ዘሌዋውያን 15 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዘሌዋውያን 15:1-33

የሚያረክስ የሰውነት ፈሳሽ

1እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴንና አሮንን እንዲህ አላቸው፤ 2“ለእስራኤላውያን እንዲህ ብላችሁ ንገሯቸው፤ ‘ማንም ሰው ከሰውነቱ ፈሳሽ ነገር ቢወጣ ያ ሰው ርኩስ ነው። 3ከሰውነቱ የሚወጣው ፈሳሽ መፍሰሱን ቢቀጥል ወይም ባይቀጥል ሰውየው ርኩስ ነው፤ ፈሳሹም ርኩሰት የሚያስከትለው እንደዚህ ነው፦

4“ ‘ፈሳሽ ነገር የሚወጣው ሰው የተኛበት የትኛውም መኝታ ርኩስ ይሆናል፤ እርሱ የተቀመጠበት ማንኛውም ነገር ርኩስ ይሆናል። 5ዐልጋውን የነካ ማንኛውም ሰው ልብሱን ይጠብ፤ ሰውነቱንም በውሃ ይታጠብ፤ እስከ ማታ ድረስ ግን ርኩስ ይሆናል። 6ፈሳሽ ነገር የሚወጣው ሰው በተቀመጠበት በየትኛውም ነገር ላይ የተቀመጠ ሰው ሁሉ ልብሱን ይጠብ፤ ሰውነቱንም በውሃ ይታጠብ፤ እስከ ማታ ድረስ ግን ርኩስ ይሆናል።

7“ ‘ፈሳሽ ነገር የሚወጣውን ሰው የነካ ማንኛውም ሰው ልብሱን ይጠብ፤ ሰውነቱንም በውሃ ይታጠብ፤ እስከ ማታ ድረስ ግን ርኩስ ይሆናል።

8“ ‘ፈሳሽ ነገር የሚወጣው ሰው ንጹሕ በሆነ ሰው ላይ ቢተፋ፣ የተተፋበት ሰው ልብሱን ይጠብ፤ ሰውነቱንም በውሃ ይታጠብ፤ እስከ ማታ ድረስ ግን ርኩስ ይሆናል።

9“ ‘ፈሳሽ ነገር የሚወጣው ሰው የተቀመጠበት ኮርቻ ሁሉ ርኩስ ይሆናል፤ 10ከበታቹ ያለውንም ነገር ሁሉ የነካ ማንም ሰው እስከ ማታ ድረስ ርኩስ ይሆናል። እነዚህንም ነገሮች የሚያነሣ ማንም ሰው ልብሱን ይጠብ፤ ሰውነቱንም በውሃ ይታጠብ፤ እስከ ማታ ድረስ ግን ርኩስ ይሆናል።

11“ ‘ፈሳሽ ነገር የሚወጣው ሰው እጁን በውሃ ሳይታጠብ ሌላውን ሰው ቢነካ፣ የተነካው ሰው ልብሱን ይጠብ፤ ሰውነቱንም በውሃ ይታጠብ፤ እስከ ማታ ድረስ ግን ርኩስ ይሆናል።

12“ ‘ፈሳሽ ነገር የሚወጣው ሰው የነካው የሸክላ ዕቃ ይሰበር፤ ከዕንጨት የተሠራ ዕቃ ከሆነ በውሃ ይታጠብ።

13“ ‘ፈሳሽ ነገር የሚወጣው ሰው ከፈሳሹ ሲነጻ፣ በሕጉ መሠረት ለመንጻቱ ሰባት ቀን ይቍጠር፤ ልብሱን ይጠብ፤ ሰውነቱንም በምንጭ ውሃ ይታጠብ፤ ንጹሕም ይሆናል። 14በስምንተኛውም ቀን ሁለት ርግቦች ወይም ሁለት የዋኖስ ጫጩቶች ይዞ በመገናኛው ድንኳን ደጃፍ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት በመቅረብ ለካህኑ ይስጥ። 15ካህኑም አንዱን ለኀጢአት መሥዋዕት፣ ሌላውንም ለሚቃጠል መሥዋዕት ያቅርብ፤ በዚህ መሠረት ስለ ፈሳሹ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ለሰውየው ያስተሰርይለታል።

