ዘሌዋውያን 6 – NASV & PCB

New Amharic Standard Version

ዘሌዋውያን 6:1-30

1እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤ 2“ማንኛውም ሰው በዐደራ የተሰጠውን ወይም በመያዣነት የተቀበለውን በመካድና ባልንጀራውን በማጭበርበር ኀጢአት ቢሠራ፣ እግዚአብሔርንም (ያህዌ) ቢበድል ወይም ባልንጀራውን ቢቀማው ወይም ቢያታልለው፣ 3ወይም የጠፋ ነገር አግኝቶ አላየሁም ቢል ወይም በሐሰት ቢምል ወይም ሰዎች የሚያደርጉትን እንዲህ ያለውን ማናቸውንም ኀጢአት ቢሠራ፣ 4በዚህ ሁኔታ ኀጢአት ቢሠራና በደለኛ ቢሆን፣ የሰረቀውን ወይም የቀማውን ወይም በዐደራ የተሰጠውን ወይም ጠፍቶ ያገኘውን ይመልሳል፤ 5በሐሰት የማለበትንም ሁሉ ይመልስ፤ የበደል መሥዋዕቱን በሚያቀርብበት ጊዜ የወሰደውን በሙሉ የዋናውን አንድ አምስተኛ በመጨመር ለባለንብረቱ ንብረቱ ይመልስ። 6ከመንጋውም እንከን የሌለበትን ዋጋው ተመጣጣኝ የሆነ አውራ በግ ስለ በደሉ መሥዋዕት አድርጎ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) ለማቅረብ ወደ ካህኑ ያምጣ፤ 7በዚህም ሁኔታ ካህኑ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ያስተሰርይለታል፤ ሰውየውም ስለ ፈጸመው ስለ ማንኛውም በደል ይቅር ይባላል።”

የሚቃጠል መሥዋዕት

8እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤ 9“አሮንና ልጆቹን እንዲህ ብለህ እዘዛቸው፤ ‘ስለሚቃጠለው መሥዋዕት አቀራረብ የምትከተለው ሥርዐት ይህ ነው፤ የሚቃጠለው መሥዋዕት ሌሊቱን ሁሉ እስኪነጋ ድረስ በመሠዊያው ላይ ባለው ማንደጃ ላይ ይቀመጥ፤ እሳቱም በመሠዊያው ላይ ዘወትር ሲነድድ ይደር። 10ካህኑም ከበፍታ የተሠራ የውስጥ ሱሪውን ካጠለቀ በኋላ፣ የበፍታ ቀሚሱን ይልበስ፤ እሳቱ በመሠዊያው ላይ መሥዋዕቱን ከበላው በኋላ የሚቀረውን ዐመድ አንሥቶ፣ በመሠዊያው አጠገብ ያፍስስ። 11ከዚያም ልብሱን አውልቆ ሌላ ልብስ ይቀይር፤ ዐመዱንም ተሸክሞ ከሰፈር ውጭ በአምልኮው ሥርዐት መሠረት ንጹሕ ወደ ሆነ ስፍራ ይውሰድ። 12በመሠዊያው ላይ ያለው እሳት ዘወትር ይንደድ፤ ምንጊዜም አይጥፋ። ካህኑ ጧት ጧት እሳቱ ላይ ማገዶ ይጨምር፤ በእሳቱ ላይ የሚቃጠለውን መሥዋዕት ያዘጋጅ፤ በዚህም ላይ የኅብረት መሥዋዕቱን6፥12 በትውፊት የሰላም መሥዋዕት ይባላል። ሥብ ያቃጥል። 13በመሠዊያው ላይ ያለው እሳት ዘወትር ይንደድ፤ ምንጊዜም አይጥፋ።

የእህል ቍርባን

14“ ‘የእህል ቍርባን ሥርዐት ይህ ነው፦ የአሮን ልጆች ቍርባኑን በመሠዊያው ትይዩ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ያቅርቡት። 15ካህኑ ከላመው ዱቄትና ከዘይቱ አንድ ዕፍኝ ያንሣለት፤ በእህሉ ቍርባን ላይ ያለውንም ዕጣን በሙሉ ይውሰድ፤ ይህንም፣ ሽታው እግዚአብሔርን (ያህዌ) ደስ የሚያሰኝ መሥዋዕት አድርጎ፣ ለመታሰቢያ በመሠዊያው ላይ ያቃጥለው። 16የተረፈውንም አሮንና ልጆቹ ይብሉት፤ እርሾ ሳይገባበት በተቀደሰው ስፍራ፣ በመገናኛው ድንኳን ቅጥር ግቢ ውስጥ አደባባዩ ላይ ይብሉት። 17ያለ እርሾ መጋገር አለበት፤ በእሳት ከሚቀርብልኝ ቍርባን ይህን የእነርሱ ድርሻ አድርጌ ሰጥቻቸዋለሁ። ይህም፣ እንደ ኀጢአት መሥዋዕትና እንደ በደል መሥዋዕት ሁሉ እጅግ የተቀደሰ ነው። 18ማንኛውም ከአሮን ዘር የተወለደ ወንድ ሊበላው ይችላል፤ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) ከሚቀርበው የእሳት ቍርባን ለእርሱ የተመደበ የዘላለም ድርሻው ነው፤ የሚነካውም ሁሉ6፥18 ወይም የሚነካው ሰው ሁሉ፤ እንዲሁም 27 ይመ ቅዱስ ይሆናል።’ ”

