ዘሌዋውያን 25 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

ዘሌዋውያን 25:1-55

የሰባተኛው ዓመት ዕረፍት

1እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን በሲና ተራራ ላይ እንዲህ አለው፤ 2“ለእስራኤላውያን እንዲህ ብለህ ተናገር፤ ‘ወደምሰጣችሁ ምድር በምትገቡበት ጊዜ ምድሪቱ ራሷ የእግዚአብሔርን (ያህዌ) ሰንበት ታክብር። 3ስድስት ዓመት በዕርሻህ ላይ ዝራ፤ ስድስት ዓመት ወይንህን ግረዝ፤ ፍሬውንም ሰብስብ። 4በሰባተኛው ዓመት ግን ምድሪቱ የዕረፍት ሰንበት ታድርግ፤ ይህም የእግዚአብሔር (ያህዌ) ሰንበት ነው። በዕርሻህ ላይ አትዝራ፤ ወይንህንም አትግረዝ። 5ሳይዘራ የበቀለውን አትጨደው፤ ካልተገረዘው የወይን ተክልህ ፍሬ አትሰብስብ። ምድሪቱ የአንድ ዓመት ዕረፍት ታድርግ። 6ምድሪቱም በሰንበት ጊዜዋ የምታስገኘው ማንኛውም ፍሬ ለአንተ፣ ለወንድ ባሪያህ፣ ለሴት ባሪያህ፣ ለቅጥር ሠራተኛህና ከአንተ ጋር ለሚኖር መጻተኛ ምግብ ይሁን፤ 7እንዲሁም ለቤት እንስሶችህና በምድርህ ለሚኖሩ የዱር አራዊት ምድሪቱ የምታበቅለው ሁሉ መኖ ይሁን።

የኢዮቤልዩ ዓመት

25፥8-38 ተጓ ምብ – ዘዳ 15፥1-11

25፥39-55 ተጓ ምብ – ዘፀ 21፥2-11ዘዳ 15፥12-18

8“ ‘ሰባት የሰንበት ዓመታት ማለትም ሰባት ጊዜ ሰባት ዓመታትን ቍጠር፤ ሰባቱ የሰንበት ዓመታትም አርባ ዘጠኝ ዓመታት ይሆናሉ። 9ከዚያም በኋላ በሰባተኛው ወር በዐሥረኛው ቀን፣ መለከት ይነፋ፤ በማስተስረያ ቀንም በምድራችሁ ሁሉ መለከት ንፉ። 10አምሳኛውን ዓመት ቀድሱ፤ በምድሪቱ ሁሉ ላሉ ነዋሪዎች በሙሉ ነጻነት ዐውጁ፤ ይህም ኢዮቤልዩ ይሁንላችሁ፤ ከእናንተ እያንዳንዱ ወደ ቤተ ሰቡ ርስት፣ ወደ ወገኑም ይመለስ። 11የአምሳኛው ዓመት ኢዮቤልዩ ይሁንላችሁ፤ አትዝሩ፤ ሳትዘሩት የበቀለውን አትጨዱ፤ ካልተገረዘውም የወይን ሐረግ ፍሬ አትሰብስቡ። 12ኢዮቤልዩ ስለሆነ ለእናንተ የተቀደሰ ይሁን፤ ሳትዘሩት በሜዳ የበቀለውን ብሉ።

13“ ‘በዚህ በኢዮቤልዩ ዓመት እያንዳንዱ ሰው ወደ ርስቱ ይመለስ።

14“ ‘ከወገንህ ከአንዱ መሬት ብትገዛ ወይም ብትሸጥለት፣ አንዱ ሌላውን አያታልል። 15ከኢዮቤልዩ በኋላ ያሉትን ዓመታት ብዛት መሠረት በማድረግ ከወገንህ ትገዛለህ፤ እርሱም የቀሩትን የመከር ዓመታት ብዛት መሠረት በማድረግ ይሸጥልሃል። 16የዓመቱ ቍጥር ከበዛ ዋጋውን ጨምር፤ የዓመቱ ቍጥር ካነሰም፣ ዋጋውን ቀንስ፤ ምክንያቱም የሚሸጥልህ የዓመቱን የምርት መጠን ነውና። 17አንዱ ሌላውን አያታልል፤ አምላክህን (ኤሎሂም) ፍራ፤ እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ (ያህዌ ኤሎሂም) ነኝ።

