ዕብራውያን 6 – NASV & CRO

New Amharic Standard Version

ዕብራውያን 6:1-20

1ስለዚህ ስለ ክርስቶስ የተሰጠውን የመጀመሪያ ትምህርት ትተን ወደ ብስለት እንሂድ፤ ከሞተ ሥራ ንስሓ ስለ መግባትና6፥1 ወይም ከከንቱ ሥርዐት በእግዚአብሔር ስለ ማመን እንደ ገና መሠረትን አንጣል፤ 2እንዲሁም ስለ ጥምቀቶች፣ እጆችን ስለ መጫን፣ ስለ ሙታን ትንሣኤና ስለ ዘላለም ፍርድ ትምህርት እንደ ገና አንመሥርት። 3እግዚአብሔር ቢፈቅድ ይህን እናደርጋለን።

4አንድ ጊዜ ብርሃን የበራላቸውን፣ ሰማያዊውን ስጦታ የቀመሱትን፣ ከመንፈስ ቅዱስ ተካፋዮች የሆኑትን፣ 5መልካሙን የእግዚአብሔር ቃልና የሚመጣውን ዓለም ኀይል የቀመሱትን፣ 6በኋላ ግን የካዱትን እንደ ገና ወደ ንስሓ መመለስ አይቻልም፤ ምክንያቱም እነርሱ ለገዛ ጥፋታቸው የእግዚአብሔርን ልጅ እንደ ገና ይሰቅሉታል፤ ያዋርዱታልም።

7ዘወትር በእርሷ ላይ የሚወርደውን ዝናብ የምትጠጣና ለሚያርሷትም ፍሬ የምትሰጥ መሬት ከእግዚአብሔር በረከትን ትቀበላለች። 8ነገር ግን እሾኽና አሜኬላ የምታበቅል መሬት ዋጋ ቢስ ትሆናለች፤ መረገሚያዋም ተቃርቧል፤ መጨረሻዋም በእሳት መቃጠል ነው።

9ወዳጆች ሆይ፤ ምንም እንኳ እንደዚህ ብንናገርም፣ ከድነታችሁ ጋር የተያያዘ ታላቅ ነገር እንዳላችሁ ርግጠኞች ነን። 10እግዚአብሔር ዐመፀኛ አይደለም፤ እርሱ ሥራችሁን እንዲሁም በፊትም ሆነ አሁን ቅዱሳንን በመርዳት ስለ ስሙ ያሳያችሁትን ፍቅር አይረሳም። 11የተሰጠው ተስፋ እስኪፈጸም ድረስ እያንዳንዳችሁ እንዲህ ያለውን ትጋት እስከ መጨረሻ እንድታሳዩ እንመኛለን። 12በእምነትና በትዕግሥት የተስፋውን ቃል የሚወርሱትን እንድትመስሉ እንጂ ዳተኞች እንድትሆኑ አንፈልግም።

የእግዚአብሔር የተስፋ ቃል ርግጠኛነት

13እግዚአብሔር ለአብርሃም ተስፋ በሰጠው ጊዜ፣ የሚምልበት ከእርሱ የሚበልጥ ሌላ ባለመኖሩ፣ በራሱ ማለ፤ 14እንዲህም አለ፤ “በርግጥ እባርክሃለሁ፤ ዘርህንም አበዛዋለሁ።” 15አብርሃምም በትዕግሥት ከጠበቀ በኋላ የተሰጠውን ተስፋ አገኘ።

16ሰዎች ከእነርሱ በሚበልጥ ይምላሉ፤ መሐላውም የተባለውን ነገር ስለሚያጸና በመካከላቸው የተነሣው ክርክር ሁሉ ይወገዳል። 17እግዚአብሔር የማይለወጥ ዐላማውን ለተስፋው ቃል ወራሾች ግልጽ ለማድረግ ስለ ፈለገ፣ በመሐላ አጸናው። 18እግዚአብሔር ከቶ ሊዋሽ አይችልም፤ እርሱ በሁለት በማይለወጡ ነገሮች በፊታችን ያለውን ተስፋ ለመያዝ ወደ እርሱ ለሸሸን ለእኛ ብርቱ መጽናናት እንድናገኝ አድርጓል። 19እኛም የነፍስ መልሕቅ የሆነ ጽኑና አስተማማኝ ተስፋ አለን፤ ይህም ተስፋ ከመጋረጃው በስተ ጀርባ ወዳለው ውስጠኛ መቅደስ ይገባል። 20ይህም ስፍራ ኢየሱስ ስለ እኛ ቀድሞ የገባበት ነው። እርሱም እንደ መልከጼዴቅ ሹመት ለዘላለም ሊቀ ካህናት ሆኗል።

Knijga O Kristu

Hebrejima 6:1-20

1Prestanimo zato stalno iznova ponavljati temeljna znanja o Kristu. Pođimo radije dalje i sazrijevajmo u razumijevanju. Ne moramo opet počinjati ispočetka, o važnosti odvraćanja od mrtvih djela i o vjeri u Boga. 2Ne trebaju vam više upute o krštenjima, polaganju ruku, uskrsnuću od mrtvih i vječnome sudu. 3Pođimo stoga, uz Božje dopuštenje, dalje.

4Nije moguće da se ponovno obrate oni koji su već bili prosvijetljeni i okusili nebeski dar te postali dionicima Svetoga Duha, 5koji su okusili dobru Božju riječ i silu budućega svijeta, 6a zatim su otpali od Boga. Oni se ne mogu ponovno obratiti jer svojim postupcima sami iznova pribijaju Sina Božjega na križ i izvrgavaju ga ruglu.

7Jer kad se zemlja natopi kišom što na nju često pada i kad rađa dobrim plodovima korisnima rataru, prima blagoslov od Boga. 8Ali rastu li na njoj samo trnje i drač, odbačena je, pod prokletstvom, i bit će spaljena.

9Iako tako govorimo, uvjereni smo, dragi moji, da je s vama dobro i da ste na putu spasenja. 10Jer Bog nije nepravedan. Neće zaboraviti vaše djelo: da ste mu iskazali ljubav brinući se o drugoj braći, što i sada činite. 11Žarka nam je želja da sve do konca budete tako gorljivi da se ispuni vaša nada. 12Tako nećete duhovno otupjeti i postati ravnodušnima, nego slijediti primjer onih koji su zbog svoje vjere i strpljivosti postali baštinicima Božjih obećanja.

Božje obećanje daje nadu

13Kad je Bog Abrahamu dao obećanje, kako se nije imao zakleti kime većim, zakleo se samim sobom:

14“Izobilno ću te blagosloviti

i dat ću ti brojne potomke.”6:14 Postanak 22:17.

15Abraham je strpljivo čekao i dočekao da Bog ispuni obećanje.

16Ljudi se uvijek zaklinju nekime tko je veći od njih te tako zakletvom, kao potvrdom istine, završavaju svaku raspravu. 17Bog je zakletvom zajamčio baštinicima svojih obećanja da neće promijeniti odluku. 18Bog nam je dao svoje obećanje i svoju zakletvu. To dvoje ne može se promijeniti zato što Bog ne može prevariti. Stoga se mi koji smo se njemu utekli možemo hrabro držati nade koju nam je dao.

19To je pouzdanje poput čvrstog i pouzdanog sidra našim dušama. Uvodi nas iza zastora, u nebo, u Božje svetište. 20Isus je onamo već ušao za nas. Postao je vječnim Velikim svećenikom, sličan Melkisedeku.