16“ ‘አንድ ሰው ዘሩ በሚፈስስበት ጊዜ ሰውነቱን በሙሉ በውሃ ይታጠብ፤ እስከ ማታ ድረስ ግን ርኩስ ይሆናል። 17የፈሰሰው ዘር የነካው ማንኛውም ልብስ ወይም ቍርበት በውሃ ይታጠብ፤ እስከ ማታ ድረስ ግን ርኩስ ይሆናል። 18አንድ ሰው ከአንዲት ሴት ጋር ግብረ ሥጋ ፈጽሞ ዘር ቢፈስሰው፣ ሁለቱም በውሃ ይታጠቡ፤ እስከ ማታ ድረስ ግን ርኩሳን ይሆናሉ።

19“ ‘ሴት ጊዜውን እየጠበቀ የሚመጣው የደም መፍሰስ ቢኖርባት፣ የወር አበባዋ ርኩሰት እስከ ሰባት ቀን ይቈያል፤ በዚህ ጊዜ ማንም ሰው ቢነካት እስከ ማታ ድረስ ርኩስ ይሆናል።

20“ ‘በወር አበባዋ ጊዜ የምትተኛበት ማንኛውም ነገር ርኩስ ይሆናል፤ የተቀመጠችበትም ነገር ርኩስ ይሆናል። 21መኝታዋን የነካ ማንኛውም ሰው ልብሱን ይጠብ፤ ሰውነቱንም በውሃ ይታጠብ፤ እስከ ማታ ድረስ ግን ርኩስ ይሆናል። 22የተቀመጠችበትን ማንኛውንም ነገር የነካ ሰው ልብሱን ይጠብ፤ ሰውነቱንም በውሃ ይታጠብ፤ እስከ ማታ ድረስ ግን ርኩስ ይሆናል፤ 23መኝታዋን ወይም የተቀመጠችበትን ማንኛውንም ነገር የነካ ሰው እስከ ማታ ድረስ ርኩስ ይሆናል።

24“ ‘አንድ ሰው ከእርሷ ጋር ቢተኛና የወር አበባዋ ቢነካው፣ እስከ ሰባት ቀን ድረስ ርኩስ ይሆናል፤ እርሱ የሚተኛበት መኝታ ሁሉ ርኩስ ይሆናል።

25“ ‘ሴት ከወር አበባዋ ጊዜ ሌላ ብዙ ቀን ደም ቢፈስሳት፣ ወይም የወር አበባዋ ጊዜ ካለፈ በኋላ የደሙ መፍሰስ ባይቋረጥ፣ ልክ እንደ ወር አበባዋ ጊዜ፣ ደም መፍሰሱ እስኪቆም ድረስ ርኩስ ትሆናለች። 26ደሟ መፍሰሱን በቀጠለበት ጊዜ ሁሉ፣ የምትተኛበት ማንኛውም መኝታ ልክ በወር አበባዋ ጊዜ እንደ ነበረው መኝታ ርኩስ ይሆናል፤ የምትቀመጥበትም ማንኛውም ነገር ልክ እንደ ወር አበባዋ ጊዜ ርኩስ ይሆናል። 27እነዚህንም የሚነካ ማንኛውም ሰው ርኩስ ይሆናል፤ ልብሱን ይጠብ፤ ሰውነቱንም በውሃ ይታጠብ፤ እስከ ማታ ድረስ ግን ርኩስ ይሆናል።

28“ ‘ከደሟ ፍሳሽ ሳትነጻ ሰባት ቀን ትቍጠር፤ ከዚያም በኋላ በሥርዐቱ መሠረት ንጹሕ ትሆናለች። 29በስምንተኛውም ቀን ሁለት ርግቦች ወይም ሁለት የዋኖስ ጫጩቶች ይዛ በመቅረብ በመገናኛው ድንኳን ደጃፍ ለካህኑ ትሰጣለች። 30ካህኑም አንዱን ለኀጢአት መሥዋዕት፣ ሌላውንም ለሚቃጠል መሥዋዕት ያቅርብ፤ በዚህ መሠረት ስለ ፈሳሽዋ ርኩሰት በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ያስተሰርይላታል።

31“ ‘በመካከላቸው ያለችውን ማደሪያዬን15፥31 ወይም የመገናኛ ድንኳኔን እንዳያረክሱና በርኩሰታቸው እንዳይሞቱ፣ እስራኤላውያንን ከሚያረክሳቸው ነገር ለዩአቸው።’ ”

