ዘሌዋውያን 4 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዘሌዋውያን 4:1-35

የኀጢአት መሥዋዕት

1እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ ሲል ተናገረው፤ 2“ለእስራኤል ሕዝብ እንዲህ በላቸው፤ ‘ማንም ሰው ባለማወቅ ኀጢአት ቢሠራ፣ እግዚአብሔር (ያህዌ) አታድርጉ ብሎ ካዘዛቸውም አንዱን ተላልፎ ቢገኝ፣

3“ ‘የተቀባውም ካህን በሕዝቡ ላይ በደል የሚያስከትል ኀጢአት ቢሠራ፣ ስለ ሠራው ኀጢአት እንከን የሌለበት አንድ ወይፈን ለእግዚአብሔር (ያህዌ) የኀጢአት መሥዋዕት አድርጎ ያቅርብ። 4ወይፈኑን በመገናኛው ድንኳን ደጃፍ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ያቅርብ፤ እጁንም በወይፈኑ ራስ ላይ ይጫን፤ በእግዚአብሔርም (ያህዌ) ፊት ይረደው። 5የተቀባው ካህን ከወይፈኑ ደም ጥቂት ወስዶ ወደ መገናኛው ድንኳን ይግባ፤ 6ጣቱንም በደሙ ውስጥ ነክሮ ከመቅደሱ መጋረጃ ትይዩ፣ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ሰባት ጊዜ ይርጨው። 7ካህኑ ከደሙ ጥቂት ወስዶ በመገናኛው ድንኳን ውስጥ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ያለውንና ሽታው ጣፋጭ የሆነ ዕጣን የሚታጠንበትን መሠዊያ ቀንዶች ይቅባ። የተረፈውን የወይፈኑን ደም ሁሉ በመገናኛው ድንኳን መግቢያ ላይ ባለው በሚቃጠል መሥዋዕት መሠዊያ ግርጌ ያፍስሰው። 8ለኀጢአት መሥዋዕት ከሚቀርበው ወይፈን ሥቡን ሁሉ ያውጣ፤ ይኸውም፦ የሆድ ዕቃውን የሚሸፍነውን ሥብና ከሆድ ዕቃው ጋር የተያያዘውን ሥብ፣ 9ሁለቱንም ኵላሊቶች፣ በኵላሊቶቹ ላይና በጐድኑ አጠገብ ያለውን ሥብ እንዲሁም የጕበቱን መሸፈኛ ከኵላሊቶቹ ጋር አብሮ አውጥቶ ያቅርብ፤ 10ለኅብረት መሥዋዕት4፥10 በትውፊት የሰላም መሥዋዕት ይባላል፤ እንዲሁም 26፡31፡35 ይመ፤ ከሚቀርበው ወይፈን4፥10 የዕብራይስጡ ቃል ተባዕትንና እንስትን ሊያጠቃልል ይችላል። እንዳወጣ ሁሉ ሥቡን ያውጣ፤ ካህኑም የሚቃጠል መሥዋዕት በሚቀርብበት መሠዊያ ላይ ያቃጥለው። 11ነገር ግን የወይፈኑን ቈዳና ሥጋውን ሁሉ፣ ጭንቅላቱንና እግሮቹን፣ ሆድ ዕቃውንና ፈርሱን፣ 12የወይፈኑን ብልት ሁሉ ከሰፈር ውጭ ዐመድ ወደሚፈስስበት በአምልኮው ሥርዐት መሠረት ንጹሕ ወደ ሆነው ስፍራ ይውሰደው፤ በተቈለለው ዐመድ ላይ ዕንጨት አንድዶ ያቃጥለው።

