ዘሌዋውያን 27 – NASV & PCB

New Amharic Standard Version

ዘሌዋውያን 27:1-34

ስለ ስጦታ የወጣ ሕግ

1እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤ 2“ለእስራኤላውያን እንዲህ ብለህ ተናገር፤ ‘ማንኛውም ሰው ተመጣጣኙን ዋጋ በመክፈል ለእግዚአብሔር (ያህዌ) ሰውን ለመስጠት የተለየ ስእለት ቢሳል፣ 3ዕድሜው ከሃያ እስከ ስድሳ ዓመት ለሆነ ወንድ፣ በቤተ መቅደሱ ሰቅል27፥3 0.6 ኪሎ ግራም ገደማ ይሆናል፤ እንዲሁም 16 ይመ ሚዛን መሠረት፣ ግምቱ አምሳ ጥሬ ሰቅል27፥3 11.5 ግራም ገደማ ይሆናል፤ እንዲሁም 25 ይመ ብር ይሁን። 4ለሴት ከሆነ ግምቱ ሠላሳ ሰቅል27፥4 0.3 ኪሎ ግራም ገደማ ይሆናል ይሁን። 5ዕድሜው ከአምስት እስከ ሃያ ዓመት ለሆነ ሰው፣ ወንድ ከሆነ ግምቱ ሃያ ሰቅል፣27፥5 0.2 ኪሎ ግራም ገደማ ይሆናል ሴት ከሆነች ግምቷ ዐሥር ሰቅል27፥5 110 ግራም ገደማ ይሆናል፤ እንዲሁም 7 ይመ ይሁን። 6ዕድሜው ከአንድ ወር እስከ አምስት ዓመት ለሆነ ሰው፣ ወንድ ከሆነ ግምቱ አምስት ሰቅል27፥6 55 ግራም ገደማ ይሆናል ጥሬ ብር፣ ለሴት ከሆነ ሦስት ሰቅል27፥6 35 ግራም ገደማ ይሆናል ጥሬ ብር ይሁን። 7ስድሳ ዓመት ወይም ከዚያ በላይ ለሆነ ሰው፣ ወንድ ከሆነ ግምቱ ዐሥራ አምስት ሰቅል፣ ሴት ከሆነች ዐሥር ሰቅል ይሁን። 8ስእለት የተሳለው ድኻ ከሆነና ግምቱን መክፈል ካልቻለ ግን፣ ለስጦታ ያሰበውን ሰው ወደ ካህኑ ያምጣ፤ ካህኑም የተሳለው ሰው ባለው ዐቅም መሠረት መክፈል የሚገባውን ይተምንለታል።

9“ ‘ሰውየው የተሳለው ለእግዚአብሔር (ያህዌ) መሥዋዕት ሆኖ መቅረብ የሚችል እንስሳ ከሆነ፣ እንዲህ ያለው ለእግዚአብሔር (ያህዌ) የተሰጠ እንስሳ የተቀደሰ ይሆናል። 10ሰውየው መልካም የሆነውን እንስሳ መልካም ባልሆነው፣ መልካም ያልሆነውንም መልካም በሆነው አይለውጥ ወይም አይተካ፤ አንዱን እንስሳ በሌላው ከተካም ሁለቱ የተቀደሱ ይሆናሉ። 11እንስሳው በሥርዐቱ መሠረት የረከሰ፣ ለእግዚአብሔርም (ያህዌ) መሥዋዕት ሆኖ መቅረብ የማይገባው ከሆነ፣ ሰውየው እንስሳውን ወደ ካህኑ ያቅርብ፤ 12መልካም ቢሆን ወይም ባይሆን፣ ካህኑ ዋጋውን ይወስን፤ የካህኑም ውሳኔ የጸና ይሆናል። 13ባለቤቱ እንስሳውን መዋጀት ከፈለገ ግን፣ በተተመነው ዋጋ ላይ አንድ አምስተኛ መጨመር አለበት።

14“ ‘አንድ ሰው ቤቱን ለእግዚአብሔር (ያህዌ) ይሆን ዘንድ ቢቀድስ፣ መልካም ቢሆን ወይም ባይሆን ካህኑ ዋጋውን ይተምን፤ ካህኑም የተመነው ዋጋ የጸና ይሆናል። 15ቤቱን የቀደሰው ሰው መልሶ ሊዋጀው ከፈለገ ግን፣ የዋጋውን አንድ አምስተኛ በዋጋው ላይ መጨመር አለበት፤ ቤቱም ዳግመኛ የራሱ ይሆናል።

