ዘሌዋውያን 6 – NASV & NUB

New Amharic Standard Version

ዘሌዋውያን 6:1-30

1እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤ 2“ማንኛውም ሰው በዐደራ የተሰጠውን ወይም በመያዣነት የተቀበለውን በመካድና ባልንጀራውን በማጭበርበር ኀጢአት ቢሠራ፣ እግዚአብሔርንም (ያህዌ) ቢበድል ወይም ባልንጀራውን ቢቀማው ወይም ቢያታልለው፣ 3ወይም የጠፋ ነገር አግኝቶ አላየሁም ቢል ወይም በሐሰት ቢምል ወይም ሰዎች የሚያደርጉትን እንዲህ ያለውን ማናቸውንም ኀጢአት ቢሠራ፣ 4በዚህ ሁኔታ ኀጢአት ቢሠራና በደለኛ ቢሆን፣ የሰረቀውን ወይም የቀማውን ወይም በዐደራ የተሰጠውን ወይም ጠፍቶ ያገኘውን ይመልሳል፤ 5በሐሰት የማለበትንም ሁሉ ይመልስ፤ የበደል መሥዋዕቱን በሚያቀርብበት ጊዜ የወሰደውን በሙሉ የዋናውን አንድ አምስተኛ በመጨመር ለባለንብረቱ ንብረቱ ይመልስ። 6ከመንጋውም እንከን የሌለበትን ዋጋው ተመጣጣኝ የሆነ አውራ በግ ስለ በደሉ መሥዋዕት አድርጎ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) ለማቅረብ ወደ ካህኑ ያምጣ፤ 7በዚህም ሁኔታ ካህኑ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ያስተሰርይለታል፤ ሰውየውም ስለ ፈጸመው ስለ ማንኛውም በደል ይቅር ይባላል።”

የሚቃጠል መሥዋዕት

8እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤ 9“አሮንና ልጆቹን እንዲህ ብለህ እዘዛቸው፤ ‘ስለሚቃጠለው መሥዋዕት አቀራረብ የምትከተለው ሥርዐት ይህ ነው፤ የሚቃጠለው መሥዋዕት ሌሊቱን ሁሉ እስኪነጋ ድረስ በመሠዊያው ላይ ባለው ማንደጃ ላይ ይቀመጥ፤ እሳቱም በመሠዊያው ላይ ዘወትር ሲነድድ ይደር። 10ካህኑም ከበፍታ የተሠራ የውስጥ ሱሪውን ካጠለቀ በኋላ፣ የበፍታ ቀሚሱን ይልበስ፤ እሳቱ በመሠዊያው ላይ መሥዋዕቱን ከበላው በኋላ የሚቀረውን ዐመድ አንሥቶ፣ በመሠዊያው አጠገብ ያፍስስ። 11ከዚያም ልብሱን አውልቆ ሌላ ልብስ ይቀይር፤ ዐመዱንም ተሸክሞ ከሰፈር ውጭ በአምልኮው ሥርዐት መሠረት ንጹሕ ወደ ሆነ ስፍራ ይውሰድ። 12በመሠዊያው ላይ ያለው እሳት ዘወትር ይንደድ፤ ምንጊዜም አይጥፋ። ካህኑ ጧት ጧት እሳቱ ላይ ማገዶ ይጨምር፤ በእሳቱ ላይ የሚቃጠለውን መሥዋዕት ያዘጋጅ፤ በዚህም ላይ የኅብረት መሥዋዕቱን6፥12 በትውፊት የሰላም መሥዋዕት ይባላል። ሥብ ያቃጥል። 13በመሠዊያው ላይ ያለው እሳት ዘወትር ይንደድ፤ ምንጊዜም አይጥፋ።

