ዘሌዋውያን 23 – NASV & NSP

New Amharic Standard Version

ዘሌዋውያን 23:1-44

1እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤ 2“ለእስራኤላውያን እንዲህ ብለህ ተናገር፤ ‘የተቀደሱ ጉባኤዎች ብላችሁ የምትዋጇቸው የተመረጡ የእግዚአብሔር (ያህዌ) በዓላት እነዚህ ናቸው፤

ሰንበት

3“ ‘ሥራ የምትሠሩበት ስድስት ቀን አላችሁ፤ ሰባተኛው ቀን ግን የዕረፍት ሰንበት፣ የተቀደሰ ጉባኤ ዕለት ነው። የእግዚአብሔር (ያህዌ) ሰንበት ስለሆነ፣ በምትኖሩበት ስፍራ ሁሉ ምንም ዐይነት ሥራ አትሥሩበት።

የፋሲካና የቂጣ በዓል

23፥4-8 ተጓ ምብ – ዘፀ 12፥14-20ዘኍ 28፥16-25ዘዳ 16፥1-8

4“ ‘የተመረጡ የእግዚአብሔር (ያህዌ) በዓላት ብላችሁ በተወሰኑላቸው ጊዜያት የምታውጇቸው የተቀደሱ ጉባኤዎች እነዚህ ናቸው፤ 5የመጀመሪያው ወር በገባ በዐሥራ አራተኛው ቀን ምሽት የእግዚአብሔር (ያህዌ) ፋሲካ በዓል ይጀመራል። 6በዚያው ወር በዐሥራ አምስተኛው ቀን የእግዚአብሔር (ያህዌ) የቂጣ በዓል ይጀመራል፤ ሰባት ቀንም ያለ እርሾ የተጋገረ ቂጣ ትበላላችሁ። 7በመጀመሪያው ቀን የተቀደሰ ጉባኤ አድርጉ፤ የዕለት ተግባራችሁንም አታከናውኑ። 8ሰባት ቀን በእሳት የሚቃጠል መሥዋዕት ለእግዚአብሔር (ያህዌ) አቅርቡ፤ በሰባተኛው ቀን የተቀደሰ ጉባኤ አድርጉ፤ በዚያ ዕለት የተለመደ ተግባራችሁን አታከናውኑ።’ ”

የበኵራት ስጦታ በዓል

9እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤ 10“ለእስራኤላውያን እንዲህ ብለህ ተናገር፤ ‘እኔ ወደምሰጣችሁ ምድር ገብታችሁ መከር በምትሰበስቡበት ጊዜ ከሰበሰባችሁት እህል የመጀመሪያውን ነዶ ለካህኑ አቅርቡ፤ 11ነዶው ተቀባይነት እንዲያገኝላችሁም በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ይወዝውዘው፤ ካህኑ ነዶውን የሚወዘውዘው በሰንበት ቀን ማግስት ነው። 12ነዶውን በምትወዘውዙበት ቀን እንከን የሌለበትን የአንድ ዓመት ተባዕት የበግ ጠቦት የሚቃጠል መሥዋዕት እንዲሆን ለእግዚአብሔር (ያህዌ) አቅርቡ፤ 13ከዚህም ጋር ለእግዚአብሔር (ያህዌ) በእሳት የሚቀርብ፣ ሽታውም ደስ የሚያሰኝ እንዲሆን ሁለት ዐሥረኛ የኢፍ23፥13 4.5 ሊትር ገደማ ይሆናል፤ እንዲሁም 17 ይመ መስፈሪያ በዘይት የተለወሰ የላመ ዱቄት ለእህል ቍርባን፣ አንድ አራተኛ የኢን23፥13 1 ሊትር ገደማ ይሆናል መስፈሪያ የወይን ጠጅ ለመጠጥ ቍርባን አቅርቡ። 14ስጦታውን ለአምላካችሁ (ኤሎሂም) እስከምታቀርቡበት እስከዚያ ቀን ድረስ፣ እንጀራም ቢሆን ቈሎ ወይም እሸት አትብሉ፤ ይህም በምትኖሩበት ስፍራ ሁሉ ለሚመጡት ትውልዶች የዘላለም ሥርዐት ነው።

