1ሊባኖስ ሆይ፤ እሳት ዝግባሽን እንዲበላው
ደጆችሽን ክፈቺ!
2የጥድ ዛፍ ሆይ፤ ዝግባ ወድቋልና አልቅስ፤
የከበሩትም ዛፎች ጠፍተዋል!
የባሳን ወርካዎች ሆይ፤ አልቅሱ፤
ጥቅጥቅ ያለው ደን ተመንጥሯል!
3የእረኞችን ዋይታ ስሙ፤
ክብራቸው ተገፍፏልና፤
የአንበሶችን ጩኸት ስሙ፤
ጥቅጥቅ ያለው የዮርዳኖስ ደን ወድሟል!
ሁለቱ እረኞች
4እግዚአብሔር አምላኬ እንዲህ ይላል፤ “ለዕርድ የተለዩትን በጎች አሰማራ፤ 5የገዟቸው ያርዷቸዋል፤ ሳይቀጡም ይቀራሉ፤ የሸጧቸውም፣ ‘እግዚአብሔር ይመስገን፤ ባለጠጋ ሆኛለሁ’ ይላሉ፤ ጠባቂዎቻቸውም እንኳ አይራሩላቸውም። 6ከእንግዲህ በምድሪቱ ለሚኖረው ሕዝብ አልራራምና” ይላል እግዚአብሔር፤ “ሰውን ሁሉ ለባልንጀራውና ለንጉሡ አሳልፌ እሰጣለሁ፤ እነርሱ ምድሪቱን ያስጨንቃሉ፤ እኔም ከእጃቸው አላድናቸውም።”
7ስለዚህ ለዕርድ የተለዩትን በጎች፣ በተለይም የተጨቈኑትን አሰማራሁ። ሁለት በትሮች ወስጄም፣ አንዱን “ሞገስ” ሌላውንም “አንድነት” ብዬ ጠራኋቸው፤ መንጋውንም አሰማራሁ። 8በአንድ ወር ውስጥ ሦስቱን እረኞች አስወገድሁ።
በጎቹ ጠሉኝ፤ እኔም፣ ሰለቸኋቸው፤ 9“እረኛችሁ አልሆንም፤ የሚሞቱት ይሙቱ፤ የሚጠፉት ይጥፉ፤ የቀሩትም አንዱ የሌላውን ሥጋ ይብላ” አልኋቸው።
10ከዚያም ከአሕዛብ ሁሉ ጋር የገባሁትን ኪዳን ለማፍረስ፣ “ሞገስ” ብዬ የጠራሁትን በትሬን ወስጄ ሰበርሁት። 11በዚያም ቀን ኪዳኑ ፈረሰ፤ ሲመለከቱኝ የነበሩትና የተጨነቁት በጎችም የእግዚአብሔር ቃል መሆኑን ዐወቁ።
12እኔም፣ “የሚበጅ መስሎ ከታያችሁ ዋጋዬን ክፈሉኝ፤ አይሆንም ካላችሁም ተዉት” አልኋቸው፤ ስለዚህ ሠላሳ ብር ከፈሉኝ።
13እግዚአብሔርም ሊከፍሉኝ የተስማሙበትን ጥሩ ዋጋ “በግምጃ ቤቱ ውስጥ አኑረው” አለኝ፤ እኔም ሠላሳውን ብር ወስጄ በእግዚአብሔር ቤት ባለው ግምጃ ቤት አስቀመጥሁት። 14ከዚያም የእስራኤልንና የይሁዳን ወንድማማችነት በማፍረስ፣ “አንድነት” ብዬ የጠራሁትን ሁለተኛውን በትሬን ሰበርሁት።
15እግዚአብሔርም እንዲህ አለኝ፤ “እንደ ገና የሰነፍ እረኛ ዕቃ ውሰድ፤ 16እነሆ፤ በምድሪቱ ላይ እረኛ አስነሣለሁ፤ እርሱም የጠፋውን አያስብም፤ የባዘነውን አይፈልግም፤ የተሰበረውን አይጠግንም፤ የዳነውንም አይቀልብም፤ ነገር ግን የሠባውን ሥጋ ይበላል፤ ሰኰናውንም ሳይቀር ይቀለጣጥማል።
17“መንጋውን ለሚተው፣
ለማይረባ እረኛ ወዮለት!
ሰይፍ ክንዱንና ቀኝ ዐይኑን ትውጋው!
ክንዱ ፈጽማ ትስለል!
ቀኝ ዐይኑም ጨርሳ ትታወር!”
1เลบานอนเอ๋ย จงเปิดประตูทั้งหลายของเจ้าเถิด
เพื่อไฟจะได้เผาผลาญเหล่าสนซีดาร์ของเจ้า!
2ต้นสนเอ๋ย จงร่ำไห้เถิด เพราะซีดาร์ถูกโค่นลงแล้ว
ต้นไม้งามตระหง่านนั้นย่อยยับลงแล้ว!
ต้นโอ๊กแห่งบาชานเอ๋ย จงร่ำไห้เถิด
ป่าทึบถูกตัดเตียนแล้ว!
