ዕንባቆም 2 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዕንባቆም 2:1-20

1በመጠበቂያዬ ላይ እቆማለሁ፤

በምሽጉ ቅጥር ላይ ወጥቼ እቈያለሁ፤

ምን እንደሚለኝ፣

ለክርክሩም2፥1 ወይም በተገሠጽሁ ጊዜ የምሰጠውን ምላሽ የምሰጠውን መልስ ለማወቅ እጠባበቃለሁ።

የእግዚአብሔር መልስ

2እግዚአብሔርም እንዲህ ሲል መለሰ፤

“በቀላሉ እንዲነበብ፣

ራእዩን ጻፈው፤

በሰሌዳም ላይ ቅረጸው።

3ራእዩ የተወሰነለትን ጊዜ ይጠብቃልና፤

ስለ መጨረሻውም ይናገራል፤

እርሱም አይዋሽም፤

የሚዘገይ ቢመስልም ጠብቀው፤

በርግጥ ይመጣል2፥3 የሚመጣ ሰው እንዳለ የሚያመለክቱ አሉ።፤ ከቶም አይዘገይም።

4“እነሆ፤ እርሱ ታብዮአል፤

ምኞቱ ቀና አይደለም፤

ጻድቅ ግን በእምነት2፥4 በታማኝነቱ የሚሉ አሉ። ይኖራል።

5በርግጥ የወይን ጠጅ አታልሎታል፤

ትዕቢተኛ ነው፤ ከቶ አያርፍም፤

እንደ ሲኦል2፥5 መቃብር የሚሉ አሉ። ስስታም ነው፣

እንደ ሞት ከቶ አይጠግብም፤

ሕዝቦችን ለራሱ ይሰበስባል፤

ሰዎችንም ሁሉ ማርኮ ይወስዳል።

6“ታዲያ በእንደዚህ ዐይነቱ ሰው ላይ በማፌዝና በመዘበት እንዲህ እያሉ ሁሉም አይሣለቁበትምን?

“ ‘የተሰረቀውን ሸቀጥ ለራሱ ለሚያከማች፣

ራሱን በዐመፅ ባለጠጋ ለሚያደርግ ወዮለት!

ይህ የሚቀጥለውስ እስከ መቼ ነው?’

7ባለ ዕዳ ያደረግሃቸው ድንገት አይነሡብህምን?

ነቅተውስ አያስደነግጡህምን?

በእጃቸውም ትወድቃለህ።

8አንተ ብዙ ሕዝብ ስለ ዘረፍህ፣

የተረፉት ሕዝቦች ይዘርፉሃል፤

የሰው ደም አፍስሰሃልና፤

አገሮችንና ከተሞችን፣ በውስጣቸው የሚኖሩትን ሁሉ አጥፍተሃል።

9“በተጭበረበረ ትርፍ መኖሪያውን ለሚገነባ፣

ከጠላት እጅ ለማምለጥ፣

ቤቱን በከፍታ ላይ ለሚሠራ ወዮለት!

10የብዙ ሰዎች ነፍስ እንዲጠፋ አሢረሃል፤

በገዛ ቤትህ ላይ ውርደትን፣ በራስህም ላይ ጥፋትን አምጥተሃል።

11ድንጋይ ከቅጥሩ ውስጥ ይጮኻል፤

ከዕንጨት የተሠሩ ተሸካሚዎችም ይመልሱለታል።

12“ከተማን ደም በማፍሰስ ለሚሠራ፣

በወንጀልም ለሚመሠርታት ወዮለት።

13ሰዎች፣ ለእሳት ማገዶ እንዲሆን እንዲለፉ፣

ሕዝቦችም በከንቱ እንዲደክሙ፣

እግዚአብሔር ጸባኦት ወስኖ የለምን?

14ውሃ ባሕርን እንደሚሸፍን ሁሉ፣

ምድርም የእግዚአብሔርን ክብር በማወቅ ትሞላለችና።

15“ኀፍረተ ሥጋቸውን ለማየት፣

ባልንጀሮቹን ለሚያጠጣ፣

እስኪሰክሩም ድረስ ወይን ለሚቀዳላቸው ወዮለት!

