ዘካርያስ 12 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዘካርያስ 12:1-14

የኢየሩሳሌም ጠላቶች እንደሚደመሰሱ የተነገረ ንግር

1ስለ እስራኤል የተነገረው የእግዚአብሔር ቃል ይህ ነው፤ ሰማያትን የዘረጋ፣ ምድርን የመሠረተ የሰውንም መንፈስ በውስጡ የሠራ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ 2“ኢየሩሳሌምን በዙሪያዋ ላሉት ሕዝቦች ሁሉ የሚያንገደግድ ጽዋ አደርጋታለሁ፤ ይሁዳም እንደ ኢየሩሳሌም ሁሉ ትከበባለች። 3የምድር አሕዛብ ሁሉ በእርሷ ላይ በሚሰበሰቡበት በዚያ ቀን፣ ኢየሩሳሌምን ለአሕዛብ ሁሉ የማይነቃነቅ ዐለት አደርጋታለሁ፤ ለማነቃነቅ የሚሞክሩ ሁሉ ራሳቸውን ይጐዳሉ። 4በዚያን ቀን እያንዳንዱን ፈረስ በድንጋጤ፣ የተቀመጡባቸውንም ሰዎች እብደት እመታለሁ” ይላል እግዚአብሔር። “የይሁዳን ቤት በዐይኔ እጠብቃለሁ፤ ነገር ግን የአሕዛብን ፈረሶች ሁሉ አሳውራለሁ። 5የይሁዳ መሪዎች በልባቸው፣ ‘የኢየሩሳሌም ሕዝቦች ብርቱ ናቸው፤ አምላካቸው እግዚአብሔር ጸባኦት ነውና’ ይላሉ።

6“በዚያ ቀን የይሁዳን መሪዎች በዕንጨት ክምር ውስጥ እንዳለ የእሳት ምድጃ፣ በነዶም መካከል እንዳለ የፋና ነበልባል አደርጋቸዋለሁ፤ በግራና በቀኝ ዙሪያውን ያሉትን ሕዝቦች ይበላሉ፤ ኢየሩሳሌም ግን ከስፍራዋ ንቅንቅ አትልም።

7“የዳዊት ቤትና የኢየሩሳሌም ነዋሪዎች ክብር ከይሁዳ ክብር እንዳይበልጥ እግዚአብሔር በመጀመሪያ የይሁዳን መኖሪያዎች ያድናል። 8ከመካከላቸው እጅግ ደካማ የሆነው እንደ ዳዊት፣ የዳዊት ቤትም ፊት ፊታቸው እንደሚሄድ እንደ እግዚአብሔር መልአክ፣ እንደ አምላክ ይሆንላቸው ዘንድ በኢየሩሳሌም የሚኖሩትን እግዚአብሔር ይከልላቸዋል። 9በዚያ ቀን ኢየሩሳሌምን በወጓት አሕዛብ ሁሉ ላይ እወጣለሁ።

ስለ ወጉት የተደረገ ሐዘን

10“በዳዊት ቤትና በኢየሩሳሌም ነዋሪዎች ላይ የርኅራኄና የልመና መንፈስ አፈስሳለሁ፤ ወደ ወጉኝ ወደ12፥10 ወይም ለእኔ ሊሆን ይችላል። እኔም ይመለከታሉ፤ እነርሱም ለአንድያ ልጅ እንደሚለቀስ ያለቅሱለታል፤ ለበኵር ልጅ ምርር ተብሎ እንደሚለቀስም አምርረው ያለቅሱለታል።” 11በዚያ ቀን በመጊዶን ሜዳ ለሐዳድሪሞን እንደ ተለቀሰ ሁሉ በኢየሩሳሌም የሚለቀሰውም እንደዚሁ ታላቅ ልቅሶ ይሆናል። 12ምድሪቱ ታለቅሳለች፤ የየነገዱ ወንዶች ለየራሳቸው ያለቅሳሉ፤ ሚስቶቻቸውም ለየራሳቸው ያለቅሳሉ፤ በዚህም ዐይነት የዳዊት ቤት ነገድ ወንዶች ከነሚስቶቻቸው፣ የናታን ቤት ነገድ ወንዶች ከነሚስቶቻቸው፣ 13የሌዊ ቤት ነገድ ወንዶች ከነሚስቶቻቸው፣ የሰሜኢ ቤት ነገድ ወንዶች ከነሚስቶቻቸው፣ 14የቀሩትም ነገዶች ወንዶች ሁሉ ከነሚስቶቻቸው ያለቅሳሉ።