3จงฟังเสียงร่ำไห้ของบรรดาคนเลี้ยงแกะ
ทุ่งหญ้าอันอุดมสมบูรณ์ของพวกเขาถูกทำลายไป!
จงฟังเสียงคำรามของเหล่าสิงห์
ป่าอันเขียวขจีของจอร์แดนถูกทำลายไปแล้ว!
คนเลี้ยงแกะทั้งสอง
4พระยาห์เวห์พระเจ้าของข้าพระองค์ตรัสว่า “จงเลี้ยงฝูงแกะที่จะต้องถูกฆ่า 5ผู้ซื้อฆ่าแกะเหล่านั้นและไม่ถูกลงโทษแต่อย่างใด บรรดาคนขายก็พูดว่า ‘สรรเสริญองค์พระผู้เป็นเจ้า เรารวยแล้ว!’ คนเลี้ยงแกะเองขายมันไปโดยไม่ปรานีฝูงแกะเลย 6เพราะเราจะไม่สงสารชาวแผ่นดินนี้อีกแล้ว” องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศดังนี้ “เราจะมอบทุกคนไว้ในมือเพื่อนบ้านและกษัตริย์ของพวกเขา ซึ่งจะข่มเหงเบียดเบียนแผ่นดินนี้ เราจะไม่ช่วยพวกเขาจากเงื้อมมือของคนเหล่านั้น”
7ดังนั้นข้าพเจ้าจึงเลี้ยงแกะที่จะต้องถูกฆ่า โดยเฉพาะตัวที่ถูกรังแก แล้วข้าพเจ้าเอาไม้เท้าคนเลี้ยงแกะมาสองอัน อันหนึ่งตั้งชื่อว่า “พระคุณ” และอีกอันหนึ่งตั้งชื่อว่า “กลมเกลียว” แล้วข้าพเจ้าก็เลี้ยงดูแกะ 8ภายในเดือนเดียวข้าพเจ้าได้กำจัดคนเลี้ยงแกะทั้งสามคนนั้นออกไป
แต่ข้าพเจ้ากลับเอือมระอาฝูงแกะคือชนชาตินี้ และพวกเขาก็เกลียดชังข้าพเจ้า 9ข้าพเจ้าจึงกล่าวว่า “เราจะไม่เป็นคนเลี้ยงของเจ้าอีกแล้ว ใครจะตายก็ให้ตายไป ใครจะพินาศก็ให้พินาศไป ที่เหลือก็ให้กินเลือดกินเนื้อกันเอง”
10แล้วข้าพเจ้าเอาไม้เท้าที่ชื่อว่า “พระคุณ” มาหักเสีย เป็นการล้มเลิกพันธสัญญาที่ข้าพเจ้าทำไว้กับประชาชาติทั้งปวง 11เป็นอันยกเลิกสัญญาในวันนั้น แล้วผู้ตกทุกข์ได้ยากในฝูงแกะซึ่งมองดูข้าพเจ้าอยู่ ก็รู้ว่าเป็นพระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้า
12ข้าพเจ้ากล่าวกับพวกเขาว่า “หากท่านเห็นชอบ ก็จงจ่ายค่าจ้างให้เรา ถ้าไม่เห็นดี ก็เก็บค่าจ้างนั้นไว้เถิด” ฉะนั้นเขาจึงจ่ายเงินให้ข้าพเจ้าเป็นเงินสามสิบแผ่น
13องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับข้าพเจ้าว่า “จงโยนเงินนี้ให้แก่ช่างปั้นหม้อ คือเงินค่าจ้างอย่างงามที่พวกเขาจ่ายให้” ข้าพเจ้าก็นำเงินสามสิบแผ่นนั้นโยนเข้าไปในพระนิเวศขององค์พระผู้เป็นเจ้าสำหรับช่างปั้นหม้อ
14แล้วข้าพเจ้าหักไม้เท้าอันที่สองซึ่งชื่อว่า “กลมเกลียว” เพื่อแสดงว่ายูดาห์กับอิสราเอลเลิกเป็นพี่น้องกันแล้ว
15แล้วองค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับข้าพเจ้าว่า “จงหยิบเครื่องใช้ของคนเลี้ยงแกะโง่เขลาขึ้นมาอีก 16เพราะเรากำลังจะตั้งคนเลี้ยงขึ้นมาคนหนึ่งสำหรับดินแดนนี้ ซึ่งจะไม่ใส่ใจแกะที่หลงหาย ไม่ดูแลลูกแกะ ไม่รักษาเยียวยาตัวที่บาดเจ็บ หรือเลี้ยงดูตัวที่แข็งแรง แต่จะกินเนื้อแกะตัวที่อ้วนพีและฉีกกีบเท้าของมันออก
17“วิบัติแก่คนเลี้ยงแกะที่ไร้ค่า
ผู้ซึ่งทอดทิ้งฝูงแกะ!
ขอให้ดาบฟันแขนของเขาและตาขวาของเขา!
ขอให้แขนของเขาลีบไป
และให้ตาขวาของเขาบอดสนิท!”