ዕንባቆም 3 – NASV & NIV

New Amharic Standard Version

ዕንባቆም 3:1-19

የዕንባቆም ጸሎት

1በዝማሬ የቀረበ የነቢዩ የዕንባቆም ጸሎት፤ በሺግዮኖት።3፥1 የሥነ ጽሑፍ ወይም የሙዚቃ ቋንቋ ሳይሆን አይቀርም።

2እግዚአብሔር ሆይ፤ ዝናህን ሰምቻለሁ፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ ሥራህም አስፈራኝ፤

በእኛ ዘመን አድሳቸው፤

በእኛም ጊዜ እንዲታወቁ አድርግ፤

በመዓት ጊዜ ምሕረትን ዐስብ።

3እግዚአብሔር ከቴማን፣

ቅዱሱም ከፋራን ተራራ መጣ። ሴላ3፥3 ትርጕሙ በትክክል የማይታወቅ ቢሆንም የዜማ ቃል ሳይሆን አይቀርም።

ክብሩ ሰማያትን ሸፈነ፤

ውዳሴውም ምድርን ሞላ።

4ጸዳሉ እንደ ፀሓይ ብርሃን ነው፤

ጨረር ከእጁ ወጣ፤

ኀይሉም በዚያ ተሰውሯል።

5መቅሠፍት በፊቱ ሄደ፤

ቸነፈርም እግር በእግር ተከተለው።

6ቆመ፤ ምድርን አንቀጠቀጠ፤

ተመለከተ፤ ሕዝቦችን አብረከረከ፤

የዘላለም ተራሮች ተፈረካከሱ፤

የጥንት ኰረብቶችም ፈራረሱ፤

መንገዱ ዘላለማዊ ነው።

7የኢትዮጵያ ድንኳኖች ሲጨነቁ፣

የምድያምም መኖሪያዎች ሲታወኩ አየሁ።

8እግዚአብሔር ሆይ፤ በወንዞች ላይ ተቈጣህን?

መዓትህስ በምንጮች ላይ ነበርን?

በፈረሶችህና በድል አድራጊ ሠረገሎችህ

በጋለብህ ጊዜ፣

በባሕር ላይ ተቈጥተህ ነበርን?

9ቀስትህን አዘጋጀህ፤

ፍላጻም እንዲመጣልህ አዘዝህ፤ ሴላ

ምድርን በወንዞች ከፈልህ፤

10ተራሮች አዩህ፤ ተጨነቁም፤

የውሃ ሞገድ ዐልፎ ሄደ፤

ቀላዩ ደነፋ፤

ማዕበሉንም ወደ ላይ አነሣ።

11ከሚወረወሩ ፍላጾችህ፣

ከሚያብረቀርቅ የጦርህ ነጸብራቅ የተነሣም፣

ፀሓይና ጨረቃ በቦታቸው ቆሙ።

12በምድር ላይ በመዓት ተመላለስህ፤

ሕዝቦችንም በቍጣ ረገጥሃቸው።

13ሕዝብህን ለመታደግ፣

የቀባኸውንም ለማዳን ወጣህ፤

የክፋትን ምድር መሪ ቀጠቀጥህ፤

ከራስ ጠጕሩ እስከ እግር ጥፍሩም ዕርቃኑን አስቀረኸው። ሴላ

14እንደ ዐውሎ ነፋስ ሊበታትነን የመጣውን፣

ምስኪኑን በስውር በመዋጥ የሚደሰተውን፣

የሰራዊት አለቃ ራስ፣

በገዛ ጦሩ ወጋህ።

15ታላላቅ ውሆችን በመናጥ፣

ባሕሩን በፈረሶችህ ረገጥህ።

16እኔ ሰማሁ፤ ልቤም ደነገጠብኝ፤

ከንፈሬ ከድምፁ የተነሣ ተንቀጠቀጠ፤

ፍርሀት እስከ ዐጥንቴ ዘልቆ ገባ፤

እግሬም ተብረከረከ፤

ሆኖም በሚወርረን ሕዝብ ላይ እስኪመጣ ድረስ፣

የጥፋትን ቀን በትዕግሥት እጠባበቃለሁ።

17ምንም እንኳ የበለስ ዛፍ ባያፈራ፣

ከወይን ተክልም ፍሬ ባይገኝ፣

የወይራም ዛፍ ፍሬ ባይሰጥ፣

ዕርሻዎችም ሰብል ባይሰጡ፣

የበጎች ጕረኖ እንኳ ባዶውን ቢቀር፣

ላሞችም በበረት ውስጥ ባይገኙ፣

18እኔ ግን በእግዚአብሔር ደስ ይለኛል፤

በድነቴ አምላክ ሐሤት አደርጋለሁ።

19ጌታ እግዚአብሔር ኀይሌ ነው፤

እግሮቼን እንደ ዋላ እግሮች ያደርጋል፤

በከፍታዎችም ላይ ያስሄደኛል።

ለመዘምራን አለቃ፣ በባለ አውታር መሣሪያዎቼ የተዘመረ መዝሙር።

New International Version

Habakkuk 3:1-19

Habakkuk’s Prayer

1A prayer of Habakkuk the prophet. On shigionoth.3:1 Probably a literary or musical term

2Lord, I have heard of your fame;

I stand in awe of your deeds, Lord.

Repeat them in our day,

in our time make them known;

in wrath remember mercy.

3God came from Teman,

the Holy One from Mount Paran.3:3 The Hebrew has Selah (a word of uncertain meaning) here and at the middle of verse 9 and at the end of verse 13.

His glory covered the heavens

and his praise filled the earth.

4His splendor was like the sunrise;

rays flashed from his hand,

where his power was hidden.

5Plague went before him;

pestilence followed his steps.

6He stood, and shook the earth;

he looked, and made the nations tremble.

The ancient mountains crumbled

and the age-old hills collapsed—

but he marches on forever.

7I saw the tents of Cushan in distress,

the dwellings of Midian in anguish.

8Were you angry with the rivers, Lord?

Was your wrath against the streams?

Did you rage against the sea

when you rode your horses

and your chariots to victory?

9You uncovered your bow,

you called for many arrows.

You split the earth with rivers;

10the mountains saw you and writhed.

Torrents of water swept by;

the deep roared

and lifted its waves on high.

11Sun and moon stood still in the heavens

at the glint of your flying arrows,

at the lightning of your flashing spear.

12In wrath you strode through the earth

and in anger you threshed the nations.

13You came out to deliver your people,

to save your anointed one.

You crushed the leader of the land of wickedness,

you stripped him from head to foot.

14With his own spear you pierced his head

when his warriors stormed out to scatter us,

gloating as though about to devour

the wretched who were in hiding.

15You trampled the sea with your horses,

churning the great waters.

16I heard and my heart pounded,

my lips quivered at the sound;

decay crept into my bones,

and my legs trembled.

Yet I will wait patiently for the day of calamity

to come on the nation invading us.

17Though the fig tree does not bud

and there are no grapes on the vines,

though the olive crop fails

and the fields produce no food,

though there are no sheep in the pen

and no cattle in the stalls,

18yet I will rejoice in the Lord,

I will be joyful in God my Savior.

19The Sovereign Lord is my strength;

he makes my feet like the feet of a deer,

he enables me to tread on the heights.

For the director of music. On my stringed instruments.