የመከር በዓል

23፥15-22 ተጓ ምብ – ዘኍ 28፥26-31ዘዳ 16፥9-12

15“ ‘የሚወዘወዘውን የነዶ መሥዋዕት ካቀረባችሁበት የሰንበት ማግስት አንሥታችሁ ሰባት ሙሉ ሳምንታት ቍጠሩ። 16እስከ ሰባተኛው ሰንበት ማግስት ድረስ አምሳ ቀን ቍጠሩ፤ ከዚያም የአዲስ እህል ቍርባን ለእግዚአብሔር (ያህዌ) አቅርቡ። 17በሁለት ዐሥረኛ የኢፍ መስፈሪያ የላመ ዱቄት፣ በእርሾ የተጋገረ ሁለት እንጀራ ለሚወዘወዝ መሥዋዕት፣ የበኵራት ስጦታ እንዲሆን ከየቤታችሁ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) አምጡ። 18ከእንጀራውም ጋር ሰባት ነውር የሌለባቸው የአንድ ዓመት ተባዕት የበግ ጠቦቶች፣ አንድ ወይፈንና ሁለት አውራ በጎች አቅርቡ፤ እነዚህም ከእህል ቍርባናቸውና ከመጠጥ ቍርባናቸው ጋር ለእግዚአብሔር (ያህዌ) የሚቃጠል መሥዋዕት ይሆናሉ፤ ይህም በእሳት የሚቀርብ ሽታውም እግዚአብሔርን (ያህዌ) ደስ የሚያሰኝ መሥዋዕት ነው። 19እንዲሁም አንድ ተባዕት ፍየል ለኀጢአት መሥዋዕት፣ ሁለት የአንድ ዓመት ተባዕት ጠቦቶችም ለኅብረት መሥዋዕት23፥19 በትውፊት የሰላም መሥዋዕት ይባላል አቅርቡ። 20ካህኑም ሁለቱን የበግ ጠቦቶች ከበኵራቱ እንጀራ ጋር የሚወዘወዝ መሥዋዕት አድርጎ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ይወዘውዛቸዋል፤ እነዚህም ለእግዚአብሔር (ያህዌ) ቅዱስ መሥዋዕት፣ የካህኑም ድርሻ ናቸው። 21በዚያኑ ዕለት የተቀደሰ ጉባኤ ዐውጁ፤ የተለመደ ተግባራችሁንም አታከናውኑ፤ ይህም በምትኖሩበት ስፍራ ሁሉ ለሚመጡት ትውልዶች የዘላለም ሥርዐት ነው።

22“ ‘የምድራችሁን መከር በምትሰበስቡበት ጊዜ፣ የዕርሻችሁን ዳርና ዳር አትጨዱ፤ ቃርሚያውን አትልቀሙ፤ እነዚህንም ለድኾችና ለእንግዶች ተዉላቸው፤ እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ (ያህዌ ኤሎሂም) ነኝ።’ ”

የመለከት በዓል

23፥23-25 ተጓ ምብ – ዘኍ 29፥1-6

23እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤ 24“እስራኤላውያንን እንዲህ በላቸው፤ ‘የሰባተኛው ወር የመጀመሪያ ቀን ዕረፍት ይሁንላችሁ፤ በመለከት ድምፅም የሚከበር የተቀደሰ ጉባኤ ይኑራችሁ። 25መሥዋዕትን በእሳት ለእግዚአብሔር (ያህዌ) አቅርቡ እንጂ የተለመደ ተግባራችሁን አታከናውኑበት።’ ”

የስርየት ቀን

23፥26-32 ተጓ ምብ – ዘሌ 16፥2-34ዘኍ 29፥7-11

26እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤ 27“የሰባተኛው ወር ዐሥረኛ ቀን የስርየት ቀን ነው፤ የተቀደሰ ጉባኤ አድርጉ፤ አንዳች ነገርም አትብሉ፤23፥27 ወይም ጹሙ፤ እንዲሁም 29፡32 ይመ መሥዋዕትም በእሳት ለእግዚአብሔር (ያህዌ) አቅርቡ። 28በእግዚአብሔር (ያህዌ) በአምላካችሁ (ኤሎሂም) ፊት ለእናንተ ስርየት የሚደረግበት የስርየት ቀን ስለሆነ፣ በዚያ ዕለት ምንም ሥራ አትሥሩ። 29በዚያ ዕለት ሰውነቱን የሚያጐሳቍል ማንኛውም ሰው ከወገኖቹ መካከል ተለይቶ ይጥፋ። 30በዚያ ዕለት ማንኛውንም ሥራ የሚሠራውን ሰው ሁሉ ከወገኖቹ መካከል ለይቼ አጠፋዋለሁ። 31ማንኛውንም ሥራ ከቶ አትሥሩበት፤ ይህ በምትኖሩበት ስፍራ ሁሉ ለልጅ ልጆቻችሁ የዘላለም ሥርዐት ነው። 32ይህ ለእናንተ የዕረፍት ሰንበት ስለሆነ፣ ራሳችሁን ዝቅ ዝቅ አድርጉ23፥32 ወይም ጹሙ በወሩም ከዘጠነኛው ቀን ምሽት ጀምራችሁ እስከሚቀጥለው ቀን ምሽት ድረስ ሰንበታችሁን አክብሩ።”