18“ ‘ሥርዐቴን ጠብቁ፤ ሕጌን በጥንቃቄ አድርጉ፤ በምድሪቱም በሰላም ትኖራላችሁ። 19ምድሪቱ ፍሬዋን ትሰጣለች፤ እስክትጠግቡ ትበላላችሁ፤ በዚያም በሰላም ትኖራላችሁ። 20እናንተም፣ “ካልዘራን ወይም ሰብላችንን ካልሰበሰብን በሰባተኛው ዓመት ምን እንበላለን?” በማለት ትጠይቁ ይሆናል። 21በስድስተኛው ዓመት በረከቴን እሰድድላችኋለሁ፤ ምድሪቱም ለሦስት ዓመት የሚበቃ ፍሬ ትሰጣለች። 22በስምንተኛው ዓመት በምትዘሩበት ጊዜ፣ የምትበሉት ቀድሞ ከሰበሰባችሁት ሰብል ይሆናል፤ የዘጠነኛውን ዓመት መከር እስክትሰበስቡ ድረስ ከዚሁ እህል ትበላላችሁ።

23“ ‘መሬት ለዘለቄታ አይሸጥ፤ ምክንያቱም ምድሪቱ የእኔ ናት፤ እናንተም መጻተኞችና እንግዶች ናችሁ። 24ርስት አድርጋችሁ በምትይዙት ምድር ሁሉ መሬት የሚዋጅበት ሁኔታ እንዲኖር አድርጉ።

25“ ‘ከወገንህ አንዱ ደኽይቶ ርስቱን ቢሸጥ፣ የቅርብ ዘመዱ መጥቶ ወገኑ የሸጠውን ይዋጅለት። 26ነገር ግን ሰውየው ርስቱን የሚዋጅለት ምንም ዘመድ ባይኖረውና እርሱ ራሱ መዋጀት የሚችልበትን ሀብት ቢያገኝ፣ 27ርስቱን ከሸጠበት ጊዜ ጀምሮ ያለውን የሽያጭ ዘመን በመቍጠር የዋጋውን ልዩነት ለገዛው ሰው ይመልስ፤ እርሱም ወደ ገዛ ርስቱ ይመለስ። 28ነገር ግን ዋጋውን መመለስ ካልቻለ፣ የሸጠው ርስት እስከ ኢዮቤልዩ ዓመት ድረስ የገዥው ንብረት ሆኖ ይቈያል፤ በኢዮቤልዩ ዓመት ለባለቤቱ ይመለሳል፤ ሰውየውም ወደ ርስቱ ይመለሳል።

29“ ‘ማንኛውም ሰው ቅጥር በተሠራለት ከተማ ውስጥ የሚገኝ መኖሪያ ቤቱን ቢሸጥ ከሸጠበት ጊዜ ጀምሮ እስከ አንድ ዓመት ሊዋጀው ይችላል፤ የመዋጀት መብቱ እስከ አንድ ዓመት ድረስ ነው። 30አንዱ ዓመት ከማለቁ በፊት መዋጀት ካልቻለ ግን፣ ቅጥር በተሠራለት ከተማ ውስጥ ያለው ቤት የገዢውና የልጅ ልጆቹ ንብረት ሆኖ ይቀራል፤ በኢዮቤልዩ አይመለስለትም። 31ቅጥር በዙሪያው ባልተሠራለት መንደር ውስጥ የሚገኙ ቤቶች ግን እንደ ዕርሻ መሬት ተቈጥረው ሊዋጁ ይችላሉ፤ በኢዮቤልዩም ይመለሳሉ።

32“ ‘ነገር ግን ሌዋውያን የራሳቸው በሆኑት ከተሞች ውስጥ የሚገኙትን ቤቶቻቸውን ምንጊዜም የመዋጀት መብት አላቸው። 33ሌዋውያን በከተማቸው ያለውን ቤታቸውን ቢሸጡና መዋጀት ባይችሉ፣ በኢዮቤልዩ ይመለሳል፤ በሌዋውያን ከተሞች የሚገኙ ቤቶች በእስራኤላውያን መካከል የሌዋውያን ንብረት ናቸውና። 34በከተሞቻቸው ዙሪያ ያለው የግጦሽ መሬት ግን አይሸጥ፤ ለዘላለም ቋሚ ንብረታቸው ነውና።

35“ ‘በመካከልህ ከወገንህ አንዱ ቢደኸይ፣ ራሱንም መርዳት ባይችል፣ በመካከልህ ይኖር ዘንድ መጻተኛውን ወይም እንግዳውን እንደምትረዳ እርዳው። 36ወገንህ በመካከልህ ይኖር ዘንድ ምንም ዐይነት ወለድ25፥36 ወይም እጅግ ብዙ ወለድ፤ እንዲሁም 37 ይመ አትቀበለው፤ አምላክህን (ኤሎሂም) ፍራው። 37ገንዘብህን በዐራጣ አታበድረው፤ ምግብህንም በትርፍ አትሽጥለት። 38የከነዓንን ምድር ልሰጥህና አምላክህ (ኤሎሂም) ልሆን፣ ከግብፅ ያወጣሁህ እኔ እግዚአብሔር አምላክህ (ያህዌ ኤሎሂም) ነኝ።