32ፈሳሽ ነገር የሚወጣውን፣ ዘሩም በመፍሰሱ ርኩስ የሆነውን ሰው ሁሉ፣ 33በወር አበባ ላይ ያለችን ሴት፣ ፈሳሽ ነገር የሚወጣቸውን ወንድ ወይም ሴት፣ በሥርዐቱ መሠረት ርኩስ ከሆነች ሴት ጋር የሚተኛውን ወንድ በሚመለከት ሕጉ ይኸው ነው።

Thai New Contemporary Bible

เลวีนิติ 15:1-33

สิ่งมลทินที่หลั่งออกจากร่างกาย

1องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสสั่งโมเสสกับอาโรนว่า 2“จงแจ้งประชากรอิสราเอลว่า ‘ชายใดมีสิ่งที่หลั่งออกมาจากร่างกาย สิ่งที่หลั่งออกมานั้นเป็นมลทิน 3ไม่ว่าสิ่งนั้นจะไหลออกมาหรือคั่งอยู่ก็ตามก็ทำให้เขาเป็นมลทิน สิ่งที่หลั่งออกจะทำให้เขาเป็นมลทินในกรณีต่อไปนี้คือ

4“ ‘ชายใดมีสิ่งที่หลั่งออกมา นอนที่เตียงใดหรือนั่งบนสิ่งใด สิ่งนั้นพลอยเป็นมลทินไปด้วย 5ใครก็ตามที่แตะต้องเตียงของเขาจะต้องซักเสื้อผ้าและอาบน้ำ เขาจะเป็นมลทินไปจนถึงเวลาเย็น 6ใครก็ตามนั่งบนที่นั่งของชายที่มีสิ่งที่หลั่งออก ผู้นั้นต้องซักเสื้อผ้าและอาบน้ำ และเขาจะเป็นมลทินจนถึงเวลาเย็น

7“ ‘ใครก็ตามที่สัมผัสชายผู้มีสิ่งที่หลั่งออก จะต้องซักเสื้อผ้าและอาบน้ำ และเขาจะเป็นมลทินจนถึงเวลาเย็น

8“ ‘หากชายผู้มีสิ่งที่หลั่งออกถ่มน้ำลายไปถูกคนที่สะอาด คนนั้นจะต้องซักเสื้อผ้าและอาบน้ำ และเขาจะเป็นมลทินจนถึงเวลาเย็น

9“ ‘เขานั่งบนอานใดๆ อานนั้นก็เป็นมลทิน 10ผู้ใดแตะต้องสิ่งที่เขานั่งทับ จะเป็นมลทินจนถึงเวลาเย็น ผู้ใดหยิบฉวยสิ่งเหล่านั้น จะต้องซักเสื้อผ้าและอาบน้ำ และเขาจะเป็นมลทินจนถึงเวลาเย็น

11“ ‘หากชายผู้มีสิ่งที่หลั่งออกถูกเนื้อต้องตัวผู้ใดโดยไม่ได้ล้างมือก่อน ผู้นั้นจะต้องซักเสื้อผ้าของตนและอาบน้ำ และเขาเป็นมลทินจนถึงเวลาเย็น

12“ ‘ถ้าผู้เป็นมลทินไปแตะต้องภาชนะดินเผา จะต้องทุบภาชนะนั้นทิ้ง ส่วนภาชนะไม้จะต้องล้างน้ำทุกใบ

13“ ‘เมื่อเขาปลอดจากสิ่งที่หลั่งออก ให้เขาคอยอยู่เจ็ดวัน เป็นการชำระตนให้สะอาดตามระเบียบพิธี เขาต้องซักเสื้อผ้าและอาบน้ำด้วยน้ำสะอาด แล้วเขาจะสะอาด 14ในวันที่แปดเขาต้องนำนกเขาหรือนกพิราบรุ่นสองตัวมาเข้าเฝ้าองค์พระผู้เป็นเจ้าตรงทางเข้าเต็นท์นัดพบ แล้วมอบนกให้แก่ปุโรหิต 15ปุโรหิตจะถวายนกตัวหนึ่งเป็นเครื่องบูชาไถ่บาป อีกตัวหนึ่งเป็นเครื่องเผาบูชา ปุโรหิตจะลบบาปให้ชายผู้นั้นที่มีสิ่งที่หลั่งออกด้วยวิธีนี้ต่อหน้าองค์พระผู้เป็นเจ้า