16በክብር ፈንታ ዕፍረት ትሞላለህ፤

አሁን ደግሞ ተራው የአንተ ነውና፤ ጠጣ፤ ኀፍረተ ሥጋህም ይገለጥ፤

በእግዚአብሔር ቀኝ እጅ ያለው ጽዋ ይመለስብሃል፤

ክብርህንም ውርደት ይሸፍነዋል።

17በሊባኖስ ላይ የሠራኸው ግፍ ያጥለቀልቅሃል፤

እንስሳቱን ማጥፋትህም ያስደነግጥሃል፤

የሰው ደም አፍስሰሃልና፤

አገሮችንና ከተሞችን በውስጣቸው የሚኖሩትንም ሁሉ አጥፍተሃልና።

18“የሰው እጅ የቀረጸው ጣዖት፣

ሐሰትንም የሚናገር ምስል ምን ፋይዳ አለው?

ሠሪው በገዛ እጁ ሥራ ይታመናልና፣

መናገር የማይችሉ ጣዖታትን ይሠራልና።

19ዕንጨቱን፣ ‘ንቃ!’

ሕይወት የሌለውንም ድንጋይ፣ ‘ተነሣ!’ ለሚል ወዮለት፤

በውኑ ማስተማር ይችላልን?

እነሆ፤ በወርቅና በብር ተለብጧል፤

እስትንፋስም የለውም።”

20እግዚአብሔር ግን በተቀደሰ መቅደሱ አለ፣

ምድር ሁሉ በፊቱ ጸጥ ትበል።

Thai New Contemporary Bible

ฮาบากุก 2:1-20

1ข้าพเจ้าจะยืนเฝ้ายาม

และประจำการบนเชิงเทิน

ข้าพเจ้าจะคอยดูว่าพระองค์จะตรัสประการใดแก่ข้าพเจ้า

และข้าพเจ้าจะตอบคำร้องทุกข์นี้อย่างไร2:1 หรือและจะตอบประการใด เมื่อข้าพเจ้าถูกตำหนิ

คำตอบขององค์พระผู้เป็นเจ้า

2แล้วองค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสตอบว่า

“จงเขียนสิ่งที่เราเปิดเผยแก่เจ้า

ให้เห็นชัดเจนบนแผ่นจารึก

เพื่อว่าทุกคนที่อ่านจะเข้าใจได้ทันที2:2 หรือผู้นำสารจะได้นำวิ่งไป

3เพราะสิ่งที่เราจะเปิดเผยแก่เจ้านั้นยังรอกำหนดเวลาอยู่

เป็นเรื่องวาระสุดท้าย

และจะพิสูจน์ได้ว่าไม่ใช่เรื่องเท็จ

แม้จะเนิ่นช้าอยู่ ก็จงอดใจรอ

มันจะมาถึงอย่างแน่นอนและจะไม่ล่าช้า2:3 หรือถึงแม้พระองค์จะเนิ่นช้าอยู่ ก็จงอดใจรอ / พระองค์จะมาถึงอย่างแน่นอนและจะไม่ล่าช้า

4“ดูเถิด เขาผยองขึ้น

ความปรารถนาของเขาไม่ถูกทำนองคลองธรรม

แต่คนชอบธรรมจะดำรงชีวิตโดยความเชื่อ2:4 หรือความซื่อสัตย์ของเขา

5อันที่จริงเหล้าองุ่นทรยศเขา

เขาหยิ่งผยองและไม่เคยพักสงบ

เพราะเขาตะกละเหมือนหลุมฝังศพ

และเหมือนความตายซึ่งไม่เคยอิ่ม

เขารวบรวมประชาชาติมาเป็นของตน

และจับชนชาติทั้งปวงมาเป็นเชลย

6“คนเหล่านั้นทั้งหมดจะไม่ร้องยั่วเย้าเขาด้วยคำเยาะเย้ยและคำสบประมาทหรอกหรือว่า

“ ‘วิบัติแก่เขาผู้เอาของที่ขโมยมากองสุมไว้

และทำให้ตนเองร่ำรวยโดยการขู่กรรโชก!

สิ่งนี้จะต้องดำเนินไปอีกนานเพียงใด?’

