ዕዝራ 4 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

ዕዝራ 4:1-24

ቤተ መቅደሱ እንዳይሠራ የተነሣ ተቃውሞ

1የይሁዳና የብንያም ጠላቶች ከምርኮ የተመለሱት ሰዎች የእስራኤልን አምላክ የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ በመሥራት ላይ መሆናቸውን ሲሰሙ፣ 2ወደ ዘሩባቤልና ወደ ቤተ ሰቡ አለቆች መጥተው፣ “እኛም እንደ እናንተ አምላካችሁን የምንፈልግ ነን፤ የአሦር ንጉሥ አስራዶን ወደዚህ ካመጣን ጊዜ ጀምሮ ለእርሱ ስንሠዋለት ቈይተናል፤ ስለዚህ አብረን ከእናንተ ጋር እንሥራ” አሏቸው።

3ዘሩባቤል፣ ኢያሱና ሌሎቹ የእስራኤል ቤተ ሰቦች አለቆች ግን፣ “ለአምላካችን ቤተ መቅደስ እንድትሠሩ ከእኛ ጋር የሚያገናኛችሁ ምንም ነገር የለም። የፋርስ ንጉሥ ቂሮስ ባዘዘን መሠረት ለእስራኤል አምላክ ለእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ የምንሠራው እኛ ብቻ ነን” ሲሉ መለሱላቸው።

4ከዚያም የምድሪቱ ነዋሪዎች የይሁዳን ሕዝብ ተስፋ ማስቈረጥና ሥራውንም እንዳይቀጥሉ ማስፈራራት ጀመሩ4፥4 ወይም፣ ቤተ መቅድሱን ለመሥራት ሲነሡ አወኳቸው።5ከፋርስ ንጉሥ ከቂሮስ ዘመነ መንግሥት ጀምሮ እስከ ፋርስ ንጉሥ እስከ ዳርዮስ ዘመነ መንግሥት ድረስ ዕቅዶቻቸውን የሚያሰናክሉ መካሪዎችን በገንዘብ ገዙባቸው።

በጠረክሲስና በአርጤክስስ ዘመን የተደረገ ሌላው ተቃውሞ

6በጠረክሲስ ዘመነ መንግሥት መጀመሪያ በይሁዳና በኢየሩሳሌም ነዋሪዎች ላይ የጽሑፍ ክስ መሠረቱባቸው።

7በፋርስ ንጉሥ በአርጤክስስ ዘመን ቢሽላም፣ ሚትሪዳጡ፣ ጣብኤልና ተባባሪዎቹ ወደ አርጤክስስ ደብዳቤ ጻፉ። ደብዳቤው የተጻፈው በአረማይክ ፊደል፣ በአረማይክ ቋንቋ ነበረ4፥7 ወይም፣ በአረማይክ ቋንቋ ተጽፎ በዚያው ቋንቋ የተተረጐመዕዝ 4፥8–6፥18 ያለው ክፍል የተጻፈው በአረማይክ ቋንቋ ነው።

8አገረ ገዥው ሬሁምና ጸሓፊው ሲምሳይ በኢየሩሳሌም ላይ ለንጉሡ ለአርጤክስስ እንዲህ የሚል ደብዳቤ ጻፉ፤

9ደብዳቤው የተጻፈው፣ ከአገረ ገዥው ሬሁም፣ ከጸሓፊው ሲምሳይ በትሪፖሊስ፣ በፋርስ፣ በአርክ፣ በባቢሎን እንዲሁም በሱሳ ማለትም በኤላማውያን ላይ ዳኞችና ገዦች ከሆኑት ከተባባሪዎቻቸው፣ 10ደግሞም ታላቁና ኀያሉ አስናፈር4፥10 በአረማይክ ቋንቋ “አሹርባኒጳል” ማለት ነው። አፍልሶ በሰማርያ ከተማና ከኤፍራጥስ ወንዝ ማዶ እንዲሰፍሩ ካደረጋቸው ሌሎች ሕዝቦች ነው።

11የላኩለት ደብዳቤ ቅጅ ይህ ነው፤

ለንጉሥ አርጤክስስ፣

በኤፍራጥስ ወንዝ ማዶ ከሚኖሩት አገልጋዮችህ የተላከ፤

12ከአንተ ዘንድ ወደ እኛ የመጡት አይሁዳውያን ወደ ኢየሩሳሌም በመሄድ ዐመፀኛና ርኩስ ከተማ እንደ ገና በመሥራት ላይ ናቸው፤ ቅጥሮቿንም እንደ ገና በመሥራትና መሠረቶቿንም በመጠገን ላይ መሆናቸው በንጉሡ ዘንድ የታወቀ ይሁን።

13ከዚህም በላይ ይህች ከተማ ከተሠራች፣ ቅጥሮቿም እንደ ገና ከተገነቡ፣ ቀረጥና እጅ መንሻ ወይም ግብር እንደማይከፍሉ፣ የቤተ መንግሥቱም ገቢ እንደሚቀንስ በንጉሡ ዘንድ የታወቀ ይሁን። 14አሁንም እኛ ስለ ቤተ መንግሥቱ ስለሚገደን፣ የንጉሡም ክብር ሲነካ ዝም ብሎ ማየት ተገቢ ሆኖ ስላላገኘነው፣ ይህ ነገር በንጉሡ ዘንድ የታወቀ እንዲሆን ይህን መልእክት ልከናል፤ 15ስለዚህ በአባቶችህ ቤተ መዛግብት ምርመራ ይደረግ፤ በእነዚህ መዛግብት ውስጥ ይህች ከተማ ዐመፀኛ ከተማ እንደ ሆነች፣ ነገሥታትንና አውራጃዎችን የጐዳችና ከጥንት ጀምሮ የዐመፅ ጐሬ ስለ መሆኗ ማስረጃ ታገኛለህ፤ እንግዲህ ከተማዪቱ የተደመሰሰችው በዚህ ምክንያት ነው። 16ይህች ከተማ ተመልሳ የምትሠራና ቅጥሮቿም እንደ ገና የሚገነቡ ከሆነ፣ ከኤፍራጥስ ማዶ ምንም ነገር እንደማይኖርህ፣ ንጉሥ ታውቅ ዘንድ እንወድዳለን።