16“ ‘አንድ ሰው ከወረሰው ርስት ላይ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) የዕርሻ መሬት ቢቀድስ፣ ዋጋው የሚተመነው ለመሬቱ በሚያስፈልገው ዘር መጠን ይሆናል፤ ይኸውም ለአንድ ሆሜር27፥16 220 ሊትር ገደማ ይሆናል መስፈሪያ የገብስ ዘር አምሳ ሰቅል ጥሬ ብር ነው። 17ሰውየው ዕርሻውን የቀደሰው በኢዮቤልዩ ዓመት ከሆነ፣ የተወሰነው ዋጋ አይለወጥም። 18ዕርሻውን የሚቀድሰው ከኢዮቤልዩ በኋላ ከሆነ ግን፣ ካህኑ ዋጋውን የሚተምነው እስከሚመጣው የኢዮቤልዩ ዓመት ድረስ ባሉት ዓመታት ቍጥር ልክ ነው፤ የተተመነውም ዋጋ ይቀነሳል። 19ዕርሻውን የቀደሰው ሰው መልሶ መዋጀት ከፈለገ፣ በዋጋው ላይ አንድ አምስተኛ መጨመር አለበት፤ ከዚያ በኋላ ዕርሻው እንደ ገና የራሱ ይሆናል። 20ዕርሻውን ባይዋጅ ወይም ለሌላ ሰው አሳልፎ ቢሸጥ፣ ከዚያ በኋላ ሊዋጀው አይችልም። 21ዕርሻው በኢዮቤልዩ በሚለቀቅበት ጊዜ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) እንደ ተሰጠ ዕርሻ ተቈጥሮ ቅዱስና የካህናቱ27፥21 ወይም የካህኑ ንብረት ይሆናል።

22“ ‘አንድ ሰው የወረሰው ርስት ያልሆነውን፣ በገንዘቡ የገዛውን የዕርሻ መሬት ለእግዚአብሔር (ያህዌ) ቢቀድስ፣ 23ካህኑ የዕርሻውን መሬት ዋጋ እስከ ኢዮቤልዩ ዓመት ድረስ ባለው ጊዜ መጠን ይተምናል፤ ሰውየው የተተመነውን ዋጋ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) የተቀደሰ አድርጎ በዚያኑ ዕለት ይክፈል። 24በኢዮቤልዩ ዓመትም የዕርሻው መሬት የቀድሞው ባለ ርስት ለነበረው፣ ለሸጠውም ሰው ይመለሳል። 25እያንዳንዱ ዋጋ የሚተመነው በቤተ መቅደሱ ሰቅል ልክ ሆኖ አንዱ ሰቅል ሃያ ጌራ ነው።

26“ ‘የእንስሳት በኵር ቀድሞውኑ የእግዚአብሔር (ያህዌ) ስለሆነ፣ ማንም ሰው የእንስሳትን በኵር ለእግዚአብሔር (ያህዌ) መቀደስ አይችልም፤ በሬም27፥26 የዕብራይስጡ ቃል ተባዕትና እንስትን ሊያጠቃልል ይችላል ሆነ በግ የእግዚአብሔር (ያህዌ) ነውና። 27እንስሳው ርኩስ ከሆነ ግን፣ ባለቤቱ በተተመነው ዋጋ ላይ አንድ አምስተኛ ጨምሮ ሊዋጀው ይችላል፤ የማይዋጀው ከሆነ ግን በተተመነው ዋጋ ይሸጥ።

28“ ‘ነገር ግን ለእግዚአብሔር (ያህዌ) ተለይቶ የተሰጠ27፥28 የዕብራይስጡ አገላለጽ አንድን ነገር ወይም ሰውን እንደማይመለስ ሆኖ ለእግዚአብሔር መስጠትን ያመለክታል። ማንኛውም ነገር፦ ሰውም ሆነ እንስሳ ወይም በውርስ የተገኘ መሬት አይሸጥም፤ አይዋጅምም። ለእግዚአብሔር (ያህዌ) የተሰጠ ማንኛውም ነገር እጅግ የተቀደሰ ነውና።