7เจ้าหนี้ของเจ้าจะไม่ลุกฮือขึ้นในทันทีทันใดหรือ?

เขาจะไม่ตื่นขึ้นและทำให้เจ้าตัวสั่นงันงกหรือ?

เมื่อนั้นเจ้าจะตกเป็นเหยื่อของเขา

8เพราะเจ้าได้ปล้นชิงมาหลายชาติ

ชนชาติที่เหลืออยู่จะปล้นเจ้า

เพราะเจ้าทำให้คนต้องหลั่งเลือด

เจ้าได้ทำลายดินแดนและเมืองต่างๆ ตลอดจนทุกคนในนั้น

9“วิบัติแก่เขาผู้สร้างอาณาจักรของตนด้วยสิ่งที่ได้มาอย่างอยุติธรรม

เพื่อสร้างรังไว้บนที่สูง

เพื่อหนีจากเงื้อมมือแห่งหายนะ!

10เจ้าวางแผนให้หลายชนชาติถูกทำลาย

ก่อความอัปยศแก่เรือนของเจ้าเองและทำให้ชีวิตของตนเองต้องเสียไป

11ก้อนหินที่ผนังจะส่งเสียงร้อง

และไม้ขื่อไม้คานก็จะส่งเสียงสะท้อน

12“วิบัติแก่ผู้สร้างนครด้วยการนองเลือด

และตั้งเมืองด้วยอาชญากรรม!

13พระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์ได้ทรงตัดสินพระทัยไว้แล้วไม่ใช่หรือว่า

การลงแรงทำงานของชนชาตินั้นก็เป็นเพียงเชื้อไฟ

การตรากตรำจนสิ้นแรงของชนชาติต่างๆ ก็สูญเปล่า?

14เพราะโลกจะเต็มไปด้วยความรู้ถึงพระเกียรติสิริขององค์พระผู้เป็นเจ้า

ดั่งห้วงนํ้าทั้งหลายที่ปกคลุมท้องทะเล

15“วิบัติแก่ผู้ที่ให้เหล้าองุ่นเพื่อนบ้านดื่ม

เทเหล้าจากถุงหนังให้เขาจนเมามาย

เพื่อจะได้จ้องดูร่างเปลือยเปล่าของเขา

16เจ้าจะเต็มไปด้วยความอับอายแทนที่จะได้เกียรติยศ

บัดนี้ถึงคราวของเจ้า! จงดื่มสิ และเจ้าจะถูกเปิดเผยความเปลือยเปล่า2:16 หรือและโซซัดโซเซไป!

ถ้วยจากพระหัตถ์ขวาขององค์พระผู้เป็นเจ้ากำลังเวียนมาถึงเจ้า

แล้วความอัปยศอดสูจะบดบังเกียรติยศของเจ้า

17ความโหดร้ายที่เจ้าทำไว้แก่เลบานอนจะล้มล้างเจ้า

และการที่เจ้าทำลายล้างสัตว์ต่างๆ จะทำให้เจ้าหวาดกลัว

เพราะเจ้าทำให้คนต้องหลั่งเลือด

เจ้าได้ทำลายดินแดนและเมืองต่างๆ ตลอดจนทุกคนในนั้น

18“รูปเคารพมีคุณค่าอะไรในเมื่อมนุษย์เป็นผู้แกะสลักมันขึ้น?

หรือรูปที่สอนความเท็จนั้นมีคุณค่าอะไร?

เพราะผู้ที่สร้างรูปนั้นขึ้นก็วางใจในสิ่งที่ตนสร้าง

เขาสร้างรูปเคารพที่พูดไม่ได้

19วิบัติแก่ผู้ที่กล่าวกับไม้ว่า ‘จงมีชีวิตขึ้นมาเถิด!’

หรือกล่าวแก่หินไร้ชีวิตว่า ‘จงตื่นขึ้นมาเถิด!’

มันจะให้คำแนะนำได้หรือ?

เขาหุ้มมันด้วยทองและเงิน

มันไม่มีลมหายใจ”

20แต่องค์พระผู้เป็นเจ้าประทับในพระวิหารศักดิ์สิทธิ์ของพระองค์

ให้ทั้งโลกจงเงียบอยู่ต่อหน้าพระองค์