17ንጉሡም ይህን መልስ ላከ፤

ለአገረ ገዥው ሬሁም፣ ለጸሓፊው ሲምሳይ፣ በሰማርያና በኤፍራጥስ ማዶ ለሚኖሩ ተባባሪዎቻቸው፤

ሰላም ለእናንተ ይሁን፤

18የላካችሁልኝ ደብዳቤ በፊቴ ተተርጕሞ ተነብቧል። 19እኔም ትእዛዝ ሰጥቼ ምርመራ ተደርጓል፤ በምርመራውም መሠረት ይህች ከተማ ከጥንት ጀምሮ በነገሥታት ላይ ስታምፅ የኖረች የዐመፅና የወንጀል መናኸሪያ እንደ ሆነች ማስረጃ ተገኝቷል። 20ኢየሩሳሌም ከኤፍራጥስ ማዶ ያለውን አገር ሁሉ የገዙ፣ ቀረጥ፣ ግብርና እጅ መንሻም ይቀበሉ የነበሩ ኀያላን ነገሥታት ነበሯት። 21አሁንም እኔ ትእዛዝ እስከምሰጥበት ድረስ ይህች ከተማ እንደ ገና እንዳትሠራ ሥራውን ያቆሙ ዘንድ ለእነዚህ ሰዎች ትእዛዝ አስተላልፉ።

22ይህን ነገር ቸል እንዳትሉ ተጠንቀቁ፤ በነገሥታቱ ላይ የሚደርሰው ኪሳራ ለምን እየበዛ ይሄዳል?

23የንጉሡ የአርጤክስስ ደብዳቤ ቅጅ በሬሁም፣ በጸሓፊው በሲምሳይና በተባባሪዎቻቸው ፊት እንደ ተነበበ፣ ወዲያውኑ በኢየሩሳሌም ወደሚገኙት አይሁድ ሄደው ሥራውን እንዲያቆሙ አስገደዷቸው።

24ስለዚህም በኢየሩሳሌም የሚሠራው የእግዚአብሔር ቤት ሥራ እስከ ፋርስ ንጉሥ እስከ ዳርዮስ ዘመነ መንግሥት ሁለተኛ ዓመት ድረስ ተቋረጠ።

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

以斯拉记 4:1-24

建殿工作受阻

1犹大便雅悯的敌人听说流亡者回来要为以色列的上帝耶和华建殿, 2就去见所罗巴伯以色列的族长,对他们说:“请让我们与你们一同建造,因为我们像你们一样也寻求你们的上帝。自从亚述以撒哈顿带我们到这里以后,我们就一直献祭给上帝。” 3所罗巴伯耶书亚以色列其余的族长回答说:“你们不能参与建殿。遵照波斯塞鲁士的吩咐,我们要自己为以色列的上帝耶和华建殿。”

4于是,当地人阻挠犹大人,使他们不敢建殿, 5波斯塞鲁士统治年间,一直到波斯大流士统治期间,当地人收买谋士,破坏他们的计划。

阻扰重建耶路撒冷

6亚哈随鲁统治初期,他们写信控告犹大耶路撒冷的居民。

7波斯亚达薛西统治年间,比施兰米特利达他别及其同党上奏亚达薛西。奏章是用亚兰文写的,经过翻译后呈上。 8利宏省长和伸帅书记也写了奏本给亚达薛西王,控告耶路撒冷人,内容如下: 9利宏省长、伸帅书记和我们的同僚底拿人、亚法萨提迦人、他毗拉人、亚法撒人、亚基卫人、巴比伦人、书珊迦人、底亥人、以拦人, 10以及伟大尊贵的亚斯那巴迁来并安置在撒玛利亚各城与幼发拉底河西一带的人民, 11上奏亚达薛西王,

“‘幼发拉底河西的臣民奏告亚达薛西王, 12王该知道,从王那里到我们这里来的犹太人已经去了耶路撒冷,如今正在重建这座叛逆、罪恶之城,正在重建地基,修筑城墙。 13王该知道,如果这城建好,城墙完工,他们将不再进贡、交赋、纳税,王的税收必受亏损。 14我们既食王禄,就不能坐视王遭受损失,因此上奏于王。 15请王查看先王的记录,必从中获悉这城是叛逆之城,危害列王和各省。自古以来,城中叛乱不断,因此才被毁灭。 16我们愿王知道,这城一旦建好,城墙完工,幼发拉底河西之地就不再为王所有了。’”

17王回复利宏省长、伸帅书记及其住在撒玛利亚幼发拉底河西一带的同僚,说:“愿你们平安! 18你们呈上的奏章,经过翻译已奏报给我。 19我已命人查考,发现这城自古以来屡屡背叛列王,是悖逆和叛乱之地。 20强大的君王曾经统管耶路撒冷幼发拉底河西全境,并向人们征收贡物和赋税。 21现在你们要下令让这些人停止建造这城,等候我的谕旨。 22要认真办理这事,不可迟延,何必容事情恶化,使王受亏损呢?”

23利宏伸帅书记及其同僚接到谕旨后,急忙赶往耶路撒冷,用武力强迫犹太人停工。

恢复建殿工作

24于是,耶路撒冷上帝殿的重建工程停止了,一直停到波斯大流士第二年。