የእህል ቍርባን

14“ ‘የእህል ቍርባን ሥርዐት ይህ ነው፦ የአሮን ልጆች ቍርባኑን በመሠዊያው ትይዩ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ያቅርቡት። 15ካህኑ ከላመው ዱቄትና ከዘይቱ አንድ ዕፍኝ ያንሣለት፤ በእህሉ ቍርባን ላይ ያለውንም ዕጣን በሙሉ ይውሰድ፤ ይህንም፣ ሽታው እግዚአብሔርን (ያህዌ) ደስ የሚያሰኝ መሥዋዕት አድርጎ፣ ለመታሰቢያ በመሠዊያው ላይ ያቃጥለው። 16የተረፈውንም አሮንና ልጆቹ ይብሉት፤ እርሾ ሳይገባበት በተቀደሰው ስፍራ፣ በመገናኛው ድንኳን ቅጥር ግቢ ውስጥ አደባባዩ ላይ ይብሉት። 17ያለ እርሾ መጋገር አለበት፤ በእሳት ከሚቀርብልኝ ቍርባን ይህን የእነርሱ ድርሻ አድርጌ ሰጥቻቸዋለሁ። ይህም፣ እንደ ኀጢአት መሥዋዕትና እንደ በደል መሥዋዕት ሁሉ እጅግ የተቀደሰ ነው። 18ማንኛውም ከአሮን ዘር የተወለደ ወንድ ሊበላው ይችላል፤ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) ከሚቀርበው የእሳት ቍርባን ለእርሱ የተመደበ የዘላለም ድርሻው ነው፤ የሚነካውም ሁሉ6፥18 ወይም የሚነካው ሰው ሁሉ፤ እንዲሁም 27 ይመ ቅዱስ ይሆናል።’ ”

19እግዚአብሔርም (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤ 20“አሮን ወይም ልጆቹ በተቀቡበት ዕለት6፥20 ወይም በተቀባበት ዕለት አሮን እና ልጆቹ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) የሚያቀርቡት ቍርባን ይህ ነው፦ የኢፍ6፥20 ሁለት ሊትር ገደማ ይሆናል አንድ ዐሥረኛው የላመ ዱቄት ግማሹን ለጧት፣ ግማሹን ለማታ የዘወትር የእህል ቍርባን አድርገው ያቅርቡት። 21በሚገባ በዘይት ተለውሶ በምጣድ ላይ ይጋገር፤ ከዚያም የእህሉን ቍርባን ቈራርሰህ6፥21 የዚህ ቃል የዕብራይስጡ ትርጓሜ በርግጠኝነት አይታወቅም ሽታው እግዚአብሔርን (ያህዌ) ደስ የሚያሰኝ ይሆን ዘንድ አቅርብ። 22በእርሱ ቦታ ተቀብቶ ካህን የሚሆነው ልጁ ይህን ያዘጋጅ፤ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) የተመደበ ድርሻ ነውና ፈጽሞ ይቃጠል። 23ካህኑ የሚያቀርበው የእህል ቍርባን ሁሉ ፈጽሞ ይቃጠል እንጂ አይበላ።”

የኀጢአት መሥዋዕት

24እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤ 25“አሮንንና ልጆቹን እንዲህ በላቸው፤ ‘ስለ ኀጢአት መሥዋዕት አቀራረብ የምትከተለው ሥርዐት ይህ ነው፤ የሚቃጠል መሥዋዕት በሚታረድበት ስፍራ የኀጢአቱም መሥዋዕት እዚያው በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ይታረድ፤ ይህም እጅግ ቅዱስ ነው። 26መሥዋዕቱንም የሚያቀርበው ካህን ይብላው፤ ይህም በተቀደሰው ስፍራ በመገናኛው ድንኳን ቅጥር ግቢ ውስጥ፣ በአደባባዩ ላይ ይበላ። 27ሥጋውን የሚነካ ሁሉ የተቀደሰ ይሆናል፤ ደሙ በልብስ ላይ ቢረጭ፣ ያን ልብስ በተቀደሰ ስፍራ ዕጠብ። 28ሥጋው የተቀቀለበት የሸክላ ዕቃ ይሰበር፤ የናስ ዕቃ ከሆነ ግን ተፈግፍጎ በውሃ ይታጠብ። 29ከካህናት ወገን የሆነ ወንድ ሁሉ ከዚህ መብላት ይችላል፤ ይህም እጅግ ቅዱስ ነው። 30ነገር ግን ደሙ ማስተስረያ እንዲሆን ወደ መገናኛው ድንኳን ወደ ቅድስት የቀረበው የኀጢአት መሥዋዕት ሁሉ በእሳት ይቃጠል እንጂ አይበላ።

