ዘካርያስ 10 – NASV & NIV

New Amharic Standard Version

ዘካርያስ 10:1-12

እግዚአብሔር ለይሁዳ ይጠነቀቃል

1የበልግ ዝናብ እንዲሰጣችሁ እግዚአብሔርን ጠይቁ፤

ማዕበሉን ደመና የሚያደርግ እግዚአብሔር ነው፤

እርሱ ለሰዎች በቂ ዝናብን፣

ለእያንዳንዱም የምድርን ተክል ይሰጣል።

2ተራፊም አሳሳች ነገር ይናገራል፤

ሟርተኞች የሐሰት ራእይ ያያሉ፤

የውሸት ሕልም ይናገራሉ፤

ከንቱ መጽናናት ይሰጣሉ፤

ስለዚህ ሕዝቡ እንደ በጎች ተቅበዘበዙ፤

እረኛ በማጣትም ተጨነቁ።

3“ቍጣዬ በእረኞች ላይ ነድዷል፤

መሪዎችንም እቀጣለሁ፤

እግዚአብሔር ጸባኦት፣

ለመንጋው ለይሁዳ ቤት ይጠነቀቃልና፤

በጦርነትም ጊዜ እንደ ክብሩ ፈረስ ያደርጋቸዋል።

4ከይሁዳ፣ የማእዘን ድንጋይ፣

የድንኳን ካስማ፣

የጦርነት ቀስት፣

ገዥም ሁሉ ይወጣል።

5ጠላትን መንገድ ላይ እንዳለ ጭቃ ይረጋግጣሉ፤

በአንድነት10፥5 ወይም ሁሉም ገዦች በአንድነት ማለት ነው 5 እነርሱም እንደ ጦር ሰልፈኛ ይሆናሉ፤

እግዚአብሔር ከእነርሱ ጋር ስለሆነ ተዋግተው፤

ፈረሰኞችን ያዋርዳሉ።

6“የይሁዳን ቤት አበረታለሁ፤

የዮሴፍንም ቤት እታደጋለሁ።

ስለምራራላቸው፣

ወደ ቦታቸው እመልሳቸዋለሁ፤

እነርሱም በእኔ እንዳልተተዉ ሰዎች

ይሆናሉ፤

እኔ አምላካቸው እግዚአብሔር ነኝና፣

ጸሎታቸውን እሰማለሁ።

7ኤፍሬማውያን እንደ ኀያላን ሰዎች ይሆናሉ፤

ልባቸውም የወይን ጠጅ እንደ ጠጣ ሰው ሐሤት ያደርጋል።

ልጆቻቸው ያዩታል፤ ደስተኛም ይሆናሉ፤

ልባቸውም በእግዚአብሔር ደስ ይለዋል።

8በፉጨት እጠራቸዋለሁ፤

በአንድነት እሰበስባቸዋለሁ፤

በርግጥ እቤዣቸዋለሁ፤

እንደ ቀድሞው ይበዛሉ።

9በሕዝቦች መካከል ብበትናቸውም፣

በሩቅ ምድር ሆነው ያስቡኛል፤

እነርሱና ልጆቻቸው ተርፈው፣

በሕይወት ይመለሳሉ።

10ከግብፅ እመልሳቸዋለሁ፤

ከአሦርም እሰበስባቸዋለሁ፤

ወደ ገለዓድና ወደ ሊባኖስ አመጣቸዋለሁ፤

በቂ ስፍራም አይገኝላቸውም።

11በመከራ ባሕር ውስጥ ያልፋሉ፤

የባሕሩ ማዕበል ጸጥ ይላል፤

የአባይም ጥልቅ ሁሉ ይደርቃል።

የአሦር ትምክሕት ይዋረዳል፤

የግብፅም በትረ መንግሥት ያበቃል።

12በእግዚአብሔር አበረታቸዋለሁ፤

በስሙም ይመላለሳሉ”

ይላል እግዚአብሔር

New International Version

Zechariah 10:1-12

The Lord Will Care for Judah

1Ask the Lord for rain in the springtime;

it is the Lord who sends the thunderstorms.

He gives showers of rain to all people,

and plants of the field to everyone.

2The idols speak deceitfully,

diviners see visions that lie;

they tell dreams that are false,

they give comfort in vain.

Therefore the people wander like sheep

oppressed for lack of a shepherd.

3“My anger burns against the shepherds,

and I will punish the leaders;

for the Lord Almighty will care

for his flock, the people of Judah,

and make them like a proud horse in battle.

4From Judah will come the cornerstone,

from him the tent peg,

from him the battle bow,

from him every ruler.

5Together they10:4,5 Or ruler, all of them together. / 5 They will be like warriors in battle

trampling their enemy into the mud of the streets.

They will fight because the Lord is with them,

and they will put the enemy horsemen to shame.

6“I will strengthen Judah

and save the tribes of Joseph.

I will restore them

because I have compassion on them.

They will be as though

I had not rejected them,

for I am the Lord their God

and I will answer them.

7The Ephraimites will become like warriors,

and their hearts will be glad as with wine.

Their children will see it and be joyful;

their hearts will rejoice in the Lord.

8I will signal for them

and gather them in.

Surely I will redeem them;

they will be as numerous as before.

9Though I scatter them among the peoples,

yet in distant lands they will remember me.

They and their children will survive,

and they will return.

10I will bring them back from Egypt

and gather them from Assyria.

I will bring them to Gilead and Lebanon,

and there will not be room enough for them.

11They will pass through the sea of trouble;

the surging sea will be subdued

and all the depths of the Nile will dry up.

Assyria’s pride will be brought down

and Egypt’s scepter will pass away.

12I will strengthen them in the Lord

and in his name they will live securely,”

declares the Lord.