13“ ‘መላው የእስራኤል ሕዝብ ባለማወቅ ኀጢአት ቢሠራ፣ አታድርጉ ብሎ እግዚአብሔር (ያህዌ) ካዘዘውም አንዱን ተላልፎ ቢገኝ፣ ይህ ሕዝብ ጥፋቱ ባይታወቀውም በደለኛ ነው። 14የሕዝቡ ጉባኤ ኀጢአት መሥራቱን በተረዳ ጊዜ፣ ለኀጢአት መሥዋዕት የሚሆን አንድ ወይፈን በመገናኛው ድንኳን ፊት ያቅርብ። 15የሕዝቡም ሽማግሌዎች በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት እጆቻቸውን በወይፈኑ ራስ ላይ ይጫኑ፤ ወይፈኑም በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ይታረድ። 16የተቀባውም ካህን ከወይፈኑ ደም ጥቂት ወስዶ ወደ መገናኛው ድንኳን ይግባ። 17ጣቱን በደሙ ውስጥ ነክሮ፣ በመጋረጃው ትይዩ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ሰባት ጊዜ ይርጨው። 18ከደሙ ጥቂት ወስዶ በመገናኛው ድንኳን ውስጥ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ያለውን የመሠዊያ ቀንዶች ይቅባ፤ የተረፈውን ደም ሁሉ በመገናኛው ድንኳን መግቢያ ላይ ባለው በሚቃጠል መሥዋዕት መሠዊያ ግርጌ ያፍስሰው። 19ከወይፈኑም ሥቡን ሁሉ ወስዶ በመሠዊያው ላይ ያቃጥል፤ 20ለኀጢአት መሥዋዕት ባቀረበው ወይፈን ላይ እንዳደረገው ሁሉ፣ በዚህኛውም ወይፈን ያድርግ፤ በዚህም መሠረት ካህኑ ስለ ሕዝቡ ያስተሰርያል፤ እነርሱም ይቅር ይባላሉ። 21ወይፈኑንም ከሰፈር ውጭ ያውጣው፤ የመጀመሪያውን ወይፈን እንዳቃጠለው ሁሉ ይህኛውንም ያቃጥል፤ ይህም ስለ ሕዝቡ የሚቀርብ የኀጢአት መሥዋዕት ነው።

22“ ‘አንድ የሕዝብ መሪ ባለማወቅ ኀጢአት ቢሠራ፣ አምላኩም እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) አታድርጉ ብሎ ከከለከላቸው ትእዛዞች አንዱን ተላልፎ ቢገኝ፣ እርሱ በደለኛ ነው። 23ኀጢአት መሥራቱን በተረዳ ጊዜ እንከን የሌለበትን ተባዕት ፍየል የግሉ መሥዋዕት አድርጎ ያቅርብ። 24እጁንም በፍየሉ ራስ ላይ ይጫን፤ የሚቃጠል መሥዋዕት በሚታረድበትም ስፍራ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ይረደው፤ ይህም የኀጢአት መሥዋዕት ነው። 25ካህኑም ከመሥዋዕቱ ደም በጣቱ ጥቂት ወስዶ የሚቃጠል መሥዋዕት የሚቀርብበትን መሠዊያ ቀንዶች ይቅባ፤ የተረፈውንም ደም ሁሉ በመሠዊያው ግርጌ ያፍስሰው። 26የኅብረት መሥዋዕቱን እንዳቃጠለ ሁሉ ሥቡንም በሙሉ በመሠዊያው ላይ ያቃጥል፤ በዚህም መሠረት ካህኑ የሰውየውን ኀጢአት ያስተሰርይለታል፤ ሰውየውም ይቅር ይባላል።

27“ ‘ከሕዝቡ መካከል አንዱ ሰው ባለማወቅ ኀጢአት ቢሠራ፣ እግዚአብሔር (ያህዌ) አታድርጉ ብሎ ከከለከላቸው ትእዛዞች አንዱን ተላልፎ ቢገኝ እርሱ በደለኛ ነው። 28ኀጢአት መሥራቱን በተረዳ ጊዜ፣ እንከን የሌለባትን እንስት ፍየል ስለ ፈጸመው ኀጢአት የግሉ መሥዋዕት አድርጎ ያቅርብ። 29እጁን ለኀጢአት መሥዋዕት በቀረበችው ፍየል ራስ ላይ ይጫን፤ የሚቃጠል መሥዋዕት በሚታረድበት ስፍራም ይረዳት። 30ካህኑ በጣቱ ከደሟ ጥቂት ወስዶ የሚቃጠል መሥዋዕት የሚቀርብበትን መሠዊያ ቀንዶች ይቅባ፤ የተረፈውንም ደም ሁሉ በመሠዊያው ግርጌ ያፍስሰው። 31ሥቡን ከኅብረት መሥዋዕት በወጣበት አኳኋን ሥቡን ሁሉ ያውጣ፤ ካህኑም ሽታው እግዚአብሔርን (ያህዌ) ደስ የሚያሰኝ መሥዋዕት አድርጎ በመሠዊያው ላይ ያቃጥለው፤ በዚህም መሠረት ካህኑ የሰውየውን ኀጢአት ያስተሰርይለታል፤ ሰውየውም ይቅር ይባላል።

