ዘካርያስ 2 – NASV & NIV

New Amharic Standard Version

ዘካርያስ 2:1-13

የመለኪያ ገመድ የያዘ ሰው

1ደግሞም ወደ ላይ ተመለከትሁ፤ እነሆ፤ በእጁ የመለኪያ ገመድ የያዘ ሰውም በፊቴ አየሁ፤ 2እኔም፣ “የት ልትሄድ ነው?” አልሁት።

እርሱም፣ “የኢየሩሳሌም ርዝመትና ስፋት ምን ያህል እንደ ሆነ ለመለካት መሄዴ ነው፤” አለኝ።

3ከእኔ ጋር ይነጋገር የነበረው መልአክም ሄደ፤ ሌላም መልአክ ሊገናኘው መጣ፤ 4እንዲህም አለው፣ “ሩጥና ለዚያ ጕልማሳ እንዲህ ብለህ ንገረው፤ ‘በውስጧ ካለው የሰውና የከብት ብዛት የተነሣ፣ ኢየሩሳሌም ቅጥር እንደሌላት ከተማ ትሆናለች፤ 5እኔ ራሴ በዙሪያዋ የእሳት ቅጥር እሆንላታለሁ’ ይላል እግዚአብሔር፣ ‘በውስጧም ክብሯ እሆናለሁ።’

6“ኑ! ኑ! ውጡ፤ ከሰሜን ምድር አምልጡ” ይላል እግዚአብሔር፤ “ለአራቱ የሰማይ ነፋሳት በትኛችኋለሁና” ይላል እግዚአብሔር

7“አንቺ ጽዮን ነዪ፤ ከባቢሎን ሴት ልጅ ጋር የምትኖሪ ሆይ፤ ኰብልዪ።” 8እግዚአብሔር ጸባኦት እንዲህ ይላልና፤ “ካከበረኝና በዘረፏችሁ አሕዛብ ላይ ከላከኝ በኋላ፣ የሚነካችሁ የዐይኑን ብሌን ይነካል፤ 9እነሆ፤ እጄን በእነርሱ ላይ አነሣለሁ፤ ባሪያዎቻቸውም ይዘርፏቸዋል፤ ከዚያም እግዚአብሔር ጸባኦት እኔን እንደ ላከኝ ታውቃላችሁ።

10“የጽዮን ልጅ ሆይ፤ እልል በዪ፤ ደስም ይበልሽ፤ እኔ እመጣለሁና፤ በመካከልሽም እኖራለሁ” ይላል እግዚአብሔር11“በዚያ ቀን ብዙ አሕዛብ ወደ እግዚአብሔር ይጠጋሉ፤ የእኔም ሕዝብ ይሆናሉ። በመካከልሽ እኖራለሁ፤ እግዚአብሔር ጸባኦት ወደ አንቺ እንደ ላከኝም ታውቃላችሁ። 12እግዚአብሔርም በተቀደሰችው ምድር ይሁዳን ርስቱ አድርጎ ይወርሳል፤ ኢየሩሳሌምንም እንደ ገና ይመርጣል። 13እግዚአብሔር ከተቀደሰ ማደሪያው ተነሥቷልና፣ ሥጋ ለባሽ ሁሉ ሆይ፤ በፊቱ ጸጥ በል።”

New International Version

Zechariah 2:1-13

A Man With a Measuring Line

In Hebrew texts 2:1-13 is numbered 2:5-17. 1Then I looked up, and there before me was a man with a measuring line in his hand. 2I asked, “Where are you going?”

He answered me, “To measure Jerusalem, to find out how wide and how long it is.”

3While the angel who was speaking to me was leaving, another angel came to meet him 4and said to him: “Run, tell that young man, ‘Jerusalem will be a city without walls because of the great number of people and animals in it. 5And I myself will be a wall of fire around it,’ declares the Lord, ‘and I will be its glory within.’

6“Come! Come! Flee from the land of the north,” declares the Lord, “for I have scattered you to the four winds of heaven,” declares the Lord.

7“Come, Zion! Escape, you who live in Daughter Babylon!” 8For this is what the Lord Almighty says: “After the Glorious One has sent me against the nations that have plundered you—for whoever touches you touches the apple of his eye— 9I will surely raise my hand against them so that their slaves will plunder them.2:8,9 Or says after… eye: 9 “I… plunder them.” Then you will know that the Lord Almighty has sent me.

10“Shout and be glad, Daughter Zion. For I am coming, and I will live among you,” declares the Lord. 11“Many nations will be joined with the Lord in that day and will become my people. I will live among you and you will know that the Lord Almighty has sent me to you. 12The Lord will inherit Judah as his portion in the holy land and will again choose Jerusalem. 13Be still before the Lord, all mankind, because he has roused himself from his holy dwelling.”