19እግዚአብሔርም (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤ 20“አሮን ወይም ልጆቹ በተቀቡበት ዕለት6፥20 ወይም በተቀባበት ዕለት አሮን እና ልጆቹ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) የሚያቀርቡት ቍርባን ይህ ነው፦ የኢፍ6፥20 ሁለት ሊትር ገደማ ይሆናል አንድ ዐሥረኛው የላመ ዱቄት ግማሹን ለጧት፣ ግማሹን ለማታ የዘወትር የእህል ቍርባን አድርገው ያቅርቡት። 21በሚገባ በዘይት ተለውሶ በምጣድ ላይ ይጋገር፤ ከዚያም የእህሉን ቍርባን ቈራርሰህ6፥21 የዚህ ቃል የዕብራይስጡ ትርጓሜ በርግጠኝነት አይታወቅም ሽታው እግዚአብሔርን (ያህዌ) ደስ የሚያሰኝ ይሆን ዘንድ አቅርብ። 22በእርሱ ቦታ ተቀብቶ ካህን የሚሆነው ልጁ ይህን ያዘጋጅ፤ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) የተመደበ ድርሻ ነውና ፈጽሞ ይቃጠል። 23ካህኑ የሚያቀርበው የእህል ቍርባን ሁሉ ፈጽሞ ይቃጠል እንጂ አይበላ።”

የኀጢአት መሥዋዕት

24እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤ 25“አሮንንና ልጆቹን እንዲህ በላቸው፤ ‘ስለ ኀጢአት መሥዋዕት አቀራረብ የምትከተለው ሥርዐት ይህ ነው፤ የሚቃጠል መሥዋዕት በሚታረድበት ስፍራ የኀጢአቱም መሥዋዕት እዚያው በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ይታረድ፤ ይህም እጅግ ቅዱስ ነው። 26መሥዋዕቱንም የሚያቀርበው ካህን ይብላው፤ ይህም በተቀደሰው ስፍራ በመገናኛው ድንኳን ቅጥር ግቢ ውስጥ፣ በአደባባዩ ላይ ይበላ። 27ሥጋውን የሚነካ ሁሉ የተቀደሰ ይሆናል፤ ደሙ በልብስ ላይ ቢረጭ፣ ያን ልብስ በተቀደሰ ስፍራ ዕጠብ። 28ሥጋው የተቀቀለበት የሸክላ ዕቃ ይሰበር፤ የናስ ዕቃ ከሆነ ግን ተፈግፍጎ በውሃ ይታጠብ። 29ከካህናት ወገን የሆነ ወንድ ሁሉ ከዚህ መብላት ይችላል፤ ይህም እጅግ ቅዱስ ነው። 30ነገር ግን ደሙ ማስተስረያ እንዲሆን ወደ መገናኛው ድንኳን ወደ ቅድስት የቀረበው የኀጢአት መሥዋዕት ሁሉ በእሳት ይቃጠል እንጂ አይበላ።

Persian Contemporary Bible

لاويان 6:1‏-30

1‏-3خداوند اين دستورات را به موسی داد: هرگاه كسی نسبت به من گناه كرده، از پس دادن چيزی كه پيش او گرو گذاشته شده خودداری نمايد يا در امانت خيانت ورزد، يا دزدی كند يا مال همسايه‌اش را غصب نمايد، و يا اينكه دربارهٔ چيز گمشده‌ای كه پيدا كرده است دروغ بگويد و قسم بخورد كه پيش او نيست، 4‏-5روزی كه جرم او ثابت شود بايد اصل مال را پس دهد و يک پنجم ارزش آن را نيز به آن افزوده، به صاحب مال بپردازد. 6او بايد قربانی جبران را كه يک قوچ سالم و بی‌عيب است نزد كاهن به خيمهٔ عبادت بياورد و به خداوند تقديم كند. قوچ بايد مطابق معيار رسمی، ارزيابی شود. 7كاهن با اين قربانی برای او در حضور خداوند كفاره خواهد كرد و گناه او بخشيده خواهد شد.