32“ ‘ስለ ኀጢአት መሥዋዕት የበግ ጠቦት የሚያቀርብ ከሆነ፣ እንከን የሌለባትን እንስት ያቅርብ። 33እጁን በጠቦቷ ራስ ላይ ይጫን፤ የሚቃጠል መሥዋዕት በሚታረድበት ስፍራም የኀጢአት መሥዋዕት አድርጎ ይረዳት። 34ካህኑም ከኀጢአት መሥዋዕቱ ደም በጣቱ ጥቂት ወስዶ የሚቃጠል መሥዋዕት የሚቀርብበትን መሠዊያ ቀንዶች ይቅባ፤ የተረፈውንም ደም ሁሉ በመሠዊያ ግርጌ ያፍስሰው። 35ሥቡ ከኅብረት መሥዋዕት ጠቦት በወጣበት አኳኋን ሥቡን ሁሉ ያውጣ፤ ካህኑም በመሠዊያው ላይ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) በእሳት በሚቀርበው መሥዋዕት ላይ ያቃጥለው። በዚህ መሠረት ሰውየው የሠራውን ኀጢአት ካህኑ ያስተሰርይለታል፤ ሰውየውም ይቅር ይባላል።

Thai New Contemporary Bible

เลวีนิติ 4:1-35

เครื่องบูชาไถ่บาป

1องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับโมเสสว่า 2“จงแจ้งชนอิสราเอลว่า ‘เมื่อผู้หนึ่งผู้ใดทำบาปโดยไม่เจตนาและทำสิ่งใดๆ ซึ่งองค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสห้าม

3“ ‘หากปุโรหิตผู้ได้รับการเจิมตั้งไว้ได้ทำบาป นำความผิดมาสู่ประชากร เขาจะต้องถวายวัวหนุ่มไม่มีตำหนิแด่องค์พระผู้เป็นเจ้า เพื่อเป็นเครื่องบูชาไถ่บาปสำหรับบาปที่เขาได้ทำ 4ให้เขานำวัวมาตรงทางเข้าเต็นท์นัดพบต่อหน้าองค์พระผู้เป็นเจ้า เขาจะต้องวางมือบนหัววัวและฆ่าวัวนั้นต่อหน้าองค์พระผู้เป็นเจ้า 5แล้วปุโรหิตผู้รับการเจิมตั้งจะนำเลือดของวัวเข้าไปในเต็นท์นัดพบ 6เอานิ้วจุ่มเลือดและพรมที่หน้าม่านของสถานนมัสการต่อหน้าองค์พระผู้เป็นเจ้าเจ็ดครั้ง 7ปุโรหิตจะเอาเลือดบางส่วนทาเชิงงอนของแท่นเผาเครื่องหอมต่อหน้าองค์พระผู้เป็นเจ้าในเต็นท์นัดพบ เลือดที่เหลือของวัวผู้จะเทลงที่ด้านล่างของแท่นเผาเครื่องบูชาตรงทางเข้าเต็นท์นัดพบ 8เขาจะเอาไขมันทั้งหมดของวัวผู้ที่เป็นเครื่องบูชาไถ่บาปออกมา คือไขมันที่หุ้มหรือติดกับเครื่องใน 9ไตสองลูกกับไขมันบนไตใกล้บั้นเอว และพังผืดหุ้มตับซึ่งเอาออกมาพร้อมไต 10เช่นเดียวกับไขมันซึ่งนำออกจากวัว4:10 ในภาษาฮีบรูคำนี้เป็นได้ทั้งตัวผู้และตัวเมียที่ถวายเป็นเครื่องสันติบูชา แล้วปุโรหิตจะเผาสิ่งเหล่านี้บนแท่นบูชา 11แต่หนัง เนื้อ หัว ขา เครื่องในและไส้ 12คือส่วนที่เหลือของวัวตัวนี้ เขาต้องนำไปยังที่ซึ่งไม่เป็นมลทินตามระเบียบพิธีนอกค่ายพักแรมซึ่งเป็นที่ทิ้งเถ้า แล้วเผาส่วนทั้งหมดในกองฟืนบนกองขี้เถ้า

13“ ‘หากชุมชนอิสราเอลทั้งหมดทำบาปโดยไม่เจตนาและทำสิ่งที่องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสห้าม แม้จะรู้เท่าไม่ถึงการณ์ ทุกคนก็มีความผิด 14เมื่อพวกเขาตระหนักถึงบาปที่ได้ทำ เหล่าประชากรจะต้องนำวัวหนุ่มตัวหนึ่งมายังเต็นท์นัดพบเพื่อถวายเป็นเครื่องบูชาไถ่บาป 15บรรดาผู้อาวุโสของชุมชนจะวางมือบนหัววัวผู้และฆ่าวัวนั้นต่อหน้าองค์พระผู้เป็นเจ้า 16จากนั้นปุโรหิตผู้รับการเจิมตั้งจะนำเลือดส่วนหนึ่งเข้าไปในเต็นท์นัดพบ 17เอานิ้วจุ่มเลือดและพรมที่หน้าม่านเจ็ดครั้งต่อหน้าองค์พระผู้เป็นเจ้า 18แล้วเอาเลือดส่วนหนึ่งทาเชิงงอนของแท่นซึ่งอยู่ต่อหน้าองค์พระผู้เป็นเจ้าในเต็นท์นัดพบ เขาจะเทเลือดส่วนที่เหลือลงที่ด้านล่างของแท่นบูชาตรงทางเข้าเต็นท์นัดพบ 19เขาจะเอาไขมันทั้งหมดออกมาเผาบนแท่นบูชา 20เขาจะทำกับวัวตัวนี้เช่นเดียวกับที่ทำกับวัวที่ใช้เป็นเครื่องบูชาไถ่บาป ปุโรหิตจะลบบาปให้ประชากรโดยวิธีนี้ และพวกเขาจะได้รับการอภัย 21แล้วเขาจะนำวัวผู้ตัวนี้ออกไปเผานอกค่ายเหมือนกับที่เผาวัวตัวแรกนั้น นี่เป็นเครื่องบูชาไถ่บาปสำหรับชุมชนทั้งหมด

