ዕብራውያን 7 – NASV & CRO

New Amharic Standard Version

ዕብራውያን 7:1-28

ካህኑ መልከጼዴቅ

1ይህ መልከጼዴቅ የሳሌም ንጉሥና የልዑል እግዚአብሔር ካህን ነበር፤ እርሱም አብርሃም ነገሥታትን ድል አድርጎ ሲመለስ አግኝቶት ባረከው፤ 2አብርሃምም ከሁሉ ነገር ዐሥራት አውጥቶ ሰጠው። በመጀመሪያ ስሙ “የጽድቅ ንጉሥ” ማለት ነው፤ ኋላም ደግሞ “የሳሌም ንጉሥ” ማለትም “የሰላም ንጉሥ ማለት” ነው። 3አባትና እናት ወይም የትውልድ ሐረግ የለውም፤ ለዘመኑ መጀመሪያ፣ ለሕይወቱም ፍጻሜ የለውም፤ ነገር ግን እንደ እግዚአብሔር ልጅ ለዘላለም ካህን ሆኖ ይኖራል።

4እስቲ እርሱ የቱን ያህል ታላቅ እንደ ሆነ አስቡ፤ ርእሰ አበው የሆነው አብርሃም እንኳ ካገኘው ምርኮ ዐሥራት አውጥቶ ሰጠው። 5ክህነት የተሰጣቸው የሌዊ ልጆች ምንም እንኳ ወንድሞቻቸው የአብርሃም ዘሮች ቢሆኑም፣ ከሕዝቡ ማለት ከገዛ ወንድሞቻቸው ዐሥራት እንዲቀበሉ ሕጉ ያዝዛል። 6ይህ ግን ትውልዱ ከሌዊ ወገን አይደለም፤ ይሁን እንጂ ከአብርሃም ዐሥራት ተቀበለ፤ የተስፋ ቃል የተቀበለውንም ባረከው። 7ትንሹ በትልቁ እንደሚባረክ ጥርጥር የለውም። 8በአንድ በኩል ዐሥራት የሚቀበሉት ሟች ሰዎች ናቸው፤ በሌላ በኩል ግን ሕያው ሆኖ እንደሚኖር የተመሰከረለት ይቀበላል። 9እንዲያውም ዐሥራት የሚቀበለው ሌዊ፣ ራሱ በአብርሃም በኩል ዐሥራት ከፍሏል ማለት ይቻላል፤ 10ምክንያቱም መልከጼዴቅ አብርሃምን ባገኘው ጊዜ፣ ሌዊ ገና በአባቱ በአብርሃም አብራክ ነበር።

ኢየሱስ እንደ መልከጼዴቅ

11ፍጹምነት የተገኘውና ሕጉ ለሕዝቡ የተሰጠው በሌዊ ክህነት መሠረት ቢሆን ኖሮ፣ እንደ አሮን ሳይሆን እንደ መልከጼዴቅ ሹመት ያለው ሌላ ካህን መምጣቱ ለምን አስፈለገ? 12የክህነት ለውጥ ካለ ሕጉም ሊለወጥ ግድ ነውና። 13ይህ ሁሉ የተነገረለት እርሱ ከሌላ ነገድ ነው፤ ከዚያም ነገድ በመሠዊያ ያገለገለ ማንም የለም። 14ጌታችን ከይሁዳ ነገድ እንደ መጣ ግልጽ ነውና፤ ሙሴ ስለ ካህናት ሲናገር ይህን ነገድ አስመልክቶ የተናገረው ምንም ነገር የለም። 15እንደ መልከጼዴቅ ያለ ሌላ ካህን ቢነሣ ግን እኛ የተናገርነው ይበልጥ ግልጽ ይሆናል፤ 16እርሱ ካህን የሆነው በማይጠፋ የሕይወት ኀይል መሠረት እንጂ፣ እንደ ትውልዱ የሕግ ሥርዐት አይደለም፤ 17እንዲህ ተብሎ ተመስክሮለታል፤

“እንደ መልከጼዴቅ ሹመት፣

አንተ ለዘላለም ካህን ነህ።”

18የቀድሞው ትእዛዝ ደካማና የማይጠቅም በመሆኑ ተሽሯል፤ 19ሕጉ ማንንም ፍጹም ሊያደርግ ስለማይችል፣ ወደ እግዚአብሔር የምንቀርብበት የተሻለ ተስፋ መጥቷል።

20ይህ ያለ መሐላ አልሆነም፤ ሌሎች ካህናት የሆኑት ያለ መሐላ ነው፤ 21እርሱ ግን ካህን የሆነው በመሐላ ነው፤ ምክንያቱም እግዚአብሔር እንዲህ ብሎ ተናግሮለታል፤

“ጌታ ማለ፤

አሳቡንም አይለውጥም፤

‘አንተ ለዘላለም ካህን ነህ።’ ”

22ከዚህ መሐላ የተነሣ፣ ኢየሱስ ለተሻለ ኪዳን ዋስ ሆኗል።

23በአገልግሎታቸው እንዳይቀጥሉ ሞት ስለ ከለከላቸው፣ የቀድሞዎቹ ካህናት ቍጥራቸው ብዙ ነበር፤ 24ኢየሱስ ግን ለዘላለም የሚኖር በመሆኑ፣ ክህነቱ የማይሻር ነው። 25ስለዚህ ስለ እነርሱ እየማለደ ሁልጊዜ በሕይወት ስለሚኖር፣ በእርሱ በኩል ወደ እግዚአብሔር የሚመጡትን ፈጽሞ7፥25 ወይም ለዘላለም ሊያድናቸው ይችላል።