የዳስ በዓል

23፥33-43 ተጓ ምብ – ዘኍ 29፥12-39ዘዳ 16፥13-17

33እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤ 34“እስራኤላውያንን እንዲህ በላቸው፤ ‘ሰባተኛውም ወር በገባ በዐሥራ አምስተኛው ቀን የእግዚአብሔር (ያህዌ) የዳስ በዓል ይጀምራል፤ እስከ ሰባት ቀንም ይቈያል። 35የመጀመሪያው ቀን የተቀደሰ ጉባኤ ነውና የተለመደ ተግባራችሁን አታከናውኑበት። 36ሰባት ቀን መሥዋዕቱን በእሳት ለእግዚአብሔር (ያህዌ) አቅርቡ፤ በስምንተኛው ቀን የተቀደሰ ጉባኤ አድርጉ፤ መሥዋዕትን በእሳት ለእግዚአብሔር (ያህዌ) አቅርቡ፤ የተለመደ ተግባራችሁንም አታከናውኑበት።

37“ ‘የሚቃጠል መሥዋዕትንና የእህል ቍርባንን፣ መሥዋዕትንና የመጠጥ ቍርባንን በተመደበላቸው ቀን ለእግዚአብሔር (ያህዌ) በእሳት ለማቅረብ፣ የተቀደሱ ጉባኤዎችን የምታውጁባቸው የእግዚአብሔር (ያህዌ) በዓላት እነዚህ ናቸው። 38እነዚህ መሥዋዕቶች ለእግዚአብሔር (ያህዌ) ሰንበት ከምታቀርቡት፣ ከስጦታችሁ፣23፥38 ወይም እነዚህ በዓላት ከእግዚአብሔር ሰንበታት በተጨማሪ የምታቀርቧቸው ናቸው፤ ስጦታዎቹም ከስእለታችሁና ከበጎ ፈቃድ ስጦታችሁ በተጨማሪ የምታቀርቧቸው ስጦታዎች ናቸው።

39“ ‘የምድራችሁን ፍሬ ከሰበሰባችሁ በኋላ በሰባተኛው ወር ከዐሥራ አምስተኛው ቀን ጀምራችሁ ሰባት ቀን ለእግዚአብሔር (ያህዌ) በዓል አክብሩ፤ የመጀመሪያው ቀን የዕረፍት ዕለት ነው፤ ስምንተኛውም ቀን እንደዚሁ የዕረፍት ዕለት ይሆናል። 40በመጀመሪያው ቀን የመልካም ዛፍ ፍሬ፣ የዘንባባ ዝንጣፊ፣ የለመለመ ዛፍ ቅርንጫፍ የአኻያ ዛፍ ቅርንጫፍ ይዛችሁ ሰባት ቀን በአምላካችሁ በእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ፊት ደስ ይበላችሁ። 41በየዓመቱም የእግዚአብሔር (ያህዌ) በዓል አድርጋችሁ ሰባት ቀን አክብሩ፤ ይህም ለልጅ ልጃችሁ የዘላለም ሥርዐት ነው፤ በሰባተኛውም ወር አክብሩት። 42ሰባት ቀን ዳስ ውስጥ ተቀመጡ፤ በትውልዱ እስራኤላዊ የሆነ ሁሉ ዳስ ውስጥ ይሰንብት፤ 43በዚህም እኔ እስራኤላውያንን ከግብፅ ባወጣሁ ጊዜ፣ ዳስ ውስጥ እንዲቀመጡ ማድረጌን የልጅ ልጆቻችሁ ያውቃሉ፤ እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ (ያህዌ ኤሎሂም) ነኝ።’ ”

44በዚህ ሁኔታም ሙሴ የተመረጡትን የእግዚአብሔር (ያህዌ) በዓላት ለእስራኤላውያን አስታወቀ።

New Serbian Translation

3. Мојсијева 23:1-44

Празници

1Господ рече Мојсију: 2„Говори народу израиљском. Реци им: ’Ово су Господњи празници, када ћете сазивати свете саборе. Ово су моји празници:

Субота

3Шест дана ради, а седмога дана је субота потпуног одмора, свети сабор. Не радите никаквог посла; нека Господња субота буде по свим вашим местима.

4Ово су Господњи празници, свети сабори, које ћеш прослављати у одређено време:

Пасха и празник Бесквасних хлебова

5Првога месеца, четрнаестог дана у месецу, увече, почиње Пасха Господња. 6А петнаестога дана истог месеца је Господњи празник Бесквасних хлебова. Једите бесквасне хлебове седам дана.