16“ ‘เมื่อชายคนใดหลั่งน้ำอสุจิ เขาจะต้องชำระทั้งร่างกายด้วยน้ำ และเป็นมลทินไปจนถึงเวลาเย็น 17ผ้าหรือหนังซึ่งเปื้อนน้ำอสุจิจะต้องนำไปซักล้างด้วยน้ำ และเป็นมลทินไปจนถึงเวลาเย็น 18เมื่อชายหญิงหลับนอนกันและมีการหลั่งน้ำอสุจิ ทั้งคู่จะต้องอาบน้ำและเป็นมลทินจนถึงเวลาเย็น

19“ ‘เมื่อผู้หญิงมีประจำเดือน จะอยู่ในระยะเป็นมลทินตลอดเจ็ดวัน ผู้ใดถูกเนื้อต้องตัวนาง จะเป็นมลทินไปจนถึงเวลาเย็น

20“ ‘ที่ซึ่งนางนอนหรือนั่งในช่วงที่นางมีประจำเดือนจะเป็นมลทิน 21ผู้ใดแตะต้องเตียงของนาง ต้องซักเสื้อผ้าและอาบน้ำ และเขาจะเป็นมลทินจนถึงเวลาเย็น 22ผู้ใดแตะต้องสิ่งที่นางนั่งทับ ต้องซักเสื้อผ้าและอาบน้ำ และเขาจะเป็นมลทินจนถึงเวลาเย็น 23ไม่ว่าจะเป็นเตียงหรือสิ่งที่นางนั่งทับ เมื่อผู้ใดไปแตะต้องสิ่งนั้น เขาจะเป็นมลทินจนถึงเวลาเย็น

24“ ‘ชายใดหลับนอนกับนางและสัมผัสประจำเดือนของนาง เขาจะเป็นมลทินไปเจ็ดวัน และเขานอนที่เตียงใด เตียงนั้นจะเป็นมลทิน

25“ ‘เมื่อผู้หญิงคนใดที่มีเลือดไหลออกเป็นเวลาหลายวัน นอกเหนือจากที่เป็นประจำเดือนปกติ หรือมีประจำเดือนหลายวันเกินกำหนด นางจะเป็นมลทินตราบเท่าที่นางมีเลือดไหลออกเหมือนอย่างวันที่นางมีประจำเดือน 26ในช่วงนั้นนางนอนที่ใด ที่นั่นก็เป็นมลทินเช่นเดียวกับเวลาที่นางมีประจำเดือนตามปกติ ทุกอย่างที่นางนั่งทับจะเป็นมลทินเช่นเดียวกัน 27ผู้ใดแตะต้องเตียงของนางหรือสิ่งที่นางนั่งทับจะเป็นมลทิน จะต้องซักเสื้อผ้าและอาบน้ำ และเป็นมลทินไปจนถึงเวลาเย็น

28“ ‘เมื่อนางได้รับการชำระจากสิ่งที่หลั่งออกมาแล้ว นางต้องนับต่อไปอีกเจ็ดวัน หลังจากนั้นนางจะสะอาดตามระเบียบพิธี 29ในวันที่แปดนางจะต้องนำนกเขาหรือนกพิราบรุ่นสองตัวมามอบแก่ปุโรหิตตรงทางเข้าเต็นท์นัดพบ 30ปุโรหิตจะถวายนกตัวหนึ่งเป็นเครื่องบูชาไถ่บาปและอีกตัวหนึ่งเป็นเครื่องเผาบูชา ปุโรหิตจะลบบาปให้นางโดยวิธีนี้ต่อหน้าองค์พระผู้เป็นเจ้าเนื่องด้วยสิ่งที่หลั่งออกที่เป็นมลทินของนาง

31“ ‘เจ้าจะต้องแยกชนอิสราเอลทั้งหลายออกจากสิ่งที่ทำให้เขาเป็นมลทิน เพื่อเขาจะไม่ตายด้วยมลทินของเขาที่ทำให้ที่ประทับ15:31 หรือพลับพลาของเราซึ่งอยู่ท่ามกลางพวกเขานั้นเป็นมลทิน’ ”

32ทั้งหมดนี้คือกฎระเบียบสำหรับผู้ชายที่เป็นมลทินเนื่องจากสิ่งที่หลั่งออกหรือหลั่งอสุจิ 33และสำหรับผู้หญิงที่อยู่ในช่วงมีประจำเดือน และสำหรับผู้ชายหรือผู้หญิงที่มีสิ่งที่หลั่งออก และสำหรับผู้ชายที่หลับนอนกับผู้หญิงที่เป็นมลทินตามระเบียบพิธี