مقررات قربانی سوختنی

8‏-9آنگاه خداوند به موسی فرمود كه در مورد قربانی سوختنی اين مقررات را به هارون و پسرانش بدهد: قربانی سوختنی بايد تمام شب بر قربانگاه باشد و آتش قربانگاه خاموش نشود. 10صبح روز بعد، كاهن لباس زير و لباس كتانی خود را بپوشد و خاكستر قربانی سوختنی را برداشته، كنار قربانگاه بگذارد. 11سپس لباسش را عوض كند و خاكستر را بيرون اردوگاه ببرد و در مكان طاهری كه برای اين كار مقرر شده است، بريزد. 12‏-13كاهن هر روز صبح هيزم تازه بر آن بنهد و قربانی سوختنی روزانه را روی آن بگذارد و پيه قربانی سلامتی را بر آن بسوزاند. آتش قربانگاه بايد هميشه روشن بماند و خاموش نشود.

مقررات هديهٔ آردی

14مقررات مربوط به هديهٔ آردی از اين قرار است: كاهن برای تقديم هديهٔ آردی به خداوند جلو قربانگاه بايستد، 15سپس مشتی از آرد مرغوب آغشته به روغن زيتون را با كندری كه بر آن است بردارد و به عنوان نمونه برای خداوند روی قربانگاه بسوزاند. اين هديه مورد پسند خداوند خواهد بود. 16‏-17بقيهٔ آرد، متعلق به كاهنان می‌باشد تا از آن برای خوراک خود استفاده كنند. اين آرد بايد بدون خميرمايه پخته شود و در حياط عبادتگاه كه مكان مقدسی است خورده شود. اين قسمت از هديهٔ آردی را كه بر آتش به خداوند تقديم می‌شود، خداوند به كاهنان داده است. مانند قربانی گناه و قربانی جبران، اين قسمت از هديهٔ آردی نيز بسيار مقدس می‌باشد. 18پسران هارون نسل اندر نسل می‌توانند اين قسمت از هديه را بخورند. اين هديه كه بر آتش به خداوند تقديم می‌شود، هميشه سهم كاهنان خواهد بود و كس ديگری حق ندارد به آن دست بزند.

19‏-20خداوند همچنين اين دستورات را به موسی داد: هارون و هر كدام از پسرانش در روزی كه برای مقام كاهنی انتصاب می‌شوند بايد يک كيلو آرد مرغوب، به اندازهٔ هديهٔ آردی روزانه به حضور خداوند بياورند و نصف آن را در صبح و نصف ديگر را در عصر به خداوند تقديم كنند. 21اين هديه بايد روی ساج با روغن زيتون پخته شود سپس تكه‌تكه شده، به عنوان هديهٔ آردی به خداوند تقديم گردد. اين هديه مورد پسند خداوند خواهد بود. 22‏-23هر كاهنی كه به جای پدر خود، كاهن اعظم می‌شود بايد در روز انتصاب خود همين هديه را تقديم كند. اين فريضه‌ای ابدی است. اين هديه بايد تماماً در حضور خداوند سوزانده شود و چيزی از آن خورده نشود.

مقررات قربانی گناه

24‏-25خداوند به موسی فرمود كه در مورد قربانی گناه اين مقررات را به هارون و پسرانش بدهد: اين قربانی بسيار مقدس است و بايد در حضور خداوند در جايی ذبح شود كه قربانیهای سوختنی را سر می‌برند. 26كاهنی كه قربانی را تقديم می‌كند، گوشت آن را در حياط عبادتگاه كه جای مقدسی است، بخورد. 27فقط كسانی كه تقديس شده‌اند، يعنی كاهنان، اجازه دارند به اين گوشت دست بزنند. اگر خون آن قربانی به لباس ايشان بپاشد بايد لباس خود را در مكانی مقدس بشويند. 28ظرف سفالينی كه گوشت در آن پخته می‌شود بايد شكسته شود. اگر گوشت در يک ظرف مسی پخته شده باشد بايد آن ظرف را كاملاً تميز كنند و با آب بشويند. 29اولاد ذكور كاهنان می‌توانند از اين گوشت بخورند. اين قربانی بسيار مقدس است. 30اما در مواردی كه خون قربانی گناه برای كفاره در قدس به داخل خيمهٔ عبادت برده می‌شود، گوشت قربانی را نبايد خورد بلكه بايد تماماً سوزاند.