22“ ‘หากผู้นำคนใดทำบาปโดยไม่เจตนาและทำสิ่งที่พระยาห์เวห์พระเจ้าของเขาตรัสห้าม เขาก็มีความผิด 23เมื่อเขาได้ตระหนักถึงบาปที่ได้ทำไป เขาต้องนำแพะตัวผู้ที่ไม่มีตำหนิมาถวายเป็นเครื่องบูชา 24ให้เขาวางมือบนหัวแพะและฆ่าในที่สำหรับฆ่าสัตว์ซึ่งเป็นเครื่องเผาบูชาต่อหน้าองค์พระผู้เป็นเจ้า นี่คือเครื่องบูชาไถ่บาป 25จากนั้นปุโรหิตจะเอานิ้วจุ่มในเลือดของเครื่องบูชาไถ่บาปและทาเชิงงอนของแท่นบูชา แล้วเทเลือดส่วนที่เหลือลงที่ด้านล่างของแท่น 26เขาจะเผาไขมันทุกส่วนบนแท่นบูชาเหมือนกับเผาไขมันของเครื่องสันติบูชา ปุโรหิตจะลบบาปของผู้นำคนนั้นโดยวิธีนี้ และเขาจะได้รับการอภัย

27“ ‘หากผู้ใดในชุมชนทำบาปโดยไม่เจตนาและทำสิ่งที่องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสห้าม เขาก็มีความผิด 28เมื่อเขาได้ตระหนักถึงบาปที่ได้ทำไป เขาต้องนำแพะตัวเมียไม่มีตำหนิมาถวายเพื่อขอไถ่บาปที่ได้ทำ 29เขาจะวางมือบนหัวเครื่องบูชาไถ่บาปและฆ่ามันในที่สำหรับฆ่าเครื่องเผาบูชา 30แล้วปุโรหิตจะเอานิ้วจุ่มเลือดทาเชิงงอนของแท่นบูชาและเทเลือดส่วนที่เหลือลงที่ด้านล่างของแท่น 31เขาจะเอาไขมันทั้งหมดออกเหมือนกับเอาไขมันออกจากเครื่องสันติบูชา และปุโรหิตจะเผาไขมันนั้นบนแท่นบูชา เป็นกลิ่นหอมที่องค์พระผู้เป็นเจ้าพอพระทัย ปุโรหิตจะลบบาปให้เขาโดยวิธีนี้ และเขาจะได้รับการอภัย

32“ ‘หากเขาถวายลูกแกะเป็นเครื่องบูชาไถ่บาป เขาจะต้องนำลูกแกะตัวเมียซึ่งไม่มีตำหนิมา 33เขาจะวางมือบนหัวลูกแกะ และฆ่าลูกแกะนั้นเป็นเครื่องบูชาไถ่บาปในที่สำหรับฆ่าสัตว์เป็นเครื่องเผาบูชา 34ปุโรหิตจะเอานิ้วจุ่มเลือดของเครื่องบูชาไถ่บาปทาเชิงงอนของแท่นเผาเครื่องบูชา แล้วเทเลือดที่เหลือลงบนบริเวณด้านล่างของแท่น 35เขาจะเอาไขมันทั้งหมดออกเหมือนกับที่เอาไขมันออกจากลูกแกะที่เป็นเครื่องสันติบูชา และปุโรหิตจะเผาไขมันนั้นบนแท่นบูชาโดยวางบนเครื่องบูชาด้วยไฟถวายแด่องค์พระผู้เป็นเจ้า ปุโรหิตจะลบบาปให้เขาโดยวิธีนี้สำหรับบาปที่เขาได้ทำ และเขาจะได้รับการอภัย