ዘካርያስ 2 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዘካርያስ 2:1-13

የመለኪያ ገመድ የያዘ ሰው

1ደግሞም ወደ ላይ ተመለከትሁ፤ እነሆ፤ በእጁ የመለኪያ ገመድ የያዘ ሰውም በፊቴ አየሁ፤ 2እኔም፣ “የት ልትሄድ ነው?” አልሁት።

እርሱም፣ “የኢየሩሳሌም ርዝመትና ስፋት ምን ያህል እንደ ሆነ ለመለካት መሄዴ ነው፤” አለኝ።

3ከእኔ ጋር ይነጋገር የነበረው መልአክም ሄደ፤ ሌላም መልአክ ሊገናኘው መጣ፤ 4እንዲህም አለው፣ “ሩጥና ለዚያ ጕልማሳ እንዲህ ብለህ ንገረው፤ ‘በውስጧ ካለው የሰውና የከብት ብዛት የተነሣ፣ ኢየሩሳሌም ቅጥር እንደሌላት ከተማ ትሆናለች፤ 5እኔ ራሴ በዙሪያዋ የእሳት ቅጥር እሆንላታለሁ’ ይላል እግዚአብሔር፣ ‘በውስጧም ክብሯ እሆናለሁ።’

6“ኑ! ኑ! ውጡ፤ ከሰሜን ምድር አምልጡ” ይላል እግዚአብሔር፤ “ለአራቱ የሰማይ ነፋሳት በትኛችኋለሁና” ይላል እግዚአብሔር

7“አንቺ ጽዮን ነዪ፤ ከባቢሎን ሴት ልጅ ጋር የምትኖሪ ሆይ፤ ኰብልዪ።” 8እግዚአብሔር ጸባኦት እንዲህ ይላልና፤ “ካከበረኝና በዘረፏችሁ አሕዛብ ላይ ከላከኝ በኋላ፣ የሚነካችሁ የዐይኑን ብሌን ይነካል፤ 9እነሆ፤ እጄን በእነርሱ ላይ አነሣለሁ፤ ባሪያዎቻቸውም ይዘርፏቸዋል፤ ከዚያም እግዚአብሔር ጸባኦት እኔን እንደ ላከኝ ታውቃላችሁ።

10“የጽዮን ልጅ ሆይ፤ እልል በዪ፤ ደስም ይበልሽ፤ እኔ እመጣለሁና፤ በመካከልሽም እኖራለሁ” ይላል እግዚአብሔር11“በዚያ ቀን ብዙ አሕዛብ ወደ እግዚአብሔር ይጠጋሉ፤ የእኔም ሕዝብ ይሆናሉ። በመካከልሽ እኖራለሁ፤ እግዚአብሔር ጸባኦት ወደ አንቺ እንደ ላከኝም ታውቃላችሁ። 12እግዚአብሔርም በተቀደሰችው ምድር ይሁዳን ርስቱ አድርጎ ይወርሳል፤ ኢየሩሳሌምንም እንደ ገና ይመርጣል። 13እግዚአብሔር ከተቀደሰ ማደሪያው ተነሥቷልና፣ ሥጋ ለባሽ ሁሉ ሆይ፤ በፊቱ ጸጥ በል።”

Thai New Contemporary Bible

เศคาริยาห์ 2:1-13

ชายที่ถือสายวัด

1แล้วข้าพเจ้าเงยหน้าขึ้น เห็นชายคนหนึ่งถือสายวัดอยู่ต่อหน้าข้าพเจ้า! 2ข้าพเจ้าถามว่า “ท่านจะไปไหน?”

เขาตอบว่า “ไปวัดกรุงเยรูซาเล็มดูว่ากว้างยาวแค่ไหน”

3แล้วทูตสวรรค์ที่สนทนากับข้าพเจ้าก็จากไป มีทูตสวรรค์อีกองค์มาพบทูตองค์นั้น 4และกล่าวกับเขาว่า “วิ่งไปบอกชายหนุ่มผู้นั้นเถิดว่า ‘เยรูซาเล็มจะมีผู้คนและฝูงสัตว์อาศัยอยู่แน่นหนา จนทำกำแพงล้อมไว้ไม่ได้ 5และเราเองจะเป็นกำแพงไฟล้อมกรุงเยรูซาเล็ม และเป็นสง่าราศีในกรุงนั้น’ องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสดังนั้น”

6องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่า “มาเถิด! มาเถิด! จงหนีไปจากดินแดนภาคเหนือเพราะเราได้ทำให้เจ้ากระจัดกระจายไปกับลมทั้งสี่แห่งฟ้าสวรรค์” องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศดังนั้น

7“มาเถิดศิโยนเอ๋ย จงหนีเถิด เจ้าทั้งหลายผู้เป็นเชลยอยู่ในบาบิโลน2:7 ภาษาฮีบรูว่าธิดาแห่งบาบิโลน!” 8เพราะพระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์ตรัสดังนี้ว่า “หลังจากพระองค์ประทานเกียรติแก่เรา และทรงใช้เรามาต่อสู้กับชนชาติทั้งหลายที่มาปล้นเจ้า เพราะผู้ใดแตะต้องเจ้าก็แตะต้องแก้วพระเนตรของพระองค์ 9แน่นอนเราจะเงื้อมือขึ้นฟาดพวกเขา เพื่อทาสของพวกเขาจะปล้นพวกเขา แล้วเจ้าจะรู้ว่าพระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์ทรงใช้เรามา

10“ธิดาแห่งศิโยน2:10 คือ ชาวเยรูซาเล็มเอ๋ย จงโห่ร้องยินดีเถิด เพราะเรากำลังจะมา และเราจะอยู่ท่ามกลางพวกเจ้า” องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศดังนั้น 11“ชนชาติมากมายจะร่วมอยู่ฝ่ายองค์พระผู้เป็นเจ้าในวันนั้น และจะเป็นประชากรของเรา เราจะอยู่ท่ามกลางพวกเจ้า และพวกเจ้าจะรู้ว่าพระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์ทรงใช้เรามาหาพวกเจ้า 12องค์พระผู้เป็นเจ้าจะทรงให้ยูดาห์เป็นกรรมสิทธิ์ส่วนของพระองค์ในดินแดนบริสุทธิ์ และจะทรงเลือกสรรเยรูซาเล็มอีกครั้ง 13มวลมนุษยชาติเอ๋ย จงนิ่งสงบต่อหน้าองค์พระผู้เป็นเจ้า เพราะพระองค์เสด็จขึ้นจากที่ประทับอันบริสุทธิ์แล้ว”