ዘሌዋውያን 24 – NASV & NUB

New Amharic Standard Version

ዘሌዋውያን 24:1-23

በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት የሚቀርብ ዘይትና ኅብስት

24፥1-3 ተጓ ምብ – ዘፀ 27፥20-21

1እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤ 2“መብራቶቹ ያለ ማቋረጥ እንዲያበሩ ከወይራ ተጨምቆ የተጠለለ ዘይት እንዲያመጡልህ እስራኤላውያንን እዘዛቸው። 3አሮንም በመገናኛው ድንኳን ውስጥ ከምስክሩ መጋረጃ ውጭ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ያሉትን መብራቶች ከምሽት እስከ ንጋት ያለ ማቋረጥ ያሰናዳቸው፤ ይህም ለትውልዶቻችሁ ሥርዐት ነው። 4በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት በንጹሕ የወርቅ መቅረዝ ላይ ያሉት መብራቶች ያለ ማቋረጥ መሰናዳት አለባቸው።

5“የላመ ዱቄት ወስደህ ዐሥራ ሁለት ኅብስት ጋግር፤ እያንዳንዱ ኅብስትም በሁለት ዐሥረኛ የኢፍ24፥5 4.5 ሊትር ገደማ ይሆናል መስፈሪያ ዱቄት ይጋገር። 6እነዚህንም ስድስት ስድስቱን በሁለት ረድፍ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ባለው የንጹሕ ወርቅ ጠረጴዛ ላይ አኑራቸው። 7ከኅብስቱ ጋር የመታሰቢያ ድርሻ ሆኖ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) በእሳት የሚቀርብ መሥዋዕት እንዲሆን ንጹሕ ዕጣን በእያንዳንዱ ረድፍ ላይ አኑር። 8ኅብስቱ የእስራኤልን ሕዝብ ይወክል ዘንድ ዘወትር በየሰንበቱ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ይደርደር፤ ይህም የዘላለም ቃል ኪዳን ነው። 9ኅብስቱ የአሮንና የልጆቹ ድርሻ ነው፤ በተቀደሰ ስፍራም ይበሉታል፤ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) በእሳት ከሚቀርበው መሥዋዕት እጅግ የተቀደሰ ድርሻቸው ነውና።”

እግዚአብሔርን መስደብ የሚያስከትለው ቅጣት

10እናቱ እስራኤላዊት፣ አባቱ ግብፃዊ የሆነ አንድ ሰው በእስራኤላውያን መካከል ወጣ፤ በሰፈርም ውስጥ ከአንድ እስራኤላዊ ጋር ተጣሉ። 11የእስራኤላዊቱ ልጅ የእግዚአብሔርን (ያህዌ) ስም በማቃለል ሰደበ፤ ስለዚህም ወደ ሙሴ አመጡት፤ የሰውየው እናት ስም ሰሎሚት ነበር፤ እርሷም ከዳን ወገን የተወለደው የደብራይ ልጅ ነበረች። 12የእግዚአብሔር (ያህዌ) ፈቃድም ግልጽ እስኪሆንላቸው ድረስ በግዞት አኖሩት።

13እግዚአብሔርም (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤ 14“ተሳዳቢውን ከሰፈር ወደ ውጭ አውጣው፤ ሲሳደብ የሰሙት ሁሉ እጃቸውን በራሱ ላይ ይጫኑበት፤ ማኅበሩም ሁሉ በድንጋይ ይውገረው። 15እስራኤላውያንን እንዲህ በላቸው፤ ‘ማንም ሰው አምላኩን (ኤሎሂም) ቢሳደብ ኀጢአት ሠርቷልና ይጠየቅበታል። 16የእግዚአብሔርን (ያህዌ) ስም የሚሳደብ ማንኛውም ሰው ይገደል፤ ማኅበሩ ሁሉ ይውገሩት፤ መጻተኛም ሆነ የአገር ተወላጅ የእግዚአብሔርን (ያህዌ) ስም ከሰደበ ይገደል።