29“ ‘እንዲጠፋ የተወሰነ ማንኛውም ሰው አይዋጅም፤27፥29 የዕብራይስጡ አገላለጽ አንድን ነገር ወይም ሰውን ሙሉ በሙሉ በማስወገድ እንደማይመለስ ሆኖ ለእግዚአብሔር መስጠትን ያመለክታል መገደል አለበት።

30“ ‘ከዕርሻ ምርትም ሆነ ከዛፍ ፍሬ፣ ማንኛውም ከምድሪቱ የሚገኝ ዐሥራት የእግዚአብሔር (ያህዌ) ነው፤ ለእግዚአብሔርም (ያህዌ) የተቀደሰ ነው። 31አንድ ሰው ከዐሥራቱ የትኛውንም መዋጀት ቢፈልግ፣ በዋጋው ላይ አንድ አምስተኛ መጨመር አለበት። 32ከቀንድ ከብቶች፣ ከበጎችና ከፍየሎች መንጋ የሚወጣው ዐሥራት ከእረኛ በትር በታች ከሚያልፉት ዐሥረኛው እንስሳ ይሆናል፤ ይህም ለእግዚአብሔር (ያህዌ) የተቀደሰ ነው። 33ሰውየው መልካም የሆነውን መልካም ካልሆነው አይለይ ወይም አይተካ፤ አንዱን በሌላው ቢተካ ግን ሁለቱም እንስሳት የተቀደሱ ይሆናሉ፤ ሊዋጁም አይችሉም።’ ”

34እግዚአብሔር (ያህዌ) በሲና ተራራ ላይ በሙሴ አማካይነት ለእስራኤል ሕዝብ የሰጣቸው ትእዛዞች እነዚህ ናቸው።

Persian Contemporary Bible

لاويان 27:1‏-34

قوانين مربوط به موقوفات

1‏-2خداوند اين مقررات را توسط موسی به قوم اسرائيل داد: هرگاه شخصی به موجب نذری به خداوند وقف شود، می‌تواند مبلغ معينی بپردازد و خود را از وقف آزاد سازد. 3مردی كه سنش بين بيست تا شصت سال باشد، پنجاه مثقال نقره بپردازد. 4زنی كه سنش بين بيست تا شصت سال باشد سی مثقال نقره، 5پسران پنج تا بيست ساله، بيست مثقال نقره و دختران پنج تا بيست ساله، ده مثقال نقره بپردازند. 6برای پسر يک ماهه تا پنج ساله، پنج مثقال نقره و برای دختر يک ماهه تا پنج ساله، سه مثقال نقره پرداخت شود. 7مرد از شصت سال به بالا، پانزده مثقال نقره و زن از شصت سال به بالا، ده مثقال نقره بپردازد. 8ولی اگر كسی فقيرتر از آن باشد كه بتواند اين مبلغ را بپردازد، نزد كاهن آورده شود و كاهن مبلغی را تعيين كند كه او قادر به پرداخت آن باشد.

9‏-10اگر كسی حيوانی كه مورد قبول خداوند است نذر كند بايد همان حيوان را تقديم نمايد زيرا اين نذر مقدس است و نمی‌توان آن را عوض كرد. نذركننده تصميم خود را دربارهٔ چيزی كه برای خداوند نذر كرده است تغيير ندهد و خوب را با بد يا بد را با خوب عوض نكند. اگر چنين كند، اولی و دومی، هر دو از آن خداوند خواهند بود. 11‏-12ولی اگر حيوانی كه برای خداوند نذر شده آن نوع حيوانی نيست كه برای قربانی مجاز می‌باشد، صاحبش آن را نزد كاهن بياورد تا قيمتش را تعيين كند و او بايد آن مبلغ را بپردازد. 13اگر حيوان از نوعی است كه می‌توان آن را به عنوان قربانی تقديم نمود ولی صاحبش می‌خواهد آن را بازخريد نمايد، در آن صورت علاوه بر قيمتی كه كاهن تعيين می‌كند، بايد يک پنجم قيمت آن را نيز اضافه بپردازد.

