가랴 6:1-15

네 대의 전차

1내가 다시 살펴보니 네 대의 전차가 놋으로 된 두 산 사이에서 나오고 있었다.

2그 첫번째 전차는 붉은 말들이 끌고 두 번째 전차는 검은 말들이,

3세 번째 전차는 백마들이, 네 번째 전차는 얼룩말들이 끌었다.

4내가 나에게 말하던 천사에게 “내 주여, 이것들이 무엇입니까?” 하고 묻자

5그가 나에게 “이것들은 하늘의 6:5 또는 ‘네바람’네 영인데 온 세상의 주 앞에 섰다가 나가는 것이다” 하고 대답해 주었다.

6검은 말들이 끄는 전차가 북쪽으로 나가자 백마들은 서쪽으로, 얼룩말들은 남쪽으로 갔다.

7그 건장한 말들이 다 나가서 땅을 두루 돌아다니려 하므로 여호와께서 “너희는 가서 땅을 두루 돌아다녀라” 하고 말씀하셨다. 그래서 그들은 곧 나가서 땅을 순회하였다.

8그때 여호와께서 나를 부르시며 “북쪽으로 간 자들이 내 노여움을 가라앉혔다” 하고 말씀하셨다.

여호수아에게 면류관을 씌우라는 명령

9여호와께서 또 나에게 말씀하셨다.

10“너는 바빌로니아의 포로 생활에서 돌아온 헬대와 도비야와 여다야에게 예물을 받고 곧장 스바냐의 아들 요시야의 집으로 가서

11그들에게서 받은 은과 금으로 면류관을 만들어 여호사닥의 아들인 대제사장 여호수아의 머리에 씌우고

12그에게 전능한 나 여호와가 이렇게 말한다고 일러 주어라. ‘가지라고 부르는 사람이 자기가 있는 곳에서 나와 나 여호와의 성전을 건축할 것이다.

13그가 성전을 짓고 영광을 얻을 것이며 왕위에 앉아 왕으로서, 제사장으로서 자기 백성을 다스릴 것이니 6:13 또는 ‘이 두 사이에 평화의 의논이 있으리라’그 둘 사이에 완전한 조화가 있을 것이다.’

14“그리고 그 면류관은 6:14 히 ‘헬렘’헬대와 도비야와 여다야와 스바냐의 아들인 6:14 히 ‘헨’요시야를 기념하는 뜻으로 성전에 두도록 하라.

156:15 암시됨.너는 또 그들에게 이렇게 말하라. ‘멀리 있는 사람들이 와서 여호와의 성전 건축을 도울 것이다. 그러면 너희가 전능하신 여호와께서 나를 보내신 줄 알게 될 것이다. 너희가 만일 너희 하나님 여호와의 명령에 전적으로 순종하면 이 모든 일이 그대로 이루어질 것이다.’ ”