39“ ‘ከወገንህ አንዱ ከመካከልህ ቢደኸይ፣ ራሱንም ለአንተም ቢሸጥ፣ እንደ ባሪያ አድርገህ አታሠራው። 40በመካከልህ እንዳለ ቅጥር ሠራተኛ ወይም እንደ እንግዳ አድርገህ ቍጠረው፤ እስከ ኢዮቤልዩ ዓመትም ይሥራልህ፤ 41ከዚያም በኋላ እርሱና ልጆቹ በነጻ ይለቀቁ፤ ወደ ቤተ ሰቡና ወደ አባቶቹ ንብረት ይመለስ። 42እስራኤላውያን ከግብፅ ያወጣኋቸው አገልጋዮቼ ስለ ሆኑ እንደ ባሪያ አይሸጡ። 43በጭካኔ አትግዛቸው፤ ነገር ግን አምላክህን (ኤሎሂም) ፍራ።

44“ ‘የሚኖሩህ ወንዶችና ሴቶች ባሪያዎችህ፣ በዙሪያህ ካሉት አሕዛብ መካከል የገዛሃቸው ባሪያዎች ይሁኑ። 45እንደዚሁም በመካከላችሁ ከሚኖሩት መጻተኞችና ከተወለዱት ወገናቸው ባሪያዎችን ግዙ፤ ንብረታችሁም ይሁኑ። 46እነርሱንም እንደ ንብረት ለልጆቻችሁ አውርሷቸው፤ በሕይወታቸው ዘመን ሁሉ ባሪያዎች ይሁኗችሁ፤ እስራኤላውያን ወገኖቻችሁን ግን በጭካኔ አትግዟቸው።

47“ ‘በመካከላችሁ የሚኖር መጻተኛ ወይም እንግዳ ሀብታም ቢሆንና ከወገናችሁ አንዱ ደኽይቶ በመካከላችሁ ለሚኖር መጻተኛ ወይም ከመጻተኛው ወገን ለአንዱ ራሱን ቢሸጥ፣ 48ከተሸጠ በኋላ ሊዋጅ ይችላል። ከዘመዶቹም አንዱ፣ 49አጎቱ ወይም የአጎቱ ልጅ ወይም ከወገኖቹ ማንኛውም የሥጋ ዘመዱ ይዋጀው፤ ሀብት ካገኘም ራሱን መዋጀት ይችላል። 50እርሱም ራሱን ከሸጠበት ዓመት አንሥቶ እስከ ኢዮቤልዩ ዓመት ድረስ ያለውን ጊዜ ከገዛው ሰው ጋር በመሆን ይቍጠር፤ ነጻ የሚለቀቅበትም ዋጋ በእነዚያ ዓመታት ለአንድ ቅጥር ሠራተኛ በሚከፈለው መሠረት ይተመናል። 51ብዙ ዓመት የሚቀረው ከሆነም፣ እርሱን ለመግዛት ከተከፈለው ዋጋ ላይ በቀረው ዓመት መጠን ለሚዋጅበት መልስ ይክፈል። 52እስከ ኢዮቤልዩ ድረስ የሚቀረው ጥቂት ዓመት ከሆነም፣ በቀረው ዓመት መጠን የሚዋጅበትን መልስ ይክፈል። 53ከዓመት እስከ ዓመት እንደ ቅጥር ሠራተኛ ይኑር፤ አሳዳሪውም በፊትህ በጭካኔ አይግዛው።

54“ ‘ከእነዚህ መንገዶች በአንዱ እንኳ መዋጀት ባይችል፣ እርሱና ልጆቹ በኢዮቤልዩ ዓመት በነጻ ይለቀቁ፤ 55እስራኤላውያን ለእኔ አገልጋዮቼ ናቸውና። እነርሱ ከግብፅ ምድር ያወጣኋቸው አገልጋዮቼ ናቸው፤ እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ (ያህዌ ኤሎሂም) ነኝ።

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

利未记 25:1-55

安息年的条例

1耶和华在西奈山上对摩西说: 2“你把以下条例告诉以色列人。

“你们到了我将要赐给你们的土地后,要让土地每七年在耶和华面前休耕一年。 3六年之内,你们可以耕种田地,修整葡萄园,收获出产。 4但第七年是安息年,土地要休息,以尊崇耶和华。你们不可耕种,不可修整葡萄园。 5不可收割自生自长的庄稼,也不可摘未经修剪而结的葡萄。这一年土地要休耕。 6但安息年间土地里自生自长的,你们和你们的仆婢、雇工与住在你们中间的外族人都可以吃, 7你们的牲畜和境内的野兽也可以吃。