26እንግዲህ ለእኛ የሚያስፈልገን፣ ቅዱስ፣ ነቀፋ የሌለበት፣ ንጹሕ፣ ከኀጢአተኞች የተለየና ከሰማያት በላይ የከበረ እንደዚህ ያለ ሊቀ ካህናት ነው። 27እርሱም እንደ ሌሎቹ ሊቃነ ካህናት መጀመሪያ ስለ ራሱ ኀጢአት፣ ከዚያም ስለ ሕዝቡ ኀጢአት በየቀኑ መሥዋዕት ማቅረብ አያስፈልገውም፤ ራሱን በሰጠ ጊዜ፣ ስለ ኀጢአታቸው ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ መሥዋዕት አቅርቧልና። 28ሕጉ ደካማ የሆኑትን ሰዎች ሊቃነ ካህናት አድርጎ ይሾማልና፤ ከሕግ በኋላ የመጣው መሐላ ግን ለዘላለም ፍጹም የሆነውን ልጅ ሾሟል።

Knijga O Kristu

Hebrejima 7:1-28

Melkisedek i Abraham

1Melkisedek je bio šalemski kralj i svećenik Svevišnjega Boga. Kad se Abraham vraćao iz bitke u kojoj je pobijedio nekoliko kraljeva, Melkisedek mu je izišao u susret i blagoslovio ga. 2Tada je Abraham uzeo desetinu od svega što je u ratu osvojio i dao Melkisedeku, čije ime najprije znači “Kralj pravednosti”, a zatim i “Kralj mira”, jer šalem znači “mir”. 3U Svetome pismu nije zapisano ništa o njegovu ocu i majci ni o njegovu rodoslovlju, kao ni o datumima njegova rođenja i smrti. On je sličan Božjemu Sinu jer kao da zauvijek ostaje svećenikom.

4Razmotrite kako je velik bio Melkisedek: veliki izraelski patrijarh Abraham priznao ga je velikim dajući mu desetinu od najboljeg plijena. 5Svećenicima, Levijevim potomcima, Zakon je nalagao da ubiru desetinu od svih, iako su im bili rođaci jer su svi bili Abrahamovi potomci. 6Ali Melkisedek, koji nije bio u srodstvu s levitima, uzeo je desetinu od Abrahama, koji je imao Božje obećanje, i blagoslovio ga. 7A neprijeporno je da uvijek onaj tko je veći blagoslivlja manjega. 8Židovski su svećenici, iako smrtnici, primali desetinu, a za Melkisedeka Bog kao da svjedoči da još živi—jer u Svetome pismu nije zabilježeno ništa o njegovoj smrti. 9Moglo bi se čak reći da su i Levijevi potomci, koji ubiru desetinu, dali Melkisedeku desetinu kroz svojega pretka Abrahama. 10Jer iako se Levi tada još nije ni rodio, sjeme iz kojega je proistekao bilo je u Abrahamovu boku kad je Melkisedek od njega ubrao desetinu.

11Da je levitsko svećenstvo moglo ispuniti Božju nakanu—a na njemu se temeljio Zakon—zašto bi još bilo potrebno da Bog pošalje drukčijeg svećenika, sličnoga Melkisedeku, a ne iz Aronova reda?

12Ako se mijenja svećenstvo, mora se promijeniti i zakon koji će to omogućiti. 13Jer taj o kojemu je riječ pripada drugom plemenu, pripadnici kojega ne služe za oltarom. 14Jasno je, naime, da je naš Gospodin podrijetlom iz Judina plemena, koje Mojsije nikad nije spomenuo u svezi sa svećenstvom.

Isus kao Melkisedek i postao je jamcem boljega saveza

15Promjena u Zakonu još je očitija zbog činjenice da je postavljen drugi svećenik, sličan Melkisedeku. 16On svećenikom nije postao stoga što je zadovoljavao stari zahtjev da pripada Levijevu plemenu, već snagom neuništivog života. 17Sveto pismo svjedoči o Kristu:

“Ti si svećenik zauvijek

i po tome sličan Melkisedeku.”7:17 Psalam 110:4.

18Stara zapovijed više ne vrijedi jer je bila nedjelotvorna i nekorisna. 19Zakon nije ništa priveo k savršenstvu. Zato nam je dano nešto bolje čemu se možemo nadati, što će nas približiti Bogu.

20Bog se zakleo da će Krist zauvijek biti svećenikom, što za druge svećenike nikada nije učinio. 21Jedino je njemu rekao:

“Gospodin se zakleo

i neće to opovrgnuti:

‘Ti si svećenik zauvijek.’”7:21 Psalam 110:4.

22Božjom je zakletvom Isus postao jamcem boljega saveza.

23U starome sustavu bilo je mnogo svećenika jer ih je smrt priječila da trajno ostanu: kad bi jedan svećenik umro, na njegovo bi mjesto došao drugi. 24Ali Isus ostaje svećnikom zauvijek i njegovo svećeništvo neće proći. 25Zato on jednom zauvijek može spasiti svakoga tko po njemu pristupi k Bogu. On zauvijek živi i posreduje za njih.

26Takav nam veliki svećenik i treba—svet, nedužan, neokaljan grijehom, odvojen je od grešnika i uzvišeniji od nebesa. 27Ne mora svakoga dana prinositi žrtve poput drugih svećenika. Oni su to činili za vlastite grijehe, a zatim za grijehe drugih ljudi. Ali Isus je to učinio jednom zauvijek žrtvujući se na križu. 28Veliki svećenici iz Mojsijeva doba bili su samo ljudi podložni slabostima. Ali nakon Zakona Bog je zakletvom na to mjesto postavio svojega Sina, zauvijek savršena.