Swedish Contemporary Bible

3 Moseboken 6:1-30

1Herren talade till Mose: 2”Om någon syndar och handlar trolöst mot Herren så att han bedrar sin nästa i fråga om något som anförtrotts åt honom eller överlämnats i hans omvårdnad eller om han stjäl eller lurar till sig något 3eller om han hittat något som andra har tappat men ljuger om det eller om han svär falskt om vilken synd som helst som en människa kan begå, 4ska han som syndat och gjort sig skyldig återlämna det han stulit eller tvingat till sig eller som anförtrotts honom eller som han hittat 5eller som han svurit falskt om. Han ska ersätta det till dess fulla värde plus tjugo procent. Samma dag ska han skaffa fram sitt skuldoffer. 6Skuldoffret ska bestå av en felfri bagge som han tar från småboskapen eller dess bestämda värde. Han ska föra den fram till prästen inför Herren. 7Prästen ska skaffa försoning åt honom inför Herren och han ska då få förlåtelse för vad det än är han gjort sig skyldig till.”

Att offra brännoffer

8Sedan talade Herren till Mose: 9”Ge Aron och hans söner denna befallning beträffande lagen om brännoffer: ’Brännoffret ska ligga kvar på altarets härd hela natten till morgonen och elden ska hållas vid liv. 10Prästen ska ta på sig sina kläder och underkläder av linne, ta bort askan som finns kvar efter brännoffret och lägga den vid sidan av altaret. 11Sedan ska han byta kläder och bära askan utanför lägret till en ren plats. 12Elden på altaret ska hållas brinnande. Den får inte slockna. Prästen ska lägga på färsk ved varje morgon, placera brännoffret ovanpå den och bränna fettet från gemenskapsoffret. 13Elden på altaret måste ständigt hållas brinnande. Den får aldrig slockna.

Att offra matoffer

14Det här är lagen om matoffret:

Arons söner ska bära fram det till altaret inför Herren. 15Den av Arons söner som blir smord till präst i hans ställe ska sedan ta en handfull av det fint malda mjölet med den inblandade oljan och all rökelsen som ligger på matoffret och bränna detta påminnelseoffer på altaret som en välbehaglig lukt inför Herren. 16Sedan ska resten tillfalla Aron och hans söner till mat. Det ska ätas osyrat på en helig plats på uppenbarelsetältets förgård. 17Det måste bakas utan surdeg. Jag har gett prästerna denna del av eldoffren som gjorts i ordning åt mig. Det är högheligt precis som syndoffret och skuldoffret. 18Det får ätas av manliga ättlingar till Aron i kommande generationer som deras del av Herrens eldoffer. Allt som rör vid detta blir heligt.’ ”

19Herren talade till Mose: 20”På den dag när Aron och hans söner blir smorda till och avskilda för sin uppgift som präster, ska de bära fram ett matoffer till Herren av tre och en halv liter fint mjöl. Hälften ska offras på morgonen och hälften på kvällen. 21Det ska tillagas på en plåt, man ska använda olja, det ska blandas väl och sedan bäras fram brutet i bitar som ett matoffer till Herren, som en välbehaglig lukt inför Herren. 22När prästernas söner ersätter sina fäder, ska de tillreda det när de blir smorda. Detta är en evig ordning. Dessa offer ska brännas upp helt inför Herren. 23Prästens matoffer är ett heloffer. Ingenting av det får ätas.”

Att offra syndoffer

24Sedan talade Herren till Mose: 25”Säg till Aron och hans söner att det här är lagen angående syndoffer: ’Dessa syndoffer är högheliga och ska slaktas inför Herren på den plats där brännofferdjuren slaktas. 26Prästen som offrar syndoffret ska äta det på en helig plats i förgården till uppenbarelsetältet. 27Allt som kommer i beröring med detta kött blir heligt. Om något av blodet kommer på ett klädesplagg, måste det tvättas på en helig plats. 28Lerkrukan som köttet kokats i måste slås sönder. Om det är ett kopparkärl som använts, ska det skuras och sköljas med vatten. 29Alla manliga medlemmar av prästsläkten får äta av detta offer för det är högheligt. 30Men man får inte äta syndoffret vars blod tagits in i tältet för att skaffa försoning i helgedomen. Det ska brännas upp.