ዘሌዋውያን 26 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዘሌዋውያን 26:1-46

በመታዘዝ የሚገኝ በረከት

1“ ‘ትሰግዱላቸው ዘንድ ጣዖታትን አታብጁ፤ ምስል ወይም የማምለኪያ ዐምድ አታቁሙ፤ በምድራችሁም ላይ የተቀረጸ ድንጋይ አታኑሩ፤ እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ (ያህዌ ኤሎሂም) ነኝ።

2“ ‘ሰንበታቴን ጠብቁ፤ መቅደሴን አክብሩ፤ እኔ እግዚአብሔር (ያህዌ) ነኝ።

3“ ‘በሥርዐቴ ብትሄዱ፣ ትእዛዜንም በጥንቃቄ ብትጠብቁ፣ 4ዝናብን በወቅቱ እሰጣችኋለሁ፤ ምድሪቱ እህሏን፣ የሜዳ ዛፎችም ፍሬያቸውን ይሰጣሉ። 5የምትወቁት እህል፣ የወይን ዘለላ እስከምትቈርጡበት ጊዜ፣ የምትቈርጡትም የወይን ዘለላ፣ እህል እስከምትዘሩበት ጊዜ ያደርሷችኋል፤ ምግባችሁን እስክትጠግቡ ትበላላችሁ፤ በምድራችሁም ላይ በጸጥታ ትኖራላችሁ።

6“ ‘በምድሪቱ ላይ ሰላምን እሰጣለሁ፤ ትተኛላችሁ፤ ማንም አያስፈራችሁም። ክፉ አራዊትን ከምድሪቱ አስወግዳለሁ፤ ሰይፍም በምድራችሁ ላይ አያልፍም። 7ጠላቶቻችሁን ታሳድዳላችሁ፤ እነርሱም በፊታችሁ በሰይፍ ይወድቃሉ። 8ከእናንተ አምስቱ መቶውን፣ መቶውም ዐሥሩን ሺሕ ያሳድዳሉ፤ ጠላቶቻችሁም በፊታችሁ በሰይፍ ይወድቃሉ።

9“ ‘ፊቴን ወደ እናንተ እመልሳለሁ፤ እንድታፈሩና እንድትበዙም አደርጋችኋለሁ፤ ቃል ኪዳኔንም ከእናንተ ጋር አጸናለሁ። 10የዓምናውን እህል እየበላችሁ ከጐተራው ሳያልቅ ለዘንድሮው እህል ደግሞ ቦታ ታስለቅቃላችሁ። 11ማደሪያዬን26፥11 ወይም የመገናኛ ድንኳኔን በመካከላችሁ አደርጋለሁ፤ ነፍሴም አትጸየፋችሁም። 12በመካከላችሁ እመላለሳለሁ፤ አምላካችሁ (ኤሎሂም) እሆናለሁ፤ እናንተም ሕዝቤ ትሆናላችሁ። 13ለግብፃውያን ባሪያዎች እንዳትሆኑ ከግብፅ ምድር ያወጣኋችሁ እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ (ያህዌ ኤሎሂም) ነኝ፤ የባርነት ቀንበራችሁን ሰብሬ ቀና ብላችሁ እንድትሄዱ አድርጌአችኋለሁ።

አለመታዘዝ የሚያስከትለው ቅጣት

14“ ‘ነገር ግን ባትሰሙኝ፣ እነዚህን ትእዛዛት ባትጠብቁ፣ 15ሥርዐቴን ብትንቁ፣ ሕጌን ብታቃልሉ፣ ትእዛዞቼንም ሁሉ ባለመፈጸም ቃል ኪዳኔን ብታፈርሱ፣ 16እኔም ይህን አደርግባችኋለሁ፤ ድንገተኛ ድንጋጤ፣ የሚቀሥፍ በሽታ፣ ዐይናችሁን የሚያጠፋና ሰውነታችሁን የሚያመነምን ትኵሳት አመጣባችኋለሁ፤ እህል የምትዘሩት በከንቱ ነው፤ ጠላቶቻችሁ ይበሉታልና። 17በጠላቶቻችሁ ድል እንድትሆኑ ፊቴን በእናንተ ላይ አከብድባችኋለሁ፤ የሚጠሏችሁ ይገዟችኋል፤ ማንም ሳያሳድዳችሁም ትሸሻላችሁ።

