ዘካርያስ 13 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

ዘካርያስ 13:1-9

ከኀጢአት መንጻት

1“በዚያ ቀን የዳዊትን ቤትና የኢየሩሳሌምን ነዋሪዎች ከኀጢአትና ከርኩሰት የሚያነጻ ምንጭ ይከፈታል።

2“በዚያ ቀን የጣዖታትን ስም ከምድሪቱ አጠፋለሁ፤ ከእንግዲህም አይታሰቡም” ይላል እግዚአብሔር ጸባኦት። “ነቢያትንና ርኩስ መንፈስን ከምድሪቱ አስወግዳለሁ። 3ማንም ትንቢት ቢናገር ወላጅ አባትና እናቱ፣ ‘በእግዚአብሔር ስም ሐሰት ተናግረሃልና ሞት ይገባሃል’ ይሉታል። ትንቢት ሲናገርም የገዛ ወላጆቹ ይወጉታል።

4“በዚያን ቀን እያንዳንዱ ነቢይ ስለሚናገረው የትንቢት ራእይ ያፍራል፤ ለማታለልም የነቢያትን ጠጕራም ልብስ አይለብስም። 5እርሱም፣ ‘እኔ ገበሬ እንጂ ነቢይ አይደለሁም፤ ከልጅነቴ13፥5 ወይም ዐራሽ፤ በወጣትነቴ የተሸጥሁ ሰው ጀምሮ ኑሮዬ የተመሠረተውም በዕርሻ ላይ ነው’ ይላል። 6አንድ ሰው፣ ‘ይህ በሰውነትህ13፥6 በእጆችህ መኻል ያሉ ቍሰሎች የሚሉ አሉ። ላይ ያለው ቍስል ምንድን ነው?’ ብሎ ቢጠይቀው፣ ‘በባልንጀሮቼ ቤት ሳለሁ የቈሰልሁት ነው’ ይላል።”

እረኛው ተመታ፤ በጎቹ ተበተኑ

7እግዚአብሔር ጸባኦት እንዲህ ይላል፤

“ሰይፍ ሆይ፤ በእረኛዬ፣

በቅርብ ወዳጄ ላይ ንቃ!

እረኛውን ምታ፣

በጎቹ ይበተናሉ፤

እኔም ክንዴን ወደ ታናናሾቹ አዞራለሁ።”

8እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “የምድር ሁሉ፣

ሁለት ሦስተኛው ተመትቶ ይጠፋል፤

አንድ ሦስተኛው ግን በውስጡ ይቀራል፤

9ይህን አንድ ሦስተኛውን ክፍል ወደ እሳት አመጣለሁ፤

እንደ ብር አነጥራቸዋለሁ፤

እንደ ወርቅም እፈትናቸዋለሁ፤

እነርሱ ስሜን ይጠራሉ፤

እኔም እመልስላቸዋለሁ፤

እኔም፣ ‘ሕዝቤ ናቸው’ እላለሁ፤

እነርሱም፣ ‘እግዚአብሔር አምላካችን ነው’ ይላሉ።”

Ketab El Hayat

زكريا 13:1-9

التطهير من الخطيئة

1«فِي ذَلِكَ الْيَوْمِ يَتَفَجَّرُ يَنْبُوعٌ لِيُطَهِّرَ ذُرِّيَّةَ دَاوُدَ وَسُكَّانَ أُورُشَلِيمَ مِنْ إِثْمِهِمْ وَنَجَاسَتِهِمْ. 2وَيَقُولُ الرَّبُّ الْقَدِيرُ: فِي ذَلِكَ الْيَوْمِ أَسْتَأْصِلُ أَسْمَاءَ الأَصْنَامِ مِنَ الأَرْضِ فَلا يَعُودُ لَهَا ذِكْرٌ، وَأُلاشِي الأَنْبِيَاءَ الْكَذَبَةَ وَالرُّوحَ النَّجِسَ مِنَ الأَرْضِ. 3وَإِنْ تَنَبَّأَ أَحَدٌ فِيمَا بَعْدُ، يَطْعَنُهُ أَبُوهُ وَأُمُّهُ اللَّذَانِ أَنْجَبَاهُ قَائِلَيْنِ: لابُدَّ أَنْ تَمُوتَ لأَنَّكَ نَطَقْتَ بِالزُّورِ بِاسْمِ الرَّبِّ. 4فِي ذَلِكَ الْيَوْمِ يَعْتَرِي الْخِزْيُ كُلَّ نَبِيٍّ كَاذِبٍ يَتَنَبَّأُ مِنْ رُؤْيَاهُ، وَلا يَرْتَدِي مُسُوحَ الشَّعْرِ لِيَكْذِبَ. 5إِنَّمَا يَقُولُ: أَنَا لَسْتُ نَبِيًّا. أَنَا رَجُلٌ فَلّاحٌ أَحْرُثُ الأَرْضَ مُنْذُ صِبَايَ. 6وَعِنْدَمَا يَسْأَلُهُ أَحَدٌ: مَا هَذِهِ الْجُرُوحُ فِي يَدَيْكَ؟ يُجِيبُهُ: هِيَ الَّتِي جُرِحْتُ بِها فِي بَيْتِ أَحِبَّائِي».

ضرب الراعي وتبددت الخراف

7وَيَقُولُ الرَّبُّ الْقَدِيرُ: «اسْتَيْقِظْ أَيُّهَا السَّيْفُ وَهَاجِمْ رَاعِيَّ وَرَجُلَ رِفْقَتِي. اضْرِبِ الرَّاعِي فَتَتَبَدَّدَ الْخِرَافُ. وَلَكِنِّي أَرُدُّ يَدِي عَنِ الصِّغَارِ (أَيِ الْقِلَّةِ الْمُؤْمِنَةِ). 8يَقُولُ الرَّبُّ فَيَفْنَى ثُلْثَا شَعْبِ أَرْضِي وَيَبْقَى ثُلْثُهُمْ حَيًّا فَقَطْ. 9فَأُجِيزُ هَذَا الثُّلْثَ فِي النَّارِ لأُنَقِّيَهُ تَنْقِيَةَ الْفِضَّةِ، وَأَمْحَصَهُ كَمَا يُمْحَصُ الذَّهَبُ. هُوَ يَدْعُو بِاسْمِي وَأَنَا أَسْتَجِيبُهُ. أَنَا أَقُولُ: هُوَ شَعْبِي، وَهُوَ يَقُولُ: الرَّبُّ هُوَ إِلَهِي».