14‏-15اگر كسی خانهٔ خود را وقف خداوند كند ولی بعد بخواهد آن را بازخريد نمايد، كاهن بايد قيمت خانه را تعيين كند و نذركننده، اين مبلغ را به اضافه يک پنجم بپردازد. آنگاه خانه دوباره از آن خودش خواهد بود.

16اگر كسی قسمتی از زمين خود را وقف خداوند كند، ارزش آن به تناسب مقدار بذری كه در آن می‌توان كاشت تعيين شود. قطعه زمينی كه صد كيلو جو در آن پاشيده شود، پنجاه مثقال نقره ارزش دارد. 17اگر شخصی در سال يوبيل مزرعهٔ خود را وقف خداوند كند، در آن صورت قيمت زمين برابر با قيمت محصول پنجاه سالهٔ آن خواهد بود. 18ولی اگر بعد از سال يوبيل باشد، آنگاه كاهن قيمت زمين را به تناسب تعداد سالهايی كه به سال يوبيل بعدی باقی مانده است، تعيين خواهد كرد. 19اگر آن شخص تصميم بگيرد آن مزرعه را بازخريد نمايد، بايستی علاوه بر قيمتی كه كاهن تعيين می‌نمايد يک پنجم هم اضافه بپردازد و مزرعه دوباره مال خودش خواهد شد. 20ولی اگر مزرعه را بدون اينكه بازخريد نموده باشد، به ديگری بفروشد، ديگر هرگز حق بازخريد آن را نخواهد داشت. 21وقتی كه در سال يوبيل آن زمين آزاد شود، به عنوان موقوفه متعلق به خداوند خواهد بود و بايد به كاهنان داده شود.

22اگر كسی مزرعه‌ای را كه خريده است، وقف خداوند كند ولی آن مزرعه قسمتی از ملک خانوادگی او نباشد، 23كاهن بايد ارزش آن را به تناسب مقدار سالهايی كه تا سال يوبيل مانده، تعيين كند، و او هم بايد همان روز مبلغ تعيين شده را بپردازد. اين مبلغ به خداوند تعلق دارد. 24در سال يوبيل مزرعه به صاحب اصلی آن كه از او خريداری شده، باز پس داده شود. 25تمام قيمت‌گذاری‌ها بايد مطابق قيمت تعيين شده باشد.

26اولين نوزاد هر حيوانی متعلق به خداوند است، پس كسی نمی‌تواند آن را برای خداوند نذر كند. اولين نوزاد حيوان حلال گوشت را می‌توان به خداوند تقديم كرد. 27اما نوزاد حيوان حرام گوشت را كه نمی‌توان برای خداوند قربانی كرد، می‌توان با پرداخت قيمتی كه كاهن برای آن تعيين می‌كند به اضافهٔ يک پنجم، بازخريد نمود. اگر صاحبش نخواهد آن را بازخريد كند، كاهن می‌تواند آن را به شخص ديگری بفروشد.

28اما چيزی كه تماماً وقف خداوند شده باشد27‏:28 «تقديس» يعنی جدا کردن، اختصاص دادن و مقدس ساختن.‏، چه انسان، چه حيوان و چه مزرعهٔ خانوادگی، هرگز فروخته يا بازخريد نشود چون برای خداوند بسيار مقدس است. 29كسی كه در دادگاه به مرگ محكوم شده باشد نمی‌تواند جان خود را بازخريد نمايد، بلكه بايد حتماً كشته شود.

30ده يک محصول زمين، چه از غله و چه از ميوه، از آن خداوند است و مقدس می‌باشد. 31اگر كسی بخواهد اين ميوه يا غله را بازخريد نمايد، بايد يک پنجم به قيمت اصلی آن اضافه كند.

32ده يک گله و رمه از آن خداوند است. وقتی حيوانات شمرده می‌شوند، هر دهمين حيوان متعلق به خداوند است. 33صاحب گله نبايد حيوانات را طوری قرار دهد كه حيوانات بد برای خداوند جدا شوند و نبايد جای حيوان خوب را با بد عوض كند. اگر چنين كند، هر دو حيوان متعلق به خداوند خواهند بود و ديگر هرگز حق بازخريد آنها را نخواهد داشت.

34اين است دستوراتی كه خداوند در كوه سينا توسط موسی به قوم اسرائيل داد.