Thai New Contemporary Bible

เศคาริยาห์ 12:1-14

ศัตรูของเยรูซาเล็มจะถูกทำลาย

1พระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้า ต่อไปนี้คือพระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้าเกี่ยวกับอิสราเอล องค์พระผู้เป็นเจ้าผู้ทรงคลี่ฟ้าสวรรค์ ผู้ทรงวางฐานรากของโลก ผู้ทรงสร้างวิญญาณในตัวมนุษย์ประกาศว่า 2“เราจะทำให้เยรูซาเล็มเป็นถ้วยที่ทำให้ชนชาติทั้งปวงซึ่งล้อมรอบกลิ้งไป ยูดาห์จะถูกล้อมเมืองเช่นเดียวกับเยรูซาเล็ม 3ในวันนั้นเมื่อมวลประชาชาติในโลกรวมตัวกันมาสู้กับเยรูซาเล็ม เราจะทำให้เยรูซาเล็มเป็นศิลาซึ่งชนชาติทั้งปวงไม่อาจขยับเขยื้อน คนที่พยายามจะขยับก็เจ็บตัว 4ในวันนั้นเราจะทำให้ม้าทุกตัวกลัวลานและผู้ขี่คลุ้มคลั่ง” องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศดังนี้ “เราจะจับตาดูพงศ์พันธุ์ยูดาห์ แต่จะทำให้ม้าทั้งปวงของชนชาติต่างๆ ตาบอด 5แล้วบรรดาผู้นำยูดาห์จะรำพึงว่า ‘ชาวเยรูซาเล็มเข้มแข็งเพราะมีพระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์เป็นพระเจ้าของพวกเขา’

6“ในวันนั้นเราจะทำให้บรรดาผู้นำยูดาห์เป็นดั่งไฟร้อนแดงกลางกองฟืน และเหมือนคบไฟลุกโชนกลางฟ่อนข้าว จะเผาผลาญชนชาติทั้งปวงที่อยู่ล้อมรอบทั้งซ้ายขวา ส่วนเยรูซาเล็มจะตั้งมั่นคงไม่ขยับเขยื้อน

7องค์พระผู้เป็นเจ้าจะทรงช่วยกองทัพยูดาห์ก่อน เพื่อเกียรติของพงศ์พันธุ์ดาวิดและชาวเยรูซาเล็มจะไม่เกินหน้ายูดาห์ 8ในวันนั้นองค์พระผู้เป็นเจ้าจะทรงปกป้องชาวเยรูซาเล็มเพื่อผู้อ่อนแอที่สุดในพวกเขาจะเหมือนดาวิด และพงศ์พันธุ์ดาวิดจะเป็นดั่งพระเจ้า เหมือนทูตขององค์พระผู้เป็นเจ้านำหน้าพวกเขาไป 9ในวันนั้นเราจะทำลายชนชาติทั้งปวงที่มาโจมตีเยรูซาเล็ม

บทคร่ำครวญแด่ผู้ถูกแทง

10“และเราจะให้พงศ์พันธุ์ดาวิดกับชาวเยรูซาเล็มมีวิญญาณ12:10 หรือพระวิญญาณแห่งพระคุณและการอธิษฐาน พวกเขาจะมองดู12:10 หรือหมายพึ่งเราผู้ที่พวกเขาได้แทง และจะไว้ทุกข์ให้เหมือนคนที่ไว้ทุกข์ให้ลูกคนเดียวของตน และร่ำไห้อย่างขมขื่นอาลัยผู้นั้นเหมือนอาลัยเมื่อลูกชายหัวปีของตนตาย 11ในวันนั้นจะมีการร่ำไห้ครั้งใหญ่ในเยรูซาเล็ม เหมือนการร่ำไห้ครั้งฮาดัดริมโมนในที่ราบเมกิดโด 12แผ่นดินจะไว้อาลัยแยกไปตามแต่ละตระกูล พวกภรรยาก็แยกต่างหากได้แก่ ตระกูลของดาวิดกับภรรยาของพวกเขา ตระกูลนาธันกับภรรยาของพวกเขา 13ตระกูลเลวีกับภรรยาของพวกเขา ตระกูลชิเมอีกับภรรยาของพวกเขา 14และตระกูลอื่นๆ ที่เหลือกับภรรยาของพวกเขา