17“ ‘ሰውን ደብድቦ የገደለ ይገደል። 18የሌላውን ሰው እንስሳ ደብድቦ የገደለ ማንኛውም ሰው ያንኑ ዐይነት እንስሳ ይተካለት። 19ማንኛውም ሰው በባልንጀራው ላይ ጕዳት ቢያደርስ፣ የዚያው ዐይነት ጕዳት ይፈጸምበት፤ 20ይኸውም በስብራት ፈንታ ስብራት፣ በዐይን ፈንታ ዐይን፣ በጥርስ ፈንታ ጥርስ ማለት ነው። በሌላው ሰው ላይ ያደረሰው ጕዳት በእርሱም ላይ ይድረስበት፤ 21እንስሳ የገደለ ማንኛውም ሰው በገደለው ፈንታ ይተካ፤ ሰው የገደለ ግን ይገደል። 22ለመጻተኛው ሆነ ለአገር ተወላጅ አንድ ዐይነት ሕግ ይኑራችሁ፤ እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ (ያህዌ ኤሎሂም) ነኝ።’ ”

23ሙሴም ይህን ለሕዝቡ ነገራቸው፤ እነርሱም ተሳዳቢውን ከሰፈር ወደ ውጭ ወስደው በድንጋይ ወገሩት፤ እስራኤላውያንም እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዳዘዘው አደረጉ።

Swedish Contemporary Bible

3 Moseboken 24:1-23

Olja och bröd inför Herren

(2 Mos 27:20-21)

1Herren talade till Mose: 2”Säg till Israels folk att skaffa fram ren olja av pressade oliver till lampstället så att lamporna ständigt kan brinna. 3Utanför förhänget framför förbundstecknet i uppenbarelsetältet ska Aron sköta om dem varje kväll och morgon så att de brinner natten igenom inför Herren. Detta är en bestående stadga som ska gälla generation efter generation. 4Lamporna i lampstället av rent guld ska ständigt brinna inför Herren.

5Av siktat mjöl ska du baka tolv bröd och använda fyra liter mjöl till varje bröd. 6Du ska stapla dem i två högar med sex bröd i var på bordet av rent guld inför Herren 7och bredvid dem ska du lägga ren rökelse som i stället för bröd är ett påminnelseoffer, ett eldoffer inför Herren.

8Sabbatsdag efter sabbatsdag ska man lägga ut bröden inför Herren som ett evigt förbund för israeliterna. 9Aron och hans söner ska ha bröden som sin del och äta dem på en helig plats. De är högheliga och ska för alltid vara hans andel av eldoffret till Herren.”

Straffet för hädelse mot Gud

10Ute i lägret började en man vars mor var israelit och hans far egypter att slåss med en israelitisk man. 11Sonen till den israelitiska kvinnan smädade och förbannade Namnet24:11 Syftar på det heliga gudsnamnet. och fördes fram till Mose. Hans mor hette Shelomit, dotter till Divri av Dans stam. 12Han hölls i förvar till dess Herrens vilja blev kungjord.

13Herren talade till Mose: 14”För ut honom utanför lägret och be alla som hört vad han sagt att lägga sina händer på hans huvud. Sedan ska hela menigheten stena honom till döds. 15Säg till israeliterna att den som hädar sin Gud måste stå för det. 16Den som smädar Herrens namn måste dö. Hela församlingen ska stena honom. Såväl en utlänning som en israelit som hädar Herrens namn måste dö.

17Den som dödar en annan människa måste straffas med döden. 18Den som dödar ett djur måste ersätta det liv för liv. 19När någon skadar sin nästa, ska man göra detsamma för honom, 20bruten lem för bruten lem, öga för öga och tand för tand. Så som någon skadar en annan, ska han själv skadas.

21Den som alltså dödar ett djur måste ersätta det och den som dödar en människa måste dö. 22Ni ska ha samma lag för en utlänning och en israelit, för jag är Herren, er Gud.”

23Så talade Mose till israeliterna. De förde då ut mannen som förbannat utanför lägret och stenade honom. Så som Herren hade befallt Mose, så gjorde israeliterna.