18“ ‘ከዚህ ሁሉ በኋላ ባትታዘዙኝ፣ ስለ ኀጢአታችሁ ሰባት ዕጥፍ እቀጣችኋለሁ፤ 19የትዕቢታችሁን ኀይል እሰብራለሁ፤ ሰማያችሁን እንደ ብረት፣ ምድራችሁንም እንደ ናስ አደርጋለሁ። 20ኀይላችሁ በከንቱ ያልቃል፤ ምድራችሁ እህሏን፣ የምድሪቱ ዛፎችም ፍሬዎቻቸውን አይሰጡምና።

21“ ‘በእኔ ላይ ማመፅ ብትቀጥሉና ባትታዘዙኝ እንደ ኀጢአታችሁ መጠን ሰባት ዕጥፍ መቅሠፍት እጨምርባችኋለሁ። 22የዱር አራዊትን እሰድድባችኋለሁ፤ ልጆቻችሁን ይነጥቋችኋል፤ ከብቶቻችሁን ያጠፉባችኋል፤ ቍጥራችሁ ይመነምናል፤ መንገዶቻችሁም ሰው አልባ ይሆናሉ።

23“ ‘በዚህ ሁሉ ግን ወደ እኔ ባትመለሱ፣ በእኔም ላይ ማመፃችሁን ብትቀጥሉ 24እኔም ጠላት እሆንባችኋለሁ፤ ስለ ኀጢአታችሁም ሰባት ዕጥፍ አስጨንቃችኋለሁ። 25ቃል ኪዳኔን ስላፈረሳችሁ፣ በላያችሁ ሰይፍ በማምጣት እበቀላችኋለሁ፤ በከተሞቻችሁ ውስጥ በምትሰበሰቡበት ጊዜ ቸነፈር እሰድድባችኋለሁ፤ ለጠላትም እጅ ዐልፋችሁ ትሰጣላችሁ። 26የእንጀራችሁ እህል እንዲቋረጥ በማደርግበት ጊዜ፣ ዐሥር ሴቶች በአንድ ምጣድ ላይ እንጀራ ይጋግራሉ፤ እንጀራውንም በሚዛን መዝነው እናንተም ትበላላችሁ፤ ግን አትጠግቡም።

27“ ‘በዚህ ሁሉ ግን ባትታዘዙኝ፣ በእኔም ላይ ማመፃችሁን ብትቀጥሉ፣ 28እኔም በቍጣዬ እመጣባችኋለሁ፤ ስለ ኀጢአታችሁም እኔው ራሴ ሰባት ዕጥፍ እቀጣችኋለሁ። 29የወንዶች ልጆቻችሁን ሥጋና የሴቶች ልጆቻችሁን ሥጋ ትበላላችሁ። 30የኰረብታ መስገጃዎቻችሁን እደመስሳለሁ፤ የዕጣን መሠዊያዎቻችሁን አፈርሳለሁ፤ በድኖቻችሁን በድን በሆኑት ጣዖቶቻችሁ ላይ እጥላለሁ፤ ነፍሴም ትጸየፋችኋለች። 31ከተሞቻችሁን አፈራርሳለሁ፤ መቅደሶቻችሁንም ወና አደርጋለሁ፤ ጣፋጭ ሽታ ያለውን መሥዋዕታችሁንም አልቀበልም። 32በዚያ የሚኖሩ ጠላቶቻችሁ እስኪደነቁ ድረስ፣ ምድሪቱን ባድማ አደርጋታለሁ። 33በአሕዛብ መካከል እበትናችኋለሁ፤ ሰይፌን መዝዤም አሳድዳችኋለሁ። ምድራችሁ ባድማ፣ ከተሞቻችሁም ፍርስራሽ ይሆናሉ። 34ምድሪቱ ባድማ በሆነችበት ጊዜ ሁሉና እናንተም በጠላቶቻችሁ ምድር በምትኖሩበት ወቅት ምድሪቱ በሰንበት ዓመቷ ትደሰታለች፤ ምድሪቱም በሰንበቷ ታርፋለች፤ ትደሰታለችም። 35ምድሪቱ እናንተ በነበራችሁባት ጊዜ በሰንበት ያላገኘችውን ዕረፍት፣ ባድማ በምትሆንበት ጊዜ ሁሉ ታገኛለች።

36“ ‘ከእናንተ በሕይወት የተረፉትን፣ በጠላቶቻቸው ምድር ሳሉ ድንጋጤ እሰድድባቸዋለሁ፤ ነፋስ የሚያንቀሳቅሰው የቅጠል ድምፅ ያስበረግጋቸዋል፤ የሚያሳድዳቸውም ሳይኖር ከሰይፍ እንደሚሸሹ ይሮጣሉ፤ ይወድቃሉም። 37የሚያሳድዳቸው ሳይኖር ከሰይፍ እንደሚሸሹ እርስ በርሳቸው ይሰነካከላሉ፤ በጠላቶቻችሁም ፊት መቆም አትችሉም። 38በአሕዛብ መካከል ታልቃላችሁ፤ የጠላቶቻችሁም ምድር ትውጣችኋለች። 39ከእናንተ የተረፉት በጠላቶቻቸው ምድር በራሳቸው ኀጢአትና በአባቶቻቸው ኀጢአት ምክንያት መንምነው ያልቃሉ።

40“ ‘ነገር ግን ለእኔ ያልታመኑበትንና በእኔም ላይ ያመፁበትን የራሳቸውን ኀጢአትና የአባቶቻቸውን ኀጢአት ቢናዘዙ፣ 41ይኸውም፣ እኔ ጠላት እንድሆንባቸውና ወደ ጠላቶቻቸው ምድር እንድሰድዳቸው ያደረገኝን ኀጢአት ቢናዘዙ፣ ያልተገረዘው ልባቸው ቢዋረድና ስለ ኀጢአታቸው የሚገባውን ቅጣት ቢቀበሉ፣ 42በዚያ ጊዜ ከያዕቆብ ጋር የገባሁትን ኪዳኔን፣ ከይስሐቅም ጋር የገባሁትን ኪዳኔን፣ ደግሞም ከአብርሃም ጋር የገባሁትን ኪዳኔን ዐስባለሁ፤ ምድሪቱንም አስባታለሁ። 43ምድሪቱ እነርሱ ለቅቀዋት ስለ ሄዱ ባዶ ትቀራለች፤ እነርሱ በሌሉበት ጊዜም ባድማ ሆና በሰንበቷ ትደሰታለች፤ ሕጌን በማቃለላቸውና ሥርዐቴን በመናቃቸው፣ የኀጢአታቸውን ቅጣት ይቀበላሉ። 44በዚህ ሁሉ ግን ከእነርሱ ጋር የገባሁትን ኪዳኔን በማፍረስ፣ በጠላቶቻቸው ምድር ሳሉ ፈጽሜ እስካጠፋቸው ድረስ አልተዋቸውም፤ አልጸየፋቸውምም፤ እኔ እግዚአብሔር አምላካቸው (ያህዌ ኤሎሂም) ነኝ። 45ስለ እነርሱም ስል፣ አምላካቸው (ኤሎሂም) እሆን ዘንድ አሕዛብ እያዩ ከግብፅ ምድር ካወጣኋቸው አባቶቻቸው ጋር የገባሁትን ኪዳን ዐስባለሁ፤ እኔ እግዚአብሔር (ያህዌ) ነኝ።’ ”

46እግዚአብሔር (ያህዌ) በራሱና በእስራኤላውያን መካከል በሲና ተራራ ላይ በሙሴ በኩል ያቆማቸው ሥርዐቶች፣ ሕጎችና ደንቦች እነዚህ ናቸው።

Thai New Contemporary Bible

เลวีนิติ 26:1-46

รางวัลของการเชื่อฟัง

1“ ‘เจ้าอย่าสร้างรูปเคารพ หรือทำแบบจำลอง หรือตั้งศิลาศักดิ์สิทธิ์สำหรับตัวเจ้าและอย่าวางหินสลักในดินแดนของเจ้าเพื่อกราบไหว้ เราคือพระยาห์เวห์พระเจ้าของเจ้า

2“ ‘จงถือรักษาสะบาโตของเรา และยำเกรงสถานนมัสการของเรา เราคือพระยาห์เวห์

3“ ‘หากเจ้าปฏิบัติตามกฎหมายของเรา และใส่ใจเชื่อฟังคำสั่งของเรา 4เราจะให้ฝนตกต้องตามฤดูกาล แผ่นดินจะให้พืชผลอุดมและต้นไม้จะออกผล 5ช่วงเวลานวดข้าวจะเนิ่นนานถึงฤดูเก็บผลองุ่น และฤดูเก็บผลองุ่นจะเนิ่นนานไปถึงฤดูหว่าน เจ้าจะได้รับประทานอย่างอิ่มหนำ และอาศัยอยู่อย่างปลอดภัยในแผ่นดินของเจ้า

6“ ‘เราจะให้ความสงบสุขในแผ่นดินนั้น ยามนอนเจ้าจะไม่ต้องหวาดผวา เราจะขับไล่สัตว์ร้ายออกไปจากแผ่นดินนั้น และดาบจะไม่แผ้วพานแผ่นดินของเจ้าเลย 7เจ้าจะรุกไล่ศัตรูของเจ้า คนเหล่านั้นจะล้มตายด้วยคมดาบต่อหน้าเจ้า 8พวกเจ้าห้าคนจะรุกไล่ศัตรูนับร้อย พวกเจ้าร้อยคนจะรุกไล่ศัตรูนับหมื่น ศัตรูทั้งหลายจะล้มตายด้วยคมดาบต่อหน้าเจ้า

9“ ‘เราจะดูแลเจ้าด้วยความโปรดปรานและให้เจ้ามีลูกเต็มบ้านมีหลานเต็มเมือง และเราจะรักษาพันธสัญญาของเราที่ให้ไว้กับเจ้า 10เจ้าจะยังคงกินพืชผลจากการเก็บเกี่ยวในปีที่แล้ว เมื่อต้องขยับขยายจัดที่สำหรับพืชผลรุ่นใหม่ 11เราจะตั้งที่พำนัก26:11 หรือพลับพลาของเราท่ามกลางพวกเจ้า และเราจะไม่ชิงชังพวกเจ้า 12เราจะดำเนินอยู่ท่ามกลางพวกเจ้า เป็นพระเจ้าของเจ้า เจ้าจะเป็นประชากรของเรา 13เราคือพระยาห์เวห์พระเจ้าของเจ้า ผู้นำเจ้าทั้งหลายออกมาจากอียิปต์ เพื่อเจ้าจะไม่ต้องเป็นทาสของชาวอียิปต์อีกต่อไป เราได้ทำลายแอกของเจ้า และช่วยให้เจ้าก้าวเดินไปอย่างสง่าผ่าเผย

โทษของการไม่เชื่อฟัง

14“ ‘แต่หากเจ้าไม่ฟังเรา ไม่ปฏิบัติตามคำสั่งเหล่านี้ 15และหากเจ้าปฏิเสธกฎหมายของเรา และชิงชังบทบัญญัติของเรา ไม่ได้ทำตามคำสั่งของเราซึ่งเป็นการละเมิดพันธสัญญาของเรา 16แล้วเราจะทำกับเจ้าอย่างนี้คือ เราจะนำความหวาดหวั่นพรั่นพรึงมาอย่างฉับพลัน โรคต่างๆ และความเจ็บไข้ที่ทำลายสายตาของเจ้า และทำให้ชีวิตของเจ้าทรุดโทรมไปมาเหนือเจ้า เจ้าจะหว่านพืชโดยเปล่าประโยชน์ เพราะศัตรูของเจ้าจะมากิน 17เราจะตั้งตนเป็นปฏิปักษ์กับเจ้า เพื่อเจ้าจะพ่ายแพ้ต่อหน้าศัตรู บรรดาผู้เกลียดชังเจ้าจะปกครองเจ้า เจ้าจะวิ่งหนีแม้ขณะที่ไม่มีใครไล่ตาม

18“ ‘และหากเจ้ายังไม่ยอมเชื่อฟัง เราจะลงโทษเจ้าหนักขึ้นเจ็ดเท่า ให้สมกับบาปของเจ้า 19เราจะทำลายความเย่อหยิ่งอย่างดื้อด้านของเจ้า และทำให้ท้องฟ้าเหนือเจ้าเป็นเช่นเหล็กและแผ่นดินเบื้องล่างเจ้าเป็นดั่งทองสัมฤทธิ์ 20เจ้าจะเสียเหงื่อลงแรงโดยเปล่าประโยชน์เพราะแผ่นดินจะไม่ให้พืชผล ต้นไม้ในที่ดินก็จะไม่ออกผล

21“ ‘หากเจ้ายังคงขัดขืนต่อต้านและไม่ยอมฟังเรา เราจะทวีความทุกข์ยากขึ้นอีกเจ็ดเท่า ให้สาสมกับบาปของเจ้า 22เราจะส่งสัตว์ร้ายมาเล่นงานเจ้าและพวกมันจะปล้นเอาลูกหลานของเจ้าไป จะทำลายฝูงสัตว์ของเจ้าและจะทำให้จำนวนคนของเจ้าลดลงจนถนนหนทางเริศร้าง

23“ ‘หากเราทำกับเจ้าถึงขนาดนี้แล้ว เจ้ายังไม่ยอมรับการดัดนิสัยจากเรา แต่ยังคงขัดขืนต่อต้านเรา 24เราเองจะต่อสู้กับเจ้า และจะให้เจ้าทุกข์ทรมานเพราะบาปของตนหนักยิ่งขึ้นอีกเจ็ดเท่า 25และเราจะนำดาบมายังเจ้าเพื่อแก้แค้นที่พันธสัญญาของเราถูกละเมิด เมื่อเจ้าถอยหนีเข้าไปยังเมืองต่างๆ ของเจ้า เราจะส่งโรคระบาดร้ายแรงมาท่ามกลางพวกเจ้า และเจ้าจะตกอยู่ในมือของศัตรู 26เราจะทลายแหล่งเสบียงของเจ้า ถึงขนาดหญิงสิบคนใช้เตาเพียงเตาเดียวอบขนมให้พวกเจ้า และต้องชั่งอาหารแบ่งกันกิน เจ้าจะกินแต่ไม่อิ่ม

27“ ‘หากถึงขนาดนี้แล้วเจ้ายังไม่ฟังเรา แต่ยังคงขัดขืนต่อต้านเรา 28เราจะต่อสู้กับเจ้าด้วยพระพิโรธ และเราเองจะลงโทษบาปของเจ้าหนักยิ่งขึ้นเจ็ดเท่า 29เจ้าจะกินเนื้อลูกชายลูกสาวของตัวเอง 30เราจะทลายแท่นบูชาบนที่สูงของเจ้า จะโค่นแท่นเผาเครื่องหอมของเจ้า ทิ้งซากศพของเจ้าไว้บนรูปเคารพที่ไม่มีชีวิตของพวกเจ้า และเราจะชิงชังพวกเจ้า 31เราจะทำให้นครต่างๆ ของเจ้าเริศร้าง และทำลายสถานนมัสการของเจ้า เราจะไม่นิยมยินดีในกลิ่นหอมที่น่าพอใจจากเครื่องบูชาของเจ้า 32เราจะทิ้งให้แผ่นดินเริศร้างจนศัตรูของเจ้าที่เข้ามาพักอาศัยตกใจ 33เราจะทำให้พวกเจ้ากระจัดกระจายไปท่ามกลางชนชาติต่างๆ เราจะชักดาบออกจากฝักรุกไล่เจ้า ดินแดนของเจ้าจะถูกทิ้งร้างและเมืองต่างๆ จะถูกทำลาย 34แล้วแผ่นดินจะได้ชื่นชมกับปีสะบาโตของมันตลอดช่วงที่ถูกทิ้งร้างซึ่งเจ้าตกอยู่ในดินแดนของศัตรู แผ่นดินจะได้พักสงบและชื่นชมกับสะบาโตของมัน 35ตลอดช่วงที่ถูกทิ้งร้าง แผ่นดินจะได้พักสงบ ชดเชยกับที่ไม่ได้หยุดพักในช่วงสะบาโตขณะที่เจ้าอาศัยอยู่ในแผ่นดิน

36“ ‘สำหรับพวกที่เหลืออยู่ เราจะทำให้จิตใจของพวกเขาหวาดหวั่นขวัญผวาในแดนของศัตรูถึงขนาดเสียงใบไม้ถูกลมพัดปลิวก็ทำให้พวกเขาหนีไป เขาจะวิ่งราวกับหนีเตลิดจากคมดาบ และเขาจะล้มลงแม้ไม่มีใครไล่ตาม 37เขาจะสะดุดล้มทับกันราวกับหนีเตลิดจากคมดาบแม้ไม่มีใครรุกไล่พวกเขา ดังนั้นเจ้าจะไม่สามารถยืนหยัดต่อหน้าศัตรูของเจ้า 38เจ้าจะพินาศในหมู่ประชาชาติทั้งหลาย และถูกกลืนหายไปในดินแดนของศัตรู 39คนที่เหลืออยู่จะเสื่อมโทรมไปในดินแดนของศัตรูเพราะบาปของพวกเขา และเพราะบาปของบรรพบุรุษของพวกเขา

40“ ‘แต่หากพวกเขาสารภาพบาปของตนและบาปของบรรพบุรุษที่พวกเขาขัดขืนต่อต้านเรา 41ซึ่งทำให้เราเป็นศัตรูกับเขา จนเราส่งพวกเขาไปยังดินแดนของเหล่าศัตรู ตราบจนจิตใจที่ไม่ได้เข้าสุหนัตของเขาถ่อมลงและพวกเขาชดใช้บาปของตน 42เมื่อนั้นเราจะระลึกถึงพันธสัญญาของเราที่ให้ไว้กับยาโคบ อิสอัค และอับราฮัม และจะระลึกถึงแผ่นดินนั้น 43เพราะแผ่นดินนั้นจะชื่นชมกับสะบาโตของมันขณะที่ถูกทิ้งร้างอยู่ พวกเขาจะชดใช้บาปของตนที่ได้ละทิ้งบทบัญญัติของเราและเกลียดชังกฎหมายของเรา 44แต่กระนั้นเมื่อเขาอยู่ในดินแดนของศัตรู เราจะไม่ปฏิเสธหรือเกลียดชังพวกเขาจนถึงกับทำลายล้างพวกเขาให้หมดสิ้น ซึ่งเป็นการละเมิดพันธสัญญาของเรากับพวกเขา เราคือพระยาห์เวห์พระเจ้าของพวกเขา 45แต่เพื่อเห็นแก่พวกเขา เราจะระลึกถึงพันธสัญญาที่ให้ไว้กับบรรพบุรุษของพวกเขาซึ่งเราได้พาออกมาจากอียิปต์ต่อหน้าประชาชาติทั้งหลาย เพื่อเป็นพระเจ้าของพวกเขา เราคือพระยาห์เวห์’ ”

46ทั้งหมดนี้คือกฎหมาย บทบัญญัติ และกฎระเบียบ ซึ่งองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงตั้งไว้ระหว่างพระองค์เองกับชนอิสราเอลผ่านทางโมเสสบนภูเขาซีนาย