禧年的条例

8“你们要计算七个安息年,即七个七年,共四十九年。 9第五十年的七月十日赎罪日那天,你们要在境内各地吹号。 10你们要以这年为圣年,向境内所有居民宣告自由。这年将成为你们的禧年。各人要得回卖掉的祖业,卖身为奴的可以自由回家。 11第五十年是你们的禧年。这一年你们不可耕种,不可收割自生自长的庄稼,也不可摘未经修剪而结的葡萄。 12这是禧年,是你们的圣年,你们可以吃土地里自生自长的。 13在禧年,各人要得回卖掉的地业。 14因此,你们和同胞买卖田地时,不可彼此亏负。 15买卖双方要按照距下个禧年的年数多少定价。 16距下个禧年的年数多,价钱就高;年数少,价钱就低。因为卖的是田地收成的次数。 17要敬畏你们的上帝,不可彼此亏负。我是你们的上帝耶和华。 18你们要遵行我的律例,持守我的典章,就可以在那片土地上安居。 19土地会出产丰富,使你们丰衣足食、安然居住。 20你们可能会问,‘第七年不种不收,我们吃什么?’ 21我要在第六年赐福给你们,使田地的出产够你们吃三年。 22第八年开始耕种时,你们仍会吃陈粮,一直吃到第九年的收割季节。

赎回土地的条例

23“你们不可永远卖掉土地,因为土地是我的,你们只不过是寄居在那片土地上的过客。 24你们购买每一块土地时,都必须让原主保留赎回的权利。 25如果有人因贫穷而卖掉土地,他的近亲要把卖掉的土地赎回来。 26如果无人为他赎回,而他自己渐渐富裕起来,有能力赎回, 27他要计算卖掉土地的年数,退还距下个禧年所剩年数的地价,便可以赎回自己的土地。 28如果他没有能力赎回,所卖的土地在禧年之前要属于买主。到了禧年,买主必须把土地归还原主。

赎回房屋的条例

29“如果有人卖掉自己城里的房子,要保留一年赎回权。卖掉房子的一年之内,他可以赎回。 30如果一年之内他没有赎回,房子便永远归买主所有,就是到了禧年也不用归还。 31如果房子在四围无墙的乡村,要视房子为乡下的土地,原主可以赎回;到了禧年,买主必须将房子归还。 32利未人的城邑里,利未人有权随时赎回所卖的房子。 33如果他们没有赎回,到了禧年要把房子归还他们;因为在利未人的城里,利未人的房屋是他们在以色列人中所拥有的产业。 34但不可出卖利未人城郊的草场。那是他们永远拥有的产业。

照顾同胞的条例

35“如果你们的同胞生活日益贫穷,难以维生,你们要像照顾外族人和寄居者一样照顾他的生活,让他住在你们当中。 36你们不可从中谋利,要敬畏上帝,让他住在你们当中。 37你们借钱给他,不可收取利息;借粮给他,不可谋利。 38我是你们的上帝耶和华。我曾经带领你们离开埃及,为要把迦南赐给你们,并做你们的上帝。

买卖奴隶的条例

39“如果你们的同胞穷得把自己卖给你们,不可把他当作奴隶, 40要待他像雇工和寄居者一样。他要为你工作到禧年。 41到了禧年,他和孩子们便可以离开你们,回到自己的宗族和祖业。 42因为以色列人是我的仆人,是我从埃及带出来的,所以他们不可卖身为奴。 43你们也不可苛待他们,要敬畏你们的上帝。 44你们可以从邻国购买奴隶, 45也可以买居住或出生在你们境内的外族人。这些人可以作你们的产业。 46你们可以将他们作为产业传给你们的子孙,使他们终身做奴隶。但你们不可苛待自己的同胞。

47“如果你们中间的外族人渐渐富裕,你们同胞中却有人日益贫穷,把自己卖给外族人或他们的族人, 48他可以保留赎身的权利。他的兄弟、 49叔伯、堂兄弟或其他近亲都可以赎回他。如果他富裕起来,也可以赎回自己。 50他要和买主计算从自己卖身为奴到下个禧年之间的年数,然后按雇工的工价,照年数计算赎价。 51如果离禧年还有很多年,他就要按比例偿还大部分卖身款为自己赎身。 52如果离禧年只有不多的几年,他就要按年数偿还卖身款为自己赎身。 53买主要待他如按年雇佣的工人。你们要确保买主不会苛待他。 54如果禧年来临前他没有被赎回,到了禧年他和孩子们都要获得自由。 55因为以色列人是我的仆人,是我从埃及领出来的仆人。我是你们的上帝耶和华。