7Првога дана одржавајте свети сабор; не радите никаквог свакодневног посла. 8Седам дана приносите Господу паљене жртве. А седмога дана биће свети сабор: не радите никакав посао.’“

Прва жетва

9Господ рече Мојсију: 10„Говори Израиљцима. Реци им: ’Кад уђете у земљу коју вам ја дајем, и почнете од ње жети жетву, први сноп своје жетве донесите свештенику. 11Тада нека он подигне сноп пред Господом да будете примљени. Свештеник ће га подигнути наредног дана након суботе. 12На дан када подижете сноп, принесите јагње од годину дана, без мане, као жртву свеспалницу Господу, 13а уз њега десетину ефе брашна замешеног с уљем, као житну жртву. То је паљена жртва, угодни мирис Господу. Уз њега иде и жртва изливница од четвртине хина23,13 Око 1 l. вина. 14До тог дана, док не принесете принос свога Бога, не смете јести хлеб, пржено жито, или свеже класје. То је вечна уредба за ваше нараштаје по свим вашим местима.

Празник Седмица

15Наредног дана након суботе, пошто принесете клас за жртву дизаницу, набројте седам пуних недеља. 16Набројте педесет дана до првога дана након седме суботе, па принесите Господу жртву од новог жита. 17Донесите из својих места два хлеба за жртву дизаницу, сваки од по две десетине мере брашна. Нека буду печени с квасцем, као првина за Господа. 18Са хлебом принесите седам јагањаца без мане, од годину дана, једног јунца из крда, и два овна, за жртву свеспалницу Господу, заједно с њиховим житним жртвама и жртвама изливницама, као паљену жртву, угодан мирис Господу. 19Принесите и једног јарца као жртву за грех, и два јагњета од годину дана, као жртву мира. 20Нека их свештеник подигне пред Господом с хлебом од првина, као жртву дизаницу, и са она два јагњета. То је свети принос за Господа, који следује свештенику. 21Истог дана сазовите сабор. Нека вам то буде свети сабор. Не радите никакав свакодневни посао! Ово је трајна уредба за све ваше нараштаје по свим вашим местима.

22Кад почнете жети жетву са своје земље, немојте жети до самог краја свога поља, нити пабирчити после своје жетве. То оставите сиромаху и странцу. Ја сам Господ, Бог ваш.’“

Први дан седмог месеца

23Господ рече Мојсију: 24„Говори Израиљцима: ’Седмога месеца, првога дана у месецу, нека вам буде потпуни починак, спомен-дан објављен гласом трубе, свети сабор. 25Не радите никаквог свакодневног посла. Принесите Господу паљену жртву.’“

Дан откупљења

26Господ рече Мојсију: 27„А десетог дана седмога месеца је дан откупљења. Нека вам то буде свети сабор. Постите23,27 Дословно: Мучите или Понизити своју душу. и принесите паљену жртву Господу. 28Не радите никаквог посла на тај дан, јер је то дан откупљења, када ће се извршити ваше откупљење пред Господом, Богом вашим. 29Онај ко не буде постио на овај дан, нека се истреби из свог народа. 30Ко год се буде латио каквог посла на овај дан, њега ћу ја затрти усред његовог народа. 31Не радите никаквог посла! То је трајна уредба за ваше нараштаје, по свим вашим местима. 32Нека вам то буде субота потпуног одмора. Постите! Прослављајте своју суботу од вечери деветог дана у месецу до следеће вечери.“

Празник Сеница

33Господ рече Мојсију: 34„Говори Израиљцима: ’Петнаестог дана у седмом месецу је празник Сеница Господу, у трајању од седам дана. 35Првога дана је свети сабор: не радите никаквог свакодневног посла. 36Седам дана приносите Господу паљене жртве, а осмога дана нека вам буде свети сабор. Тада ћете приносити Господу паљене жртве. То је свечани сабор; не радите никаквог посла.

37То су Господњи празници, које ћете славити као свете саборе, приносећи Господу паљене жртве, жртве свеспалнице, житне жртве, приносе и жртве изливнице, сваку у одређени дан, 38осим Господњих субота и ваших дарова, и осим свих завета и добровољних прилога које приносите Господу.

39А петнаестог дана у седмом месецу, кад прикупите првине земље, седам дана славите Господњи празник. Први и осми дан нека буду дани потпуног одмора. 40На први дан узмите најбоље плодове, палмове гране, гране с лиснатог дрвећа, и врбе с потока, па се седам дана веселите пред Господом, Богом својим. 41Прослављајте Господњи празник седам дана у години. Ово је трајна уредба за ваше нараштаје: славите тај празник седмог месеца. 42Живите у сеницама седам дана; сви рођени у Израиљу нека живе у сеницама, 43да би ваши нараштаји знали да сам ја, Господ, Бог ваш, учинио да народ израиљски живи у сеницама, кад сам их извео из Египта.’“

44Тако је Мојсије саопштио Израиљцима Господње празнике.