ዘካርያስ 4 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

ዘካርያስ 4:1-14

የወርቁ መቅረዝና ሁለቱ የወይራ ዛፎች

1ከእኔ ጋር ይነጋገር የነበረው መልአክም ተመልሶ፣ አንድ ሰው ከእንቅልፉ እንደሚነቃ አነቃኝ፤ 2እርሱም፣ “ምን ታያለህ?” አለኝ።

እኔም እንዲህ አልሁ፤ “እነሆ፤ በዐናቱ ላይ የዘይት ማሰሮ ያለበት ሁለንተናው ወርቅ የሆነ መቅረዝ አየሁ፤ በመቅረዙም ላይ ሰባት ቧንቧዎች ያሏቸው ሰባት መብራቶች ነበሩ። 3ደግሞም አንዱ ከዘይቱ ማሰሮ በስተ ቀኝ፣ ሌላውም በስተ ግራ የሆኑ ሁለት የወይራ ዛፎች አሉ።”

4ያነጋግረኝ የነበረውንም መልአክ፣ “ጌታዬ ሆይ፤ እነዚህ ምንድን ናቸው” አልሁት።

5እርሱም፣ “ምን እንደ ሆኑ አታውቅምን?” አለኝ።

እኔም፣ “ጌታዬ ሆይ፤ አላውቅም” አልሁት።

6ከዚያም እንዲህ አለኝ፤ “ለዘሩባቤል የተላከው የእግዚአብሔር ቃል ይህ ነው፤ ‘በመንፈሴ እንጂ በኀይልና በብርታት አይደለም’ ይላል እግዚአብሔር ጸባኦት።

7“ታላቅ ተራራ ሆይ፤ አንተ ምንድን ነህ?4፥7 ወይም ማለት ነህ በዘሩባቤል ፊት ደልዳላ ሜዳ ትሆናለህ፤ ሰዎች፣ ‘ሞገስ ይሁንለት! ሞገስ ይሁንለት!’ ብለው እየጮኹ፣ እርሱ መደምደሚያውን ድንጋይ ያወጣል።”

8ደግሞም የእግዚአብሔር ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ፤ 9“የዘሩባቤል እጆች የዚህን ቤተ መቅደስ መሠረት ጣሉ፤ የሚፈጽሙትም የእርሱ እጆች ናቸው። ከዚያም እግዚአብሔር ጸባኦት እኔን ወደ እናንተ እንደ ላከኝ ታውቃላችሁ።

10“የጥቂቱን ነገር ቀን የናቀ ማን ነው? ሰዎች በዘሩባቤል እጅ ቱንቢውን ሲያዩ ይደሰታሉ።

“እነዚህ ሰባቱ በምድር ሁሉ የሚዘዋወሩ የእግዚአብሔር ዐይኖች ናቸው።”

11ከዚያም መልአኩን፣ “ከመቅረዙ በስተ ቀኝና በስተ ግራ ያሉት እነዚህ ሁለት የወይራ ዛፎች ምንድን ናቸው?” አልሁት።

12እንደ ገናም፣ “በሁለቱ የወርቅ ቧንቧዎች አጠገብ የወርቅ ዘይት የሚያፈስሱት እነዚህ ሁለት የወይራ ቅርንጫፎች ምንድን ናቸው?” አልሁት።

13እርሱም፣ “ምን እንደ ሆኑ አታውቅምን?” አለኝ።

እኔም፣ “ጌታዬ ሆይ፤ አላውቅም” አልሁት።

14እርሱም፣ “እነዚህ ሁለቱ የምድርን ሁሉ ጌታ ለማገልገል የተቀቡ4፥14 ወይም እና ሁለቱ ዘይትና የሚያመጡ ናቸው” አለኝ።

King James Version

Zechariah 4:1-14

1And the angel that talked with me came again, and waked me, as a man that is wakened out of his sleep, 2And said unto me, What seest thou? And I said, I have looked, and behold a candlestick all of gold, with a bowl upon the top of it, and his seven lamps thereon, and seven pipes to the seven lamps, which are upon the top thereof:4.2 a bowl: Heb. her bowl4.2 seven pipes…: or, seven several pipes to the lamps 3And two olive trees by it, one upon the right side of the bowl, and the other upon the left side thereof. 4So I answered and spake to the angel that talked with me, saying, What are these, my lord? 5Then the angel that talked with me answered and said unto me, Knowest thou not what these be? And I said, No, my lord. 6Then he answered and spake unto me, saying, This is the word of the LORD unto Zerubbabel, saying, Not by might, nor by power, but by my spirit, saith the LORD of hosts.4.6 might: or, army 7Who art thou, O great mountain? before Zerubbabel thou shalt become a plain: and he shall bring forth the headstone thereof with shoutings, crying, Grace, grace unto it. 8Moreover the word of the LORD came unto me, saying, 9The hands of Zerubbabel have laid the foundation of this house; his hands shall also finish it; and thou shalt know that the LORD of hosts hath sent me unto you. 10For who hath despised the day of small things? for they shall rejoice, and shall see the plummet in the hand of Zerubbabel with those seven; they are the eyes of the LORD, which run to and fro through the whole earth.4.10 for they…: or, since the seven eyes of the LORD shall rejoice4.10 plummet: Heb. stone of tin

11¶ Then answered I, and said unto him, What are these two olive trees upon the right side of the candlestick and upon the left side thereof? 12And I answered again, and said unto him, What be these two olive branches which through the two golden pipes empty the golden oil out of themselves?4.12 through: Heb. by the hand of4.12 empty…: or, empty out of themselves oil into the gold4.12 the golden oil: Heb. the gold 13And he answered me and said, Knowest thou not what these be? And I said, No, my lord. 14Then said he, These are the two anointed ones, that stand by the Lord of the whole earth.4.